2017 ኖቬምበር 29, ረቡዕ

ና....ተማር ልጄ

ና ተማር ልጄ !!!!!

ያኔ በለጋ እድሜዬ ጨቅላ ሳለው ከጥንቱ
በእጃቸው ልምጭን ይዘው ሲያስተምሩ ለህፃናቱ
እኔም ደግሞ እንድቀስም ከማያልቀው ጥኡም ዜማ
ጠርተውኝ ነበር የኔታ ወደ እውቀቱ ከተማ
ግዕዙን እንዳቀላጥፍ በንባብ ሆነ በዜማ
አዎ ጠርተውኝ ነበር
ሰላም እለኪን እንድደግም ቃለ እግዚአብሔር እንድማር
ና ብለውኝ ነበር ያኔ በአባቶች እግር እንድትካ
ውስጤ በቃሉ ታንፆ እንደ ፀደይ እንድፈካ
ጠርተውኝ ነበር ደጋግመው እውቀት ጥበብን ሊያወርሱኝ
ከአለም ዘፈን ዳንኪራ ጥኡም ዜማን ሊሰጡኝ
ታዲያ ልቤ ደንዳናው
ጨዋታን መርጦ የሄደው
አሁን የኔታን ናፈቀ ያንን ወርቃማ ጊዜ
አለምን አትኩሮ እያየ ተውጦ በዘን ትካዜ
ቁጭ ብሎ መማርን አሻ ከማያልቀው የእውቀት ማሳ
በየኔታ እግር ሊተካ በቅኔ ጌታን ሊያነሳ
አዎ ልቤ ፈለገ
ያኔ አሻፈረኝ ብሎ ሲለመን እንቢ እንዳላለ
አሁን ሁሉን ተመኘ ልቤ በሀሳብ ዋለለ
የኔታ እያለ ተጣራ ከፊቱ እርቀው ሄደው
ያ የልጅነት ጊዜ ደጉ ቀን እያናፈቀው
ና ተማር ልጄ ያሉት ድምፃቸው ትውስ እያለውsaramareyama.8900@gmail.com

ያንቺን እኔ ልኑር

*ያንቺን እኔ ልኑር*
በሆድሽ አርግዘሽ አምጠሽ መውልደሽ፣
አፈረ ትቢያ ለብሰሽ እኔን ማሳደግሽ ፣
ለአንቺ ሳሰስች ለእኔ መብሰልሰልሽ፣
የመከራሽ ብዛት ሲገባሽ ስቃይሽ፣
ያንቺን ልኑር አልኩኝ ባልኖረው ኑረሽን፣
ፊትሽ ማዲያት ለብሶ ውበት መልክሽ ጠፍቶ፣
የነበረሽ ውበት አዲስ መልክ አውጥቶ፣
የሚያሳሳው መልክሽ ከአንቺ ሳይኖር ቀርቶ፣
ልጄ ልጄ ማለት ደግነትሽ በዝቶ፣
እኔን ውብ አረግሽኝ የአንቺ ውበት ጠፍቶ፣
የአለም ዳርቻ ልክሽን አይለካው ስፍር ቁጥር የለው ሚዛን አይመዝነው፣
እምዬ ፍቅርሽን ምን ቃላት ሊገልፀው፣
ልክ ያልተገኘለት ጥልቅ ውቃኖስ ነው፣
መቼ ኖርሽ እናቴ ከቶ ያንቺን ኑሮ፣
ልጄ ልጄ እያልሽ ከአምና ከዘንድሮ፣
ሁሌ እንደተጓዝሽ በሀዘን እንጉርጉሮ፣
እሞላለሁ ብለሽ  አንቺ የእኔን ጉሮሮ፣
መቼ ኑረሽ ታውቂያለሽ ከቶ ያንቺን ኑሮ፣
እስኪ ትንሽ እንኳን አረፍ በይ እማዬ፣
እኔ ያንቺን ልኑር ዛሬ በተራዬ፣
እንዳንቺ ባልሆንም አምጨ ባልወልድሽ፣
ከአፌ ነጥዬ ለአንቺ ባላጎርስሽ
እኔ እንዳንች ሁኔ ምን ባልኖርልሽ፣
እንደ ወለድ አንጀት አንጀቴ ባይሆንሽ፣
ለእኔ የኖርሽውም እሩብ  ባልኖርልሽ፣
አርፍ በይ እናቴ ትንሽም ላግዝች።
ተፃፈ የካቲት 21-2009 አም
.ምsaramareyama.8900Gmail.com

2017 ኖቬምበር 25, ቅዳሜ

የምዕራፍ ሁለት/2/የ18ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

*_በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፫_*

_የምዕራፍ ሁለት/የ18ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቆና መልስ_⤵⤵⤵⤵

✅1⃣ ➡ታላቁ ንጉሥ ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እንደተባለ ብዙ ጌዜ ሰምተናል ዳዊትን ለመጀመርያ ጊዜ ልበ አምላክ ብሎ የጠራው ነብይ ማነው? ለሁለተኛ ጊዜ ልበ አምላክ ዳዊት ብሎ የጠራው ሐዋርያስ ምን ይባላል?? ከመጽሐፍ ቅዱስ ማስረጃ???

*//መልስ//👉ነብዩ ሳሙኤል ነው። (1ኛ ሳሙ13፥13*)

*ቅዱስ ጳውሎስ ነው። (የሐዋርያት ስራ13÷ 22ላይን*)

✅2⃣ ➡እኔ ማነኝ ?
ምድያማውያን እስራኤልን ሲወሩ እንዳልታይ በወይን መጭመቂያ ስፍራ ስንዴ አበጥር ነበር የእግዚአብሔር መልእክተኛ ተገለጠና አንተ ሀያል ሰው እግዚአብሔር ካንተጋር ነው አለኝ መልአኩ ተገልጦ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ነው ስላለኝም ምድያማውያን በ300 ችቦ ድል አደረኳቸው ይህ ሁሉ ታሪክ ያለኝ እኔ ማነኝ??

*//መልስ//*.👉  *ጌድዮን*

✅3⃣➡  የሶምሶን ሀይል በፀጉሩ ላይ እንዳለ ሚስጥር ያወጣችበት ሴት ማን ትባላለች??

*//መልስ*//* 👉 *ደሊላ*

✅4⃣ ➡ሳዖል ዳዊትን ብዙ ጊዜ ሲያሳድደው  ዳዊት ግን እግዚአብሔር የቀባውን እራሱ   እስኪንቀው ድረስ አልገልግም እያለ መግደል ሲችል አልፎታል በ፩ድ ወቅት ሳዖል በዋሻ ውስጥ  እያለ ዳዊት ወደ እርሱ ቀረበና የሚገርም ነገር ሰርቶ ነበር። ምን ይሆን??

*መልስ የሳዖልን ልብስ ለምልክትነት ተቆርጦ አሳየው ከአጠገቡ የነበረውን ኮዳና ሰይፍ ለምልክትነት ወስዶ አሳየው (1ኛ ሳሙ 24 ፥ 1 1ኛ ሳሙ 26፥8*)


✅5⃣ ➡አንድ መስፍን ጦርነት ወጥቼ በድል ብመለስ ሊቀበለኝ የሚወጣውን ማንኛውንም ሰው መስእዋት አርጌ አቀርባውለ አለ እንዳለውም ከጦርነቱ በድል ሲመለስ ለአይኑ ማረፊያ የሆነችውን አንዲት ሴት ልጅ ነበረችውና ከበሮ እየመታች ልትቀበለው እሮጠች ያ ሰው ግን ከሩቅ አያትና አዘነ ልጅንም መስእዋት ትሁን ብሏልና አቃጠላት ይህ ልመና የማይችልበት ሰው ማን ይባላል?

*//መልስ//👉መስፍን ዮፍታሔ ነው።( መሳፍንት 11፥ 31*)

✅6⃣ ➡አንዳንድ ጊዜ ለቅዱሳን መስገድ ለማን ይበጃል የሚሉ ጥቂት አይዱሉም መፅሀፍ ቅዱስ ግን የነብያት ማህበር እኛም እኮ ነብያት ነን ሳይሉ ለንብዩ ኤልሳዕ ሰገዱ ይሉናን። ነብያት ለኤልሳዕ የሰገዱት በምን ምክንያት ነበር??

*//መልስ//👉 መንፈስ በኤልሳዕ ላይ እጥፍ ሆኖ ስላደረበትና በመጎናፀፊያው ዮርዳኖስን ሲከፍል አይተው ነብያቱ ለኤልሳዕ ሰገዱ 2ኛ ነገሥት 2፥15*

✅7⃣ ➡ንጉሥ ሲሳራ እስራኤልን ለ20 አመት አስጨንቆ ገዝቷት ነበር አንዲት። ሴት ነብይ ባርቅን አስተርታ ተነሳ እግዚአብሔር ሲሳራን በእጅህ ጥሎልሃል አለችው ባርቅም አንች አብረሽኝ ካልሔድሽ አልነሳም አለ ያች ሴት ነብይም ባርቅን አስከትላ ወደ ታቦር ተራራ ወጣችና ሲሳራን ድል አደረጉ ይህች ሴት ነብይት ማን ትባላለች???

*//መልስ// 👉ዲቦራ ናት የስሟ ትርጉም ንብ ማለት ነው ይህንን ታሪክ  መዝሙር ላይ ዲቦራና ባርቅ እያልን በብዛት እንዘምረዋለን መሳፍንት 4፥1*

✅8⃣ ➡እስራኤላውያን በባቢሎን ከተወረሩ ቡኋላ ህዝበ እስራኤል ወደ ባቢሎን ፈለሱ ጥቂት እስራኤላውያን ግን በእስራኤል ቀሩ ናቡከደነጾር በእስራኤል ለቀሩት ህዝብ  ንጉሥ ያደረገው ማንን ነበር??

*// መልስ//👉ጎዶልያስ ነው 2ኛ ነገስት 25 ፥23*


✅ 9⃣➡የኢያሪኮ ውሀ መመረዙ ምክንያት የከተማዋ ነዋሪዎች እጅግ ተቸገሩ ወደ ነብዮ ኤልያስም ቀረቡና እነሆ የከተማዋ ኑሮ መልካም ነው ውሀዋ ግን መራራ ነው የኢያሪኮ ውሀ መራራ ነው ሴቶች ውሀውን ሲጠጡ ይመክናሉ ፈውስልን አሉት ኤልሳም አዲስ ማሰሮ አምጡ ጨውም ጨምሩበት አላቸው ያን ጨው በውሀው ምንጭ ላይ ቢያደርገው መራራው የኢያርኮ ተፈወሰ
ወደ ቃና ዘገሊላ እንምጣ ኤልሳዕ የጌታ ምሳሌ ነው ኤልሳዕ አዲስ ማሰሮ አምጡ እንዳለ ጌታም 6 ጋኖችን አምጡ አለ ኤልሳዕ ማሰሮውን ጨው ሙሉበት እንዳለ ጌታም ማሰሮውን ውሀ ሙሉበት አለ ወይን የተሞላበት የቃና ዘገሊላ ማሰሮ ጨው የተገኘባት የኤልሳዕ ማሰሮ ማናት

*መልስ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት*

✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣0⃣➡
👉ለኢዮብ ጽናትን
👉ለሰሎሞን ጥበብን
👉ለኤርምያስ ትንቢትን ካልን!
👉ለአብርሃም *__//መልስ* *👉_ደግነት እንላለን።*


✅ጥ.ተራ(ቁ) 1⃣1⃣➡አባታችን ፃዲቁ  ቅዱስ ላሊበላ ካነጻቸው ከሁሉም ቤተመቅደሶች በስፋት  አንደኛ የሆነው ማን ነው??

*//መልስ//* *👉ቤተ መድኃኔአለም ነው።*

✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣2⃣➡የመንግስተ ሰማያት መክፈቻዎች እሰጥሀለሁ በምድር የምታስረው ሁሉ በሰማያት የታሰረ ይሆናል በምድርም የምትፈታው ሁሉ በሰማያት የተፈታ ይሆናል። ብሎ ጌታ  ቃል  የገባለት ለማን ነው?/ማን /ይባላል??

*//መልስ//* *👉ለቅዱስ ጴሮስ ነው።*

✅ጥ.ተራ.( ቁ)1⃣3⃣➡የፃድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥  እግዚአብሔር  ያድናቸዋል። ይህ ቅዱስ ቃል  የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል??_

_ሀ/ (መዝ 33፥ 19)_

_ለ_/ (መዝ 32፥19)_
_ሐ/ ( መዝ 20፥13)_
_መ/ መልስ የለም_


*//መልስ//* *👉ሀ)፨መዝ.33፥19 ላይ ይገኛል።*


✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣4⃣➡፠  እንደ ሚካኤል ማለት ምን ማለት ነው?? እያንዳንዱ ፊደል
፠   ሚ  . ...
፠  ካ......
፠  ኤል ...? የሚልቱስ.???

*//መልስ//*👇👇
፠   ሚካኤል ማለት *መኑ አምላክ
፠   እግዚአብሔር ያለ ማነው ?*
፠   ማለት ነው  ሚካኤል የሚለው ስም
፠   ቃሉ የዕብራይጥስ ነው ።
፠   ሚ  . መኑ
፠  ካ. የሚለው  ከመ  ማለት ሲሆን
፠  ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው።


✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣5⃣➡ሕዳር 12 ቀን የሚከበረው ዓመታዊ የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል ምንን በተመለከተ ነው???


*//መልስ//* *👉ህዳር 12 የተሾመበት ዲያብሎስን ድል የነሳበት ህዝበ እስራኤል የመራበት እለት ነው።*
2ኛ👉ህዳር 13 በዓለመ መላእክት ያሉ አእላፍ መላእክት በዓለ ሲመቱን ተሰብስበው ያከበሩበት ቀን ነው።

✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣6⃣➡ከሚከተሉት ውስጥ የማይገባ የክርስትና ስም/ለሰው ሊሰየም የማይገባ ስም የትኛው ነው??

ሀ) አማኑኤል

ለ)ዘአማኑኤል

ሐ/ ሣህለ ሥላሴ

መ/ ዘሚካኤል

ሠ/ ሁሉም

*//መልስ//* *👉ሀ)፨ አማኑኤል*

☞ የማይገባ የክርስትና ስም
በአምላክ ስም በቀጥታ መጠራት አይገባም ለምሳሌ፡- አማኑኤል፣ኤልሻዳይ፣ኢየሱስ እነዚህ ስሞች ለሠው ልጆች መጠናችን ስላልሆኑ መጠቀም የለብንም፡፡ በዚህ ምትክ ገብረ አምላክ፣ሣህለ ሥላሴ፣ፍቅርተ ክርስቶስ ፣ዘአማኑኤል በማለት መሰየም ይቻላል፡፡
☞በቅዱሳንም ስም በቀጥታም ሆነ ዘርፍ እየተደረለት መሰየም ይቻላል፡፡
 ለምሳሌ፡- ዘማርያም፣ዘሚካኤል፣አጸደ ማርያም፣ ተክለ ሐይማኖት ወዘተ...

✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣7⃣➡የቅዱስ ትውፊት ዋና ማዕከሉ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶ ነው።
 ትውፊት የምእመናን የዘወትር ሕይወት ነው። ለመሆኑ ትውፊት ማለት ምን ማለት ነው??

*//መልስ//*👉 ትወፊት ማለት በሰዋስዋዊ ዘይቤው ሲፈታ  ስጦታ፣ ልማድ፣ ትምህርት፣ ወግ፣ ታሪክ፣ ሃይማኖት፣ ሥርዓት፣ከጥንት ከአበው ሲያያዝ ሲወርድ፣ ቃለ በቃል ሲነገር የመጣ ማለት ነው።

✅ጥ.ተራ(ቁ)1⃣8⃣➡ ታቦትን በቅዱሳኑ ስም እንዲሰየም ያዘዘው ማነው??

*//መልስ//* *👉ክብር ይግባውና እራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ነው።* *(ዘጸ. 31፥1-11)(ዘጸ 37፥1)*

✅ጥ.ተራ( ቁ)1⃣9⃣➡ዘመነ ብረሃን የሚባለው ከልደተ ዳዊት እስከ ፍልሰት ባቢሎስን"14"ቱ ትውልድ ነው። ብርሀን የተባለው ጌታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ነው ። *ትክክል ወይም ትክክል አይደለም በማለት መልስ/ሽ/*
*//መልስ//* *👉ትክክክል ነው።*

✅ጥ.ተራ(ቁ)2⃣0⃣➡ዘመነ 'ሀጋይ'  ማለት 'ከታህሳስ 26-መጋቢት 25"  ያለው ሲሆን የቃሉ ትርጎሚ ሀጋይ ፡ደርቅ,ጸሀይ፡ሀገር፡በጋ፡፡ሲሆን ከ4ቱ ክፍለ ዘመነ አንዱ ነው።
 *ትክክል ነው ወይም አይደለም በማለት መልስ/ሽ/*
*//መልስ//* *👉ትክክል ነው።*


_ወስብኃት ለእግዚአብሔር_saramareyama.890@gmail.com

2017 ኖቬምበር 22, ረቡዕ

የምዕራፍ ሁለት(የ17ኛ) ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ውድድር

*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፫*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ሰነበታችሁ?? ሰላማችሁ ይብዛ!!_

_፨የምዕራፍ ሁለት/17ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር 

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
_↪ ጥ.ተራ (ቁ)1⃣✍ ቅዱስ ሉቃስ ስንት መጻህፍት ጽፏል ❓_
   _፨መልስ፨  መልስ ሁለት የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋሪያት ስራ።✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)2⃣✍ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈው ለማን ነው❓_

       _፨ መልስ ፨ለቅዱስ ቴዎፍሎስ_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ) 3⃣✍ለመጀመርያ ጊዜ ስዕለት የተሳለ አባት ማን ይባላል❓_

         _፨መልስ፨ አባታችን ያዕቆብ ነው ዘፍጥረት 28፥20_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)4⃣✍ ሄኖክ ማለት ምን ማለት ነው?? መጽሐፈ ሄኖክስ በስንት ዓ.ም ተጠረዘ❓_

       _፨መልስ ፨ሄኖክ ማለት አዲስ ማለት ነው።ሲሆን መጽሐፈ ሄኖክ በ4014 አመተ አለም ቅድመ ልደት ክርስቶስ ነው የተፃፈው። የተፃፈበት ቦታ ደብረ ቅዱስ ይባላል ይህ ቦታ ከገነት ትዮዩ የሆነ ቦታ ነው።_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ) 5⃣✍ከሚከተሉት  ከ፲፪(ከአስራ ሁለቱ)የሐዋርያት ወገን  የቱ ነው❓_

ያልሆነውሀ) ጳውሎስ 
ለ) ጴጥሮስ
ሐ) በርተሎሜዎስ
መ) ዮሐንስ

       _፨መልስ፨ ሀ) ጳውሎስ ✅_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)6⃣✍ሐዋርያ ማለት ምን ማለት ነው❓_

ሀ) የተላከ 
ለ) ልዑክ 
ሐ) ሂያጅ 
መ) ሁሉም መልስ ነው

        ፨መልስ፨መ) ሁሉም መልስ ነው ✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)7⃣✍ቅዱስ ሉቃስ ማነው❓_

_ሀ. ወንጌላዊ ነው_
_ለ. ሰአሊ ነው_
_ሐ.  ሀኪም ነው_
_መ. ከ 72 አርድት መካካል ነው_
_ሰ. ሁሉም መልስ ነው_

        ፨መልስ፨.........መ) 

_↪ጥ.ተራ(ቁ)8⃣✍ የብሔረ ብፁሀንን ታሪክ የፃፈው አባት  ማን ይባላል ❓_
 _የፃፈው ቅዱስ አባትስ ከብሔረ ብፁሀን ሲመለስ ምን አጋጠመው❓_ያጋጠመው

       ፨ መልስ፨
 ቅዱስ ዞሲማስ ነው። ሲመልስ 
 ከሰራዊቱ ጋር    ሁኖ ሲመለስ ዲያቢሎስ የብሔረ ብፁሀንን ታሪክ  መጽሐፍንም  ሊወስድበት ከጀለ ነገር ግን በእግዚአብሔር  እና በመላእክትናን ተራዳኝነት ሰይጣንን ድል አድርጓል። ✅


_↪ ጥ.ተራ(ቁ)9⃣✍በኃጢአያት  የሚያደርገን ምንድነው❓_

_ሀ/  ምክንያተኝነት_
_ለ/  ለመንፈሳዊ ነገሮች ያለንን ከበሬታ መቀነስ_
_ሐ/  ወደ ኃጢአያት የሚመራንን ነገር አለማቑረጥ_
_መ/  ሁሉም መልስ ነው_ዳዊት


         _፨መልስ፨ መ/ ሁሉም  ነው።✅_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)🔟✍ከአብረሀም እስከ  ያለው ዘመን ምን ይባላል❓_

_ሀ/  ዘመነ አበው ይባላል_
_ለ/  ዘመነ ነቢያት ይባላል_
_ሐ/  መልሱ የለም_

          _፨መልስ፨ ሀ/ ዘመነ አበው  ይባላል።_✅

_↪ጥ.ተራ(ቁ)1⃣1⃣✍በሙሴ ስም ከሚጠሩት ቅዱሳንይ መካክል የምታውቀውን ጥቀስ/ሽ❓_


        _፨መልስ፨_👇
1-ሊቀ ነቢያት ሙሴ 
2-አቡነ ሙሴ ዘድባ 
3-አቡነ ሙሴ ዘገርአልታ 
4-ሰማዕቱ አቡነ ሙሴ 
5-አቡነ ሙሴ ዘትግራይ
6-አቡነ ሙሴ ጸሊም
7-አቡነ ሙሴ ዘቡልጋ
8-አቡነ ሙሴ ዘገዳመ ሲሐት

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣2⃣✍ዮሴፍ የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ ድንግል ማርያምን  አላወቃትም፤ ሲል ምን ለማለት ነው❓_

        _፨መልስ፨_👇
_ _፦ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን_ _ትመስላለች:: ብርሌ_
_የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ_ _ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ_
_ይቀያየራል:: እመቤታችንም_ _ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ_
_መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኩዋ_ _አብሮ ሲለዋወጥ እያየ_
_ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::_

_+'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ። __ያለውስ ማን ነው?' _እያለ_
_ይጨነቅ ነበር:: ጌታን_ ከወለደች_ _በሁዋላ ግን አንድ_
_ሕብረ መልክ ሆናለችና::_ _አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች_
አላወቀም::_

_+አሁን ግን ልጇ አምላክ_ _ዘበአማን: እርሷም ወላዲተ_
_አምላክ መሆኗን አወቀ ማለት ነው።✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣3⃣✍_
_በታምረ ማርያም ፀሎት ላይ 3_ _ጊዜ እሰግድ ለኪ(3)!_
_ብለን እንሰግዳለን፣ይህንን_ _ሰግደት ያሰተማረን ቅዱስወርቅ አባት_ _ማን ይባላል❓_እንዴትስ ተጀመረ❓

      _፨መልስ፨_✍
 _ዮሀንስ አፈ  አሀዛብን በሚያስተምርበት ወቅት የእመቤታችን ስዕል አፍ አውጥታ "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች… እርሱም ታጥቆ 3 ጊዜ የሰገደላትን ለማስታወስ ነው።_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣4⃣✍የሚስጥረ ትንሳኤ ሙታን አፈፃፀም ከመፃፍ ቅዱስ ውስጥ ቅዱስ ጳውሎስ ከፃፈው ሁለቱን ጥቀሱ ❓_
           _፨መልስ፨_👉ወደ ኤፊ_ 2፥1 በበደላችሁና _በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ በእነርሱም በዚህ አለም እንዳለው ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሰራው መንፈስ አለቃ እንደኮነው በአየር ላይ ስልጣን እንዳለው አለቃ ፍቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው_ 

 _ሮሜ 1፥4_
_ይህም ወንጌል በስጋ ከዳዊት_ _ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና_ _መንፈስ ግን ከሙታን መነሳት_ _የተነሳ በሀይል የእግዚአብሔር_ _ልጅ ኮኖ ስለተገለጠ ስለ ልጁ_ _ነው እርሱም ጌታችን ኢየሱስ_ _ክርስቶስ ነው።_
_ሮሜ 1 ፥3-4ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን_ _ከሙታንሥራው መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ_ _ክርስቶስ ነው።_

_2ኛ ቆሮ 1፥9 ወዘተ..._✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣5⃣✍እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ፥ በቀድሞ  መጀመሪያ…ከጥንቱ *ከዘላለም* ጀምሮ_ *_ተሾምሁ* ፤ ምድር _ከመፈጠርዋ_ አስቀድሞ።_
_ቀላያት ገና ሳይኖሩ እኔ_ _*ተወለድሁ* ፥ የውኃ ምንጮች ገና ሳይፈልቁ… ተራሮች ገና_ _ሳይመሠረቱ፥ ከኮረብቶች በፊት_ _*እኔ ተወለድሁ፥* የሚለውን ቃል *እግዚአብሔር ወልድ* ከተጥንት ከአባቱ ከእግዚአብሔር አብ_ _*መወለዱን* በመንፈስ ቅዱስ የገለፀለት ቅዱስ ማን ይባላል❓_

   _፨መልስ፨_......ንጉሥ   ሰሎሞን ነዉ።
መፅሀፈ ምሳሌ ምዕ8:22—23

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣6⃣✍*1*/, ነብዩ ኤርሚያስ አገልጋዩን ጠርቶ ለንጉስ ኢዮአቄም ትንቢቱን እንዲያነብለት አዘዘው፤ይህ የኤርሚያስ አገልጋይ ማን ይባላል ?ንጉስ ኢዮአቄምስ ትንቢቱን ሰምቶ ምን አደረገ❓_
   _ፍንጭ ኤር(36፤23)_

             _፨መልስ፨_👇
_~የኤርሚያስ አገልጋይ ባሮክ ሲሆን ንጉሱም ትንቢቱን ሰምቶ በእሳት አቃጠለው ፤እሱም ተቀሰፈ_

_ባሮክም ትንቢቱን ከኤርሚያስ  እንደገና ፃፈው_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣7⃣✍በአንድ ወቅት የሶርያው ንጉስ በብዙ ሺ ሠራዊት  እስራኤልን ከበበ ፤የኤልሳ ደቀመዝሙር የነበረው ግያዝም የሰራዊቱን ብዛት አይቶ ጌታዬ ዛሬስ መጥፋታችን ነው ! እያለ ጮህ ይህን ግዜ ኤልሳ ለግያዝ ምን አለው ? ልባምላክ ዳዊትስ ይህን በተመለከተ በመዝሙሩ ላይ ''ይትዓየነን መልአክ እግዚአብሔር አውዶሙ ልእለ ይፈርሆ ወይአድሃኖሙ'' ብሎ ዘመረ ምን ማለት ነው❓_
   _ፍንጭ 2ኛ ነገስት (6፤16)፣(መዝ 33፤7)_

       _፨ መልስ፨_👇
_ከእኛ ጋራ ያሉት ከነርሱጋር_ _ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ_
_1ኛ ነገስት (6፤16)_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣8⃣✍እኛ ከየት ይሆን የተጠራነው እንደ ኤርሚያስ ከማሀፀን ? ወይስ ከአለም እቅፍ ?ከሀጢያት ባሀር ወይስ ከሞት አፋፍ ? ከአፈር እና _ከትብያ ላይ ወይስ ከምን_ _ይሆን የተጠራንው_
_ሙሴ እና ዳይት_ _ከእረኝነት፤ጴጥሮስን እና_ _እንድርያስን ከአሣ አጥማጅነት_ _የጠራ እግዚአብሔር ኤልሳዕን_ _ከምን ነበር የጠራው ?_በሬ _ጳውሎስ እና ሙሴ ፀሊምንስ❓_

          _፨መልስ፨_
_ኤልሳዕን 12 ጥማድ  እያረሰ ፤_
_ጳውሎስን ካሳዳጅነት ፤ሙሴ_ _ጸሊምን ከሽፍታነት_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)1⃣9⃣✍በቅዳሴ ላይ እንዲህ እያልን_ እናመሰግናለን_ _ሱራፌልይጸርውሁ ይሰግዱ_ _ሎቱ ወክሩቤል ይሴብሕዎ _ _እንዘይበሉ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ_ _እግዚአብሔር ,,,ይሄንን_ _ምስጋና በመፃፍ ቅዱስ የትኛው ምእራፍ ላይ እናገኘዋለን ❓_

                _፨መልስ፨_👇
_በትንቢተ ኢሳያስ ምእራፍ 6 ላይ ነው ፤ወንጌሉ እና ቅዳሴው እርስ በራሳቸው ይናበባሉ ለእያንዳዱ የቅዳሴ ዜማ እራሱን የቻለ የመፃፍ ቅዱስ ጥቅስ አለው።_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)2⃣0⃣✍ዲያቆናቱ በቅዳሴ ላይ ስለዝናብ እንማልዳለን ፣ስለተጨነቀች ነፍስ እንማልዳለን ፣ስለታመሙ እና ስለድዊያን እንማልዳለን ---እያሉ ይጸልያሉ ፤ንጉስ ሰለሞን ቤተክርስቲያንን ከሰራ ቡሀላ እራሱ እንደ ዳቆን ሆኖ ይህንን ፀሎት ጸልዮ ነበር ፣እግዚአብሔር ለዚህ ጸሎት የሰጠው ምላሽ ምን ነበር ❓_
  _ፍንጭ 1ኛ ነገስት (8፤35)፤_ _1ኛ ነገስት (9፤3)_

            _፨መልስ፨_👇
_በፊቴ ያቀረብከውን ልመናና ፀሎት ፤አይኖቼ እና ልቤ ዘወትር ወደ ሰራከው ቤተመቅደስ ይሆናሉ   1ኛ ነገስት (9፥3)_✅
.890@gmail.com

የምዕራፍ ሁለት(የ16ኛ)ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር


*_በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን አላችሁ? ይህ የምዕራፍ ሁለት/16ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር መረሀ ግብር ነው_
፨፨፨፨♥♥፨፨፨፨፨፨⤵

↪ጥ.ተራ/ቁ/ ➡1⃣አቤሜሌክ ኑሃሚንና ሁለቱ ልጆቿ ወደ ሞአብ ምድር የወረዱት በምን ምክንያት ነው???

*//መልስ//*፡-✍ በረሃብ ምክንያት ነው፡፡ መ.ሩት[1፥1]

↪ ጥ.ተራ/ቁ/➡2⃣ ኑሃሚን ሩትን ሄዳ ቃርሚያ እንድትቃርም የላከቻት ወደ ማን እርሻ ነበር?? የእርሻው ባለቤትስ ለኑሃሚን ምኗ ነው??

*//መልስ//*፡- ✍ወደ ቦኤዝ እርሻ፡፡ ለኑሃሚን የባሏ የአቤሜሌክ ዘመድ ነው፡፡

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡3⃣የነቢዩ የሳሙኤል እናትና አባት ማን ይባላሉ?? ሳሙኤል ማለትስ ምን ማለት ነው??
*///መልስ//*፡- ✍አባቱ ሕልቃና ሲሆን እናቱ ሐና ትባላለች፡፡ ሊቀ ካህኑ ዔሊ፡፡ ሳሙኤል ማለት እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው፡፡ 1ኛ ሳሙ.1÷1-21

↪ጥ.ተራ/ቁ/ ➡4⃣ በነቢዩ ሳሙኤል አማካኝነት ተቀብቶ ለመጀመሪያ ጊዜ የነገሠው የእስራኤል ንጉሥ ማን ይባላል??

*//መልስ//*፡-✍ ንጉሥ ሳኦል ነው፡፡ 1ኛ ሳሙ.10÷1

↪ጥ.ተራ/ቁ/ ➡5⃣እስራኤልዊያን በባሊሎን ከተወረሩ በኋላ ህዝበ እስራኤልን ወደ ባቢሎን ፈለሱ፤ጥቂት እስራኤልዊያን ግን በእስራኤል ቀሩ፤ናቡከደ ነጾር በእስራኤል ለቀሩት ህዝብ ንጉሥ ያደረገው ማንን ይባላል??

*//መልስ//*✍ጎልያስ ነው።

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡6⃣በመጽሐፍ ቅዱስ ፈጣኑ የሕግ ፀሐፊ ዕዝራ ነው፤የነቢዩ ኤርሚያስን ትንቢት ቃል በቃል ይጽፍ የነበረው ሰው ማን ይባላል??

*//መልስ//*፦✍ባሮክ ነው። ኤር[36፥329]

↪ጥ.ተራ/ቁ/ ➡7⃣በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ሙት ያስነሳው ነብይ ማን ይባላል???

*//መልስ//*✍ነቢዩ ኤልያስ ነው።

↪ጥ.ተራ/ቁ/8⃣ጽጌ ማለት ምን ማለት ነው???ማኅሌተ ጽጌ ማለትስ ምን ማለት ነው??

*//መልስ//*✍ጽጌ ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ አበባ የፍሬ ምልክት ማለት ነው። ማኅሌተ ጽጌ የሚለው በአንድ ሲጠቃለል የአበባ ምስጋና ማለት ነው።
ይህም ድንግል ማርያም የማኅጸኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው። ማኅሌተ ጽጌን በግጥም /ቅኔ/ ስንኝ በ5 በ5 የተደረሰ ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰቱን ነው።

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡9⃣እኔ ማነኝ ነገሥታቱ ነቢዩ ኤርሚያስን በውሃ ጉድጎድ ውስጥ ሲጥሉት፤
30 ሰዎችን ጠርቼ በአሮጌ ጭርቅ አድርጌ ነቢዩን ከውሃ ጉድጎድ ውስጥ ፤አወጣሁት
 እኔ ማን ነኝ?


*//መልስ//*✍ኢትዮጵያዊ አቤሜሌክ ነው፤ ሰቆቃወ ኤር[38፥7]

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣0⃣በምርኩ እያለሁ ራዕይ  የምፈታ ትነቢት የምናገር ከአብይት ነቢያት መካከል የነበርሁ ዕብራዊ ነኝ የስሜ ትርጉም እግዚእብሔር ይፈርዳል ማለት ነው በአናብስት ጉድጓድ ተጥዪ አናብስቶች የእግሬን ትቢያ የላሱ እኔ ማንኝ?????

*//መልስ//*✍ዳንኤል ነው። በባቢሎን እያለ ሕልም ይፈታ የነበረውና በአናብስት ጉድጓድ የተጣለው።
        

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣1⃣እናቴ በአመፃ ፀነሰችኝ በኃጢአትም ወለደችኝ ብየ ስለ እራሴ ታነሺነት የተናገርሁ ከይሁዳ ዘር የተወለድሁ በልጅነቴ ለንግስና የተመረጥሁ እኔ ማነኝ???
      
*//መልስ//*✍ ነብይ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው።

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣2⃣እኔ ማነኝ,,?
 ከመቶ ሃያ ቤተሰብ የሆንሁ 
ድምሬ ከ36 ቅዱሳት አንስት ያለሁ 
ልጄ ሐዋርያ ምስሉ ዘአንበሳ ቤቴ ቤተ እግዚአብሔር የነበረ 
እኔ ማነኝ ስሜ ማን ይባላል???

*//መልስ//*✍የሐዋርያው የቅዱስ ማርቆስ እናት ማርያም ናት።

↪ጥ.ተራ/ቁ/ ➡1⃣3⃣ንጉሥ ሰሎሞን ያሰራው ቤተ መቅደስ ፫/3 ክፍሎች ነበሩት፤ ምን ምን ናቸው??


*//መልስ//*✍ቅድስተ ቅዱሳን፣ቅድስትና የውጪዊው አደባባይ ናቸው። 1ኛ ነገሥት [5፥1]


↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣4⃣ንጉሥ ዳዊት ቤተ መንግስቱን፣ ልጁ ሰሎሞንም ቤተ መቅደሱን እንዲሰሩ የዝግባ ዛፍ ሰጥቼያቸው ነበር፤ እኔ ማነኝ??

*//መልስ//*✍ኪራም ይባላል። 1ኛ ነገሥት [5፥5]

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣5⃣ማቁረርያ ማለት ምን ማለት ነው?? ጥቅሙስ ምንድነው???

መቁረር /መቁረሪት/ሰን/ኩስኩስት
• ማቁረርያ፣ ማብረጃ፣ ማቀዝቀዣ /ማንቆርቆሪያ/ ማለት ነው፡፡ /ፍት. ነገ. ፲፫/፡፡ የተቀደሰ የዘይት ቅባት ይቀባ ነበር፡፡ ዘጸ. ፴፥፲፯–፱፣ ዘጸ. ፵፥፴–፴፪፡፡ በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ከመዳብ ከነሐስ ከብርና ከመሳሰሉት ይሠራል፡፡
• ካህኑ በቅዳሴ ጊዜ እጁን ለመታጠብ ይገለገልበታል። ማንቆርቆሪያ ለቅዳሴ ጠበል መያዣ ያገለግላል፡፡ ጌታችንን አይሁድ ሊሰቅሉት አሳልፈው በሰጡት ጊዜ ጲላጦስ “እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ” በማለት የታጠበበትን ያመለክታል፡፡ ማቴ. ፳፯፥፳፯፡፡

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣6⃣ኤልሳዕ ነቢዩ ኤልያስን ለመጨረሻ ጊዜ ሲለየው ምን ብሎ ነበር የለመነው??

*//መልስ//*✍ኤልሳዕ ኤልያስን መንፈስህ በዕጥፍ እንዲያድርብኝ ብሎ ለመነው። 2ኛ ነገሥት [ 2፡9]


↪ጥ.ተራ/ቁ/➡1⃣7⃣ካህኑ ዕዝራ የሕጉን መጽሐፍ ለእስራኤልላዊያን እያነበበላቸው በጥሞና ያዳምጡ ነበር፤ እስራኤልላዊያን የዕዝራን ንባብና ትርጓሜ ለመስማት ስንት ሰዓት ይቆሙ ነበር??

*//መልስ//*✍፮/6/ ሰዓት ሙሉ ቁመው ይሰሙት ነበር፤ ነህምያ [8፣3]
 
↪ጥ.ተራ /ቁ/➡1⃣8⃣ሰጎን እንቁላሎቿን የምትፈለፍለው በምድን ነው?? የሰጎን እንቁላል ከቤተ ክርስቲያን ጉልላት ላይ የሚቀመጥበት/የሚሰካበት ሚስጢርስ ምንድን ነው???

*//መልስ//*✍ሰጎን እንቁላሎቿን የምትፈለፍለው ትኩር ብላ በማየት ነው። 
ሰጎን  እንቁላሏን ጥላ በዓይኗ ትኩር ብላ ካላየች እንቁላሏ ስለሚበላሽ ዓይኗን ከእንቁላሏ አታነሳም። ልዐል እግዚአብሔርም ይችን አለም እንዱሁ ይብጠቃታል። እኛ ከእርሱ ከተለየን እንጠልለን።። ከእመ፣ ከመላእክት ጻድቃን ሰማዕታት ላይ ዓይኑን አያነሳም ዘወትር የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ጉልላቷን እየተመለከተ ይኖራል።

↪ጥ. ተራ/ቁ/➡1⃣9⃣ነቢዩ ኤልያስ  ለደቀመዝሙሩ ለኤልሳዕ ፪/2/ጊዜ መጎናጸፊያውን ሰጥቶት ነበር፤ መቼና መቼ ነበር?? ኤልሳዕስ መጎናጸፊያውን ምን አደረገው??

*//መልስ//*✍ኤልያስ ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያገኘው ኤልሳዕ 12 ጥንድ በሬዎችን እያጠመደ ነበር፤ ሁለተኛው ደግሞ ለመጨረሻ ጊዜ ኤልያስና ኤልሳዕ ሲለያዩ ማለትም ኤልያስ በሠረገላ ባረገ ጊዜ እነሆ መጎናፀፊያውን ሰጥቶል፤ ኤልሳዕም በመጎናፀፊያው ዮርዳኖስን ከፍሎበታል።

↪ጥ.ተራ/ቁ/➡2⃣0⃣በአፍሪካ ለመጀመርያ ጊዜ የዜማን ምልእክት የተጠቀመው ማን ይባላል???

*//መልስ//*✍ኢትዮጵያዊ የዜማ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ነው።

*ወስብኃት ለእግዚአብሔር*


የምዕራፍ ሁለት(የ15ኛ)ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ውድድር

https://youtu.be/AAClj-P7IAM

*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፫*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ሰነበታችሁ?? ሰላማችሁ ይብዛ!!_

_፨የምዕራፍ ሁለት/15ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር_*

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

↪ጥ. ተራ (ቁ)1⃣➡✍ከሚከተሉት ውስጥ የራእይ መጽሐፍ የሆነው የትኛው ነው????

ሀ)፨ፍካሬ ኢየሱስ
ለ)፨ራእይ ሲኖዳ
ሐ)፨መጽሐፈ ሳቤላ
መ)፨ገድለ ፊቅጦር
ሠ)፨ሁሉም የራእይ መጽሐፍቶች ናቸው


*//መልስ//*👇

✍ሠ,፨ ሁሉም የራእይ መጽሐፍቶች ናቸው።

↪ጥ.ተራ(ቁ) 2⃣✍ኤልዛቤል ኤልያስን ልትገድል ታሳድደው ነበር፤ ኤልያስም ከኤልዛቤል ሸሽቶ በ፩/አንዲት ዛፍ ስር ቁጭ አለና ____ሲል/ ተናገረ???


*//መልስ//*👇
✍ከቀደሙ አባቶች አልበልጥምና ነፍሴን ውሰዳት። 1ኛ ነገሥት [19፥4]

↪ጥ.ተራ (ቁ)3⃣✍ሙሴ በሲና ተራራ 40 ቀንና ሌሊት እንደቆየ ሁሉ አንድ(፩)ነብይም እንዲሁ በኮራት ዋሻ ውስጥ 40 በቀንና ሌሊት ቆይቷል፤ ይህ ነብይ ማን ይባላል???

ሀ)፨ ነቢዩ ኤልያስ

ለ)፨ነቢዩ ኤልሳዕ

ሐ)፨ነቢዩ ዮናስ

መ)፨ መልስ የለም።



*//መልስ//*👇
✍ሀ,፨ ነቢዩ ኤልያስ ነው። 1ኛ ነገሥት [19፥8]

↪ጥ.ተራ.(ቁ)4⃣✍የአካአብ ልጅ አካዝያስ 50 ወታደሮችን ወደ ኤልያስ ላከ፤ ወታደሮችም ኤልያስን በንቀት ና ንጉሡ ይጠራሃል አሉት፤ ከዚያስ ኤልያስን የናቁት ወታደሮች ምን ሆኑ??
*/መልስ//*👇
 ✍ኤልያስን በንቀት የተናገሩት 50 አለቆች እሣት ከሰማይ ወርዳ በላቻቸው፤ ኤልያስን አክብሮ የሰገደው ነቢይም ሕይወቱን አተረፈ። 2ኛ ነገሥት [1፥9]

↪ጥ.ተራ.(ቁ)5⃣✍አበ ብዙሃን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን የሰዋበት የሞሪያ ተራራ ሌላ ስሙ ምን ይባላል??
*/መልስ/*👇

የጽዮን ተራራ ነው። ጽዮን ማለት አንባ መጠጊያ ማለት ነው፤ 2ኛ ዜና [3፥1]

↪ጥ.ተራ(ቁ)6⃣✍ጣዖት የማምለክና ከንቱነቱ የገዛ ልጁን መሰዋዕት አድርጎ ማቅረብ ነው፤ የራሳቸውን ልጅ ለጣዖት መስዋዕት አድርገው ካቀረቡት ሰዎች ውስጥ ፫ቱን ጥቀስ/ሽ/
*//መልስ//*👇

የሕዝቅያስ አባት ንጉሥ አካዝ፣ የሕዝቅያስ ልጅ ምናሴና መስፍኑ ዮፍታሔ ልጃቸውን ለጣዖት መሰዋዕት አድርገዋል። 2ኛ ዜና [28፥3] 2ኛ ነገሥት [21፥6]

↪ጥ.ተራ.(ቁ) 7⃣✍በቅደም  ተከተል ከብሉይ ኪዳን..እስከ ሐዲስ ኪዳን ቤተ መቅደስን የሰሩት ፫ቱ ነገሥታት እነማን ናቸው??

*/መልስ/*👇

ንጉስ ሰሎሞን፣ዘሩባቤልና ንጉስ ሄሮድስ ናቸው።

↪ጥ.ተራ.(ቁ)8⃣✍ሰሎሞን ያሰራው ቤተ መቅደስ በባቢሎናዊያን ከፈረሰ በኋላ ከእንደገና እንዲሰራ ያደረገው ሰው ማን ይባላል???

ሀ)፨ ዘሩባቤል

ለ)፨ ሄሮድስ

ሐ)፨  መልስ የለም

መ)፨ ሀ&ለ መልስ ናቸው

*//መልስ//*👇
✍መ,፨ ዘሩባቤል ነው። ዘሩባቤል ማለት የባቢሎን ልጆች ማለት ሲሆን ይህም ዘሩባቤል በባቢሎን ስለተወለደ የተሰጠው ስም ነው። ጌታችንም የመጣው ከዘሩባቤል የዘር ሐረግ ነው። ማቴ [1፥12]

↪ጥ.ተራ(ቁ) 9⃣✍ሐማ የተባለው ሰው በአይሁዳውያን ላይ የዘር ማጥፋት አዋጅ ባስነገረ ጊዜ በጾምና ጸሎት ይህንን አዋጅ ያስቀረችው ታላቅ ሴት ማን ትባላለች??

ሀ)፨ ሐና

ለ)፨አስቴር

ሐ)፨ ሩት

መ)፨ ሁሉም
*//መልስ//*👇

✍ለ,፨የመርዶክዮስ የአጎቱ ልጅ የሆነችው የመጀመርያ ስሟ ሀዳሳ ይባል የነበረ አስቴር ናት።.! አስቴር ማለት፦ኮከብ ማለት ነው። በአሁኑ ወቅት አይሁድ ታሪክ ለማስታወስ "  የአስቴር ጾም"  እያሉ ይጾሙታል።

↪ጥ.ተራ.(ቁ)1⃣0⃣✍የእመቤታችን የስደት ጊዜ ፫/3 ዓመት ከ፮/6 ወር መሆኑን የተገለጸበት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የትኛው ነው???

ሀ.፨ ማቴ. ፪፥፲፫

ለ.፨ ኢ.ሳ. ፰፥፲፬

ሐ.፨ ራዕ.፲፪፥፲፬

መ.፨ ሉቃ.፩፥፵-፰

*//መልስ//*👇
✍ሀ,፨ ማቴ 2፥13


↪ጥ.ተራ(ቁ) 1⃣1⃣✍በቅዱስ መጽሐፋችን በሴት ስም ከተሰየሙት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ውስጥ ሦስቱን ጥቀስ/ሽ??

*//መልስ//*👇
✍መጽሐፈ አስቴር፣መጽሐፈ ሩት፣ መጽሐፈ ዮዲት፣ መጽሐፈ ሶስና የመሳሰሉት ናቸው።

↪ጥ.ተራ(ቁ) 1⃣2⃣በቤተ ክርስትያናችን በዘመነ ጽጌ ማኅሌት የሚደረሰው ድርሰት ምንድን ነው? ማን ደረሰው? ቁጥሩስ ስንት ነው?

*//መልስ//*👇

✍ማኅሌተ ጽጌ ነው። ድርሰቱን የደረሰው አባ ጽጌ ድንግል ሲሆን  ትውልዱም በስሜን ሽዋ በይፋት አውራጃ ውስጥ ነው።የደረሱት የቁጥር ብዛት 150 ነው።

↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣3⃣✍በእጀ ጠባቤም ላይም እጣ ተጣጣሉ መዝ[22፡18]
ይህ ትንቢት የተፈጸመው መቼ ነበር??

*//መልስ//*👇

✍አይሁድ ጌታችንን ከመስቀላቸው በፊት ነው፤ ጌታችን በመዋዕለ ሥጋዌው ከልጅነቱ ጀምሮ የሚለብሳት ከራሱ እስከ እግሩ ወጥ የሆነች ልብስ ነበረች፤ እርሱ በሥጋ ሲያድግ ልብሱም በተአምር ትረዝም ነበር።ዳዊት ትንቢት  የተነበየላትና አይሁድ እጣ የተጣጣሉት በዚህች ልብስ ላይ ነው።

↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣4⃣✍የጻድቃን መታሰቢያው እስከመቼ ነው?? ጥቅሙስ ምንድነድ??

*//መልስ//*👇

✍አባት ዝክረ ቅዱሳን ይሄሉ ለዓለም" የጻድቃን መታሰቢያ ለዘለዓለም ነው"  ሲል ልጅ ደግሞ "በረከት በጻድቃን ራስ ላይ ነው፤ የጻድቃን መታሰቢያ ለበረከት ነው" ይላል። መ.ዝ[111፥6] ምሳ[10፥7]

↪ጥ.ተራ.(ቁ)1⃣5⃣ሄሮድስ  ያስፈጃቸው ሕፃናት ቁጥር ስንት ናቸው?? ሕፃናቱ እንዲሰበሰቡ ያደረገውስ ምን በምን ዘዴ ነው??

*//መልስ//*👇

✍ብዛታቸው 144,000 ሲሆኑ ምግብና ልብስ እሰጣችኋለሁ ብሎ ነው እንዲሰበሰቡ አድርጓል።

↪ጥ.ተራ(ቁ)1⃣6⃣✍ክብር ይግባውና ጌታችንና መድኃኔታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክ ሆኖ እንደሚወለድ የተነበየው ነብይ ማነው??

*//መልስ//*👇

✍ነቢዩ ኢሳይያስ ሲሆን ትንቢቱም እንዲ ይላል፦ በጨለማ የሚኖር ሕዝብ ታላቅ ብርሀን ወጣለት፤ ህፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰቶናልና ስሙም ድንቅ፤  መካር፣ "ኃያል አምላክ" የሠላም አለቃ የዘላለም አባት ይባላን፤ ኢሳይያስ[9፥6]

↪ጥ. ተራ(ቁ)1⃣7⃣✍እስራኤልን ሊወሩ የመጡ ሶርያዊያን በእስራኤል  ንጉስ እጅ ወደቁ ፤ንጉሡም ልግደላቸውን?. ብሎ ኤልሳዕን ጠየቀው? ኤልሳዕ ምን ብሎ መለሰለት..?

*//መልስ//*👇

✍በሰይፍና በቀስት የማረካቸውን ልትገድል ይገባልን? የሚበሉትና የሚጠጡትን አቅርብላቸውና ወደ ጌታቸው ይሂዱ አለው። 2ኛ ነገሥት [6፥22]

↪ጥ.ተራ(ቁ)1⃣8⃣✍በአንድ ወቅት ንጉሥ ሕዝቅያስ ትሞታለህና ቤትህን አዘጋጅ! የሚል ቃል ሰማ፤ ንጉሥ ሕዝቅያስ ምን፦አደረገ?? ይህን ቃል ወደ ንጉሱ ያመጣለትስ ማን ነበር???
*//መልስ//*👇

✍ሕዝቅያስ ፊቱን ወደ ቤተ መቅደስ አዙሮ ጸለዬ፤ 15 አመትም ተጨመረለት። ይህን መልዕክት ያመጣለት ነቢዩ ኢሳይያስ ነበር። 2ኛ ነገሥት [20፥1]

↪ጥ.ተራ.(ቁ)1⃣9⃣✍በአንድ ወቅት ንጉሥ ኢዮርብአም በእግዚአብሔር ሰው ላይ "የያዙት" ብሎ እጁን አመለከተ፤ .....ይህን ጊዜ የኢዮርብአም እጅ  ምን ሆነ.. ከዚያስ ምን ብሎ ለመነ???.........

*//መልስ//*👇👇

ኢዮርብአም የዘረጋት እጁ ደርቃ ቀረች፤  ለነቢዩ እግዚአብሔርን ለምንልኝ አለው፤ ተፈወሰ። 1ኛ.ነገሥት[13፥4]

↪ጥ.ተራ (ቁ) 2⃣0⃣✍ የዚህን ዜማ ግጥም ትርጉም 👉ማርያም ጎየይኪ እምገጸ ሄሮድስ/፪/
ለአርእዮ/፬/ ተአምረ ግፍዕኪ
*//መልስ//*👇

ትርጉም፡- ማርያም ሆይ የግፍሽን ተአምር ለማሳየት
ከሄሮድስ ፊት ሸሸሽ ፡፡

_ወስብኃት ለእግዚአብሔር_saramareyama.890gmail.com

2017 ኖቬምበር 21, ማክሰኞ

የምዕራፍ ሁለት(የ14ኛ) ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር

https://youtu.be/jvZkoEIE4Zs

*_በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

_ፍፁም የእግዚአብሔር ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን!_

*ይህ የ14ኛ ዙር/የምዕራፍ ሁለት👉 የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ መልስ👇 ።*
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣ ↪ በመስቀሉ ደም ሰላምን አደረገ በሰማያትም  ላሉት እርቅን ሰላምን አደረገላቸው። የሚለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ  ቅዱስ ክፍል ይገኛል ምዕራፍና ቁጥሩስ???

*//መልስ///*👉ወደ ቆላስያስ  [1፥18]

✍ጥያቄ ተራ(ቁ)2⃣↪መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በስራው ምክንያት የተሰጡት ስሞች ስንት ናቸው ማን ማን??


*//መልስ//*👇👇

1ኛ👉ነብይ
2ኛ👉ካህን
3ኛ👉መጥምቅ
4ኛ👉መምህር
5ኛ👉ጻዲቅ
6ኛ👉ሰማዕት
7ኛ👉ሐዋርያ

*የሚሉ ናቸው*👆🏻

✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 3⃣↪ሰባቱ ዓውዶች  የሚባሉት ምን ምን ናቸው???
*//መልስ//*👇

/ሰባቱ ዓውዶች የሚባሉት፦👉 👉ዓውደ እለት በየሰባቱ ቀን የሚመላለሰው

👉ዓውደ ወርኅ በ30 ቀኑ የሚመላለሰው

👉ዓውደ ዓመት በጨረቃ 354 ቀን በፀሐይ በ365 ቀን እንዲሁም በከዋክብት በ364 ቀን የሚመላለስ

👉ዓውደ አበቅቴ በ19 ዓመቱ በ/19 ዓመት አንድ ጊዜ ፀሐይና ጨርቃ ጉዞአቸውን በጋራ የሚጀምሩበት/ ተራክቦየሚያደርጉበት/

👉ዓውደ ጳጉሜ በዐራት ዓመት የሚመላለስ /በዐራት ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜ 6/የሚሆንበት እንዲሁም በ600ዓመት አንድ ጊዜ ጳጉሜ ሰባት ትሆናለች።

👉ዓውደ ማኅተም በ76 ዓመት የሚመላለስ ሲሆን በ76 ዓመት በወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ አበቅቴው ደግሞ በ18 ይሆናል።

👉ዓውደ ቀመር ይህ በ5 ዓመት የሚመላለስ ሥርዓት ነው፤ በዚህ ዓውድ ሁሉ ነገሮች ይገጣጠማሉ።
ኢትዮጵያ በእነዚህ ዐውዶች ዘመን ትቆጥራለች።


✍ጥያቄ ተራ (ቁ) 4⃣↪ከመስከረም 17-25 ያለው ሳምንት ምን በመባል ይታወቃል??


*//መልስ//*👇
ከሰኔ 26-እስከ መስከረም 25 ዘመነ ክረምት እየተባለ የሚጠራ ሲሆን እንዲሁም ከመስከረም 17-25 ስለ ነገረ መስቀሉ የሚነገርበት/የሚሰበክበት፣ የሚ ዘመርበት በመሆኑ ዘመነ መስቀል እየተባለ ይጠራል።

✍ጥያቄ ተራ(ቁ)5⃣↪መስፍን ኢያሱ በሌውያን ካህናትን ታቦተ ጽዮንን አስከትሎ የአንዲት ከተማን ግንብ 7/፯ ጊዜ ሲዞር ያቺ ከተማ በ7/፯ኛው ፈረሰች፣ ይቺ ከተማ ማን ትባላለች??የከተማዋ ስም ትርጉሙስ ምን ማለት ነው??

*//መልስ//*👇
/ኢያሪኮ ስትሆን የኢያሪኮ ሰዎች  ስለሚያመልኩ። ከተማቸውን ኢያሪኮ ብለው ጠሯት፣:ኢያሪኮ ማለት፦ የጨረቃ ከተማ ማለት ጨረቃነው ።

✍ጥያቄ ተራ(ቁ)6⃣↪ የመስፍን ኢያሱ የመጀመሪያ ስሙ ማን ይባላል?? ኢያሱ ብሎ ስም ያወጣለት ማን ነው?? ኢያሱ ማለትስ ምን ማለት ነው???

*//መልስ//*👇

/ የመጀመሪያ ስሙ አውሴ ሲሆን ኢያሱ ብሎ ስም ያወጣለት ነብዩ ሙሴ ነበር፤ ሙሴ ማለት የተወለደ ማለት ሲሆን ኢያሱ ማለት ደግሞ መድኅኒት ማለት ነው። (ዘኀልቁ 13፥16)

✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 7⃣↪መጽሐፍ ቅዱስ 6/፮ መሳፍንት አሉ፤ እነርሱም፦ጎቶንያል፣ናፆድ፣ጌዲዮ፣ ዮፍታሔና ሶምሶም ሲሆኑ ብቸኘዋ ሴት መስፍን ማን ትባላለች????

*//መልስ//👇*

/ዲቦራ ናት፤ ዲቦራ ማለት ንብ ማለት ነው።.


✍ጥያቄ ተራ (ቁ) 8⃣↪እኔ ማን ነኝ ? የመጀመርያ ስሜ አውሴ ነው፤ በወጣትነቴ የግብጽን ባርነት የቀመስኩ፣  የኤርትራ ባሕር ሲከፍል በዓይኔ ያየሁ፣ከካሌብ ጋር ምድረ ርስትን የሰለልኩ፣ ከልጅነቴ ጀምሮ የሙሴ  አገልጋይ የነበርኩ እኔ ማን ነኝ???

*//መልስ//*👇

ኢያሱ ነኝ/ነው።


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 9⃣↪ምድረ ርስት ከንዓንን የወረሱት ሁለቱ ሰዎች ማንና ማን ናቸው??

*//መልስ//*👇

//ኢያሱና ካሌብ//

✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣0⃣↪መስቀል ማለት የቃሉ ትርጉም ምን ማለት ነው???

*//መልስ//*👇

/መስቀል ማለት ሰቀለ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም " የተመሳቀለ መስቀለኛ ማለት ነው።


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣1⃣↪ቅድስት ዕሌኒ የጌታችን መስቀል ለማውጣት ወደ ኢየሩሳሌም በስንት አመተ ምህርት ነው የሄደችው?? ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ የተጠመቀው በስንት አመተ ምህረት ነው???

*//መልስ//*👇

ቅድስት ዕሌኒ ወደ የጌታችን መስቀል ለማውጣት በ327 የሄደች ሲሆን ልጇ ንጉስ ቆስጠንጢኖስ አምኖ የተጠመቀው በ352 ዓ.መ ነው።

✍ጥያቄ ተራ (ቁ) 1⃣2⃣↪እነ ኢያሱ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ዮርዳኖስን ሲሻገሩ ወንዙ ሞልቶ ነበር፤  ይህም የሆነው ከአንድ ተራራ ላይ ከሚቀልጠው የበረዶ ግግር ምክንያት ሲሆን እመቤታችንም ስትወለድ ይህ ተራራ እንደ ችቦ ከሩቅ ያበራ ነበር፤ ይህ ተራራ ስሙ ማን ይባላል???

*//መልስ//*👇
የሊባኖስ ራስ የአርሞንኤም ተራራ ነው።


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣3⃣↪ የሳሙኤል እናት ሐና የወለደችው 6 ልጆችን ብቻ ነው፤ ነገር ግን 1ኛ ሳሙኤል [2፥5]ላይ መካኒቱ 7 ወለደች ብላ የዘመረችው ለምን ይሆን???

*//መልስ//*👇

አንድም ታላቁ ሳሙኤል እንደ ሁለት ልጅ ስለሚቆጠር ነበር ሐና 6 ወልዳ ሳለ መካኒቱ 7 ወለደች ብላ 1ኛ ሳሙ.[ 2፡21] የዘምመረችው።

አንድም በቤተ ክርስቲያን 7 ቁጥር ሙሉ ቁጥር ስለሆነ ሐናም እግዚአብሔር ፍፁም ሙሉ ነገርን ሰጠኝ ስትል መካኒቷ ሐና ሰባት ወለደች አለች።

✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣4⃣↪ልብ አምላክ ቅዱስ ዳዊት 150 መዝሙራትን ሲዘምር ልጁ ሰሎሞን ስንት ምሳሎዎችን ተናገረ??

*//መልስ//*👇

3ሦስት ሽ ምሳሌዎችን ተናገረ። [1ኛ ነገስት 4፥32]


✍ጥያቄ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣↪የሙሴ ተከታይ ኢያሱ ሲሆን የኤልያስ ተከታይ ማን ነው?? የቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር  ጢሞቴዎስ ከሆነ የኤልሳዕ ደቀ መዝሙር ማነው??


*//መልስ//*👇

  የኤልያስ ተከታይ  ኤልሳዕ ሲሆን የኤልሳዕ ደቀ መዝሙር  ግያዝ ነው።


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 1⃣6⃣↪ንጉሥ አክአብ የናቡቴብን ርስት እጅግ ተመኝቶ ሲጠይቀው ናቡቴ ምን ብሎ መለሰለት??

*//መልስ//*👇

የአባቶችን ርስት አልሰጥም አለው፤1ኛ ነገስት.[21፥3.


✍ጥያቄ ተራ(ቁ)1⃣7⃣↪ቅዱስ ዳዊት የመረጣቸው 3/፫ቱ ሌዋዊያን የመዘምራን አለቃ እነማን ናቸው??
*//መልስ//*👇

አሳፍ፣ኤማንና ኤዶታም ናቸው። [1ኛ.ዜና.25፡1]

✍ጥያቄ ተራ(ቁ)1⃣8⃣↪መናፍቃን ቀጥታ ወደ እግዚአብሔር ብቻ ነው መጸለይ ያለብን ይላሉ፤ የኢዮብ ወዳጆች በበደሉ ጊዜ እግዚአብሔር ምን ነበር ያላቸው???

*//መልስ//*👇

እንደ በደላችሁ እንደ አይከፍላችሁ ወደ ባሪያዬ ወደ ኢዮብ ሂዱ፤ እርሱ ስለእናንተ ይጸልያል፤  እኔም ጸሎቱን እሰማለሁ።
.መናፍቃን ቀጥታ ወደ እግዚአብሔር ብቻ ነው የምንፀልየው ሲሉ እግዚአብሔር ግን እንደ በደላችሁ እንዳይከፍላችሁ ወደ ቅዱሳን ሂዱ፤ እነሱ ይጸልያሉ፤ እኔም ጸሎታቸውን እሰማለሁ ይላል። ኢዮብ[42፡8]



✍ጥያቄ ተራ (ቁ)1⃣9⃣↪ ሰው እውቀትን ሲጨምር ኃዘንን ይጨምራል ያለው ንጉሥ ማን ነው???

*//መልስ//*👇

ጠቢቡ ሰሎሞን ነው፤ መጽሐፈ መክብብ[1፡18]


✍ጥያቄ ተራ(ቁ) 2⃣0⃣↪3/፫አመት በኢትዮጵያ በእግሩ የሄደው ነብይ ማን ይባላል??

*//መልስ//* ነብዩ ኢሳይያስ ነው። ኢሳ[20፥3] ላይ ይገኛል።

ወስብኃት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ ሁለት(13ኛ)ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ


*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!!የእግዝአብሔር ፍፁም ሰላም ይብዛላችሁ ይብዛልን_

*ሦስተኛ(3ኛ) ዙር የጠቅላል እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር* _እንደሚከተለው ነው_

_ጥ ተራ (ቁ) 1⃣"አንቺ ሴት ከአንች ጋር ምን አለኝ"? በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ ሴት የሚለው ቃል....ነው??

ሀ/ በእስራኤላውያን የትሕትና አነጋገር ነው።

ለ/ የቁጣ አነጋገር ነው።

ሐ/ ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ ማለት ነው።

መ/ ሀ እና ሐ መልስ ነው።

*//መልስ//*

መ/ ሀ እና ሐ መልስ ናቸው።
1ኛ👉 በእስራኤላውያን የትሕትና አነጋገግ ነው።

2ኛ 👉አጥንትሽ ካጥንቴ ሥጋሽ ከስጋዬ ማለት ነው። ዘፍ 2፥23 ላይ ማየት ይላልቻ።።

 ጌታችንም  ድንግል ማርያምን አንቺ ሴት ማለቱ ከሥጋሽ ስጋን ከነፍስሽ ነፍስን ነስቼ አካልሽን አካል ባህሪሽን ባህሪ አድርጌ ሰው ሆኛለሁና ማለቱን የሚያመለክ የአክብሮትና የፍቅር ሐይለ ቃል እንደሆነ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን  ያስተምራሉ።

✅ጥ ተራ (ቁ) 2⃣ሃይማኖት ማለት ምን ማለት ነው? ሃይማኖት ከማን የተሰጠ ሥጦታ ነው??

*//መልስ/*

“ሃይማኖት ወይም እምነት” አምነ አመነ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ዘር ወይም ስም፤ ፤ ሲሆን ትርጉሙም አንድን እውነት መቀበል፤ በአንድ ክፍል ላይ ተስፋ ማድረግ ወዘተ ማለት ነው።
ስለ እምነት ወይም ሃይማኖት ምሥጢራዊ ትርጉም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚከተለው በግልጽ አስቀምጦታል፡
👉 “እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው” ዕብ.11፡1 በዚህ ቃል መሠረት እምነት ተስፋ የምናደርገው ነገር ሁሉ እርግጠኛ ስለመሆኑ፤ የማናየውንም ነገር የሚተርክ የሚያስተምር ነው።

በመቀጠልም ሐዋርያው “ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደተዘጋጁ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን” ዕብ.11፡3 ይላል ። በመሆኑም እምነት ስለፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር ያለውን
እውነት እንዲሁም ከእርሱ ዘንድ ያለውን ተስፋችንን
የሚያስረዳ፤ የሚያረጋግጥልን እውነት፤ ሁሉንም የምናይበት የልብ መነጽር ነው። ስለዚህ መንፈሳዊውን  ለማወቅና የአምላክን  ለመሳተፍ ማመን እጅግ ተፈላጊና መሠረታዊ ነገር ወይም ምሥጢር ነው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 3⃣ቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ  ኢትዮጵያ ከሚለው መጠርያ ስሟ ሌላ ማን ማን እየተባለች ትጠራ ነበር??

*//መልስ//*
1ኛ👉የካም ልጅ ፉጥ በኢትዮጵያ ምድር ስለሚኖር #ፉጥ ተብላለች

2ኛ👉 ቶኔቶር ትባል ነበር ቶኔቶር ማለት ሀገረ እግዚአብሄር ማለት ነው።

 3ኛ👉ሊቀ ነብያት ሙሴ ኢትዮጵያን የኩሽ ምድር እያለ ይጠራት ነበር

4ኛ👉ኢትዮጲስ ተብላለች

5ኛ👉ሳባ የተባለ የኩሽ ልጅ ይኖርባት ስለነበር የሳባ ምድር ትባል ነበር

6ኛ👉ሰብታ ወይም አቢስ ይኖርባባት ስለነበር አቢሲኒያ ተብላለች

✅ጥ ተራ (ቁ) 4⃣ የአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ሀገረ ሥብከታቸው የት የት እንደሆነ አስረዳ/ጂ??

*//መልሱን በድምፅ /ከቭዲዮመስዋት/ኦ/ አዳምጡ*

✅ ጥ ተራ (ቁ) 5⃣ በቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ የኦሪት  የሚሰዋባቸው አብያተ ክርስቲያናትን ጥቀስ/ጥቀሽ??

*መልስ*

 (1ኛ)መርጡ ለማርያም

 (2ኛ)ተድባባ ማርያም

(3ኛ)አክሱም ፅዮን

 (4ኛ)ብርብር ማርያም

 (5ኛ)ጣና ቂርቆስ ናቸው

✅ጥ ተራ ( ቁ) 6⃣የጌታችን የመድኃኒታችን 9ኙ ባዕላት የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ/፦*

1ኛ👉�ፅንሠት
2ኛ 👉�ልደት
3ኛ👉�ጥምቀት
4ኛ👉� ደብረ ታቦር
5ኛ👉� ሆሳህና
6ኛ👉� ስቅለት
7ኛ👉� ትንሳኤ
8ኛ👉� እርገት.ክርስቲያን
9ኛ👉�ጲራቅሊጦስ ናቸው።

✅ጥ ተራ ( ቁ) 7⃣ቤተ  ክርስቲንያን ስንት ክፍሎች አሏት?? ምን ምን??

*//መልስ//*

1ኛ 👉መቅደስ
2ኛ 👉ቅድስት
3ኛ👉 ቅኔ ማህሌት

✅ ጥ ተራ (ቁ) 8⃣ ሰባቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የተናራቸው ነገሮች(ሰባቱ አፅረሃ መስቀል የሚባሉት ምን ምን ናቸው??

*//መልስ/*👇

1,,, ኤሉሄ ኤሉሄ ለማ ሰብቅታኒ /አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ ,,,, ማቴዎስ 27፥40

2,,,አባት ሆይ የሚያደርገትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ....ሉቃስ 23፥39..

3,,, ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ። ሉቃስ 23፥39

4,,, አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ። ሉቃስ 23፥46...

5,,, እነሆ ልጅሽ...እነሆ እናትህ....ዮሐንስ 19፥26...

6,,,ተጠማሁ፣...ዮሐንስ እና፥28...

7,,,ተፈፀመ...ዮሐንስ 19፥30....

✅ጥ ተራ (ቁ) 9⃣ የቤተ ክርስቲያን አስራ አራቱ/14/ ቅዳሴዎች ምን ምን ናቸው???

*//መልስ//፦*

1ኛ፦ ቅዳሴ ሐዋርያት
2ኛ፦ ቅዳሴ እግዚእ.
3ኛ፦ ቅዳሴ ማርያም
4ኛ፦ ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጎድ
5ኛ፦ ቅዳሴ ሰለስቱ
6ኛ፦ ቅዳሴ አትናቴዎስ
7ኛ፦ ቅዳሴ ባስልዮስ
8ኛ፦ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
9ኛ፦ ቅዳሴ ኤጲፋንዮስዲዮስቆሮስ

10ኛ፦ ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ
11ኛ፦ ቅዳሴ ቄርሎስ
12ኛ፦ ቅዳሴ ያዕቆብ
13፦ ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ
14ኛ፦ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ ካልዕ

✅ጥ ተራ (ቁ) 🔟 ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእለተ ሆሳዕና  በአህያ ላይ ለምን ተቀመጠ? ለምንስ በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??

*//መልስ//*👇
👉�ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይልበሽ። አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልእል በይ እነሆ ንጉስሽ ጻድቅና አዳኝ ነው። ትሑትም ሆኖ በአህያም በአህያይቱም ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመልጣ (ዘካ 9፥9) እንዲል።

•ተንኮለኛ ናት ለጠላትዋም ፈረስ አውድቃ ረግጣ ትገድላለች
•ረጋ ብላ መሄ አችልም ትቸኩላለች
•ልትወጣባት ስትልም ታስቸግራለች አትመችም ተነጣጥረህ ነው የምትወጣባት
•ጌታ የወደደውና በትንአምላክ አህያን መረጠ፡፡

በአህያ መቀመጡ
እደተገለጸው•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝብለው ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ መእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ  ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ፤እኛ በትእቢት ተይዘን ነው እንጂ በየዋህነት ብንመላለስ እሱ ያድርብን ነበር፡፡ እኛ የእግዚአብሔር ማደርያ ነንና፡፡

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣1⃣ጌታችን በመጣ ጊዜ የምንጠየቃቸው "6"ቃላተ ወንጌል የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ//*
 👉ተርቤ አላበላችሁኝምምዕራፍ

👉ተጠምቸ አላጠጣችሁኝም

👉 የማቴዎስ ወንጌል  25፥33 -46 ላይሙሉውን መመልከት ይቻላል።

✅ ጥ ተራ (ቁ)1⃣2⃣ በ186 ዓ.ም በፍቼ የተወለዱና ከኢትዮጵያ የመጀምርያ አራት ጳጳሳት አንዱና የምሥራቅ ኢትዮጵያ ጳጳስ የነበሩት። በኋላም ፋሺስት ኢጣሊያ በ1928 ዓ.ም በኢትዮያ ላይ የግፍ ጦርነት ባነሳ ጊዜ እምቢ ለሃገሬ ለሃይማኖቴ በማለታቸው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በፋሽስት ኢጣሊያን ሰማዕትነት የተቀበሉት ታላቅ አባት ማን ይባላሉ??

*//መልስ//* 👇

ታሪካቸውን የማንዘነጋው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣3⃣ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "በኩር" የሚባልበት ምክንያት

ሀ/የአብ አንድያ ልጁ ስለሆነ

ለ/ በእስራኤላውያን መጀመርያ ማኅፀን የሚከፍት ልጅ በኩር ስለሚባል

ሐ/ ሞት የማይገዛው ትንሣኤን ለመነሣት እርሱ የመጀመርያ ስለሆነ

መ/ ሁሉም መልስ ነው።

*// መልስ//*

መ/ ሁሉም

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣4⃣እመቤታችን በስደቷ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ረዘም ላለ ጊዜ ያረፈችበት ቦታ__ይባላል??

*//መልስ//*

በጣና ደሴት ሦስት ወር ከአስር(10)ቀን ቆይታለች

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣የቃል ኪዳኑ ታቦት ከማይነቅዝ እንጨት የተሰራና ከውስጥም ከውጭም  በወርቅ የተለበተ መሆኑን፤ የሚያስረዳን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል የትኛው ነው??

*//መልስ//*

ዘጸ.25፥1-22 ላይ ይነግረናል።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣6⃣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያትን ትምህርት 81 የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የምትቀበል ስትሆን ሦስቱን  አብያተ ክርስቲያን ጉባኤያትንም ትቀበላለች። የምትቀበላቸውን የጉባኤያትን ስም ጥቀስ/ጥቀሽ

*//መልስ//*👇
ኒቂያ  ጉባኤ ፣ ቁስጥንንጥንያና አፌሶን ናቸው የነዚህን ጉባኤያት ውሳኔዎቻቸውን ትቀበላለች። ሌሎች ጉባኤዎችን አትቀበልም።

✅1⃣7⃣የሙሴን ሕግ በብዙ ጥንቃቄ እንተረጉማለን የሚሉና ሰውም ሕጉን እንዳይተላለፍ በማለት የራሳቸውን ትእዛዝና ሥርዓት ያወጡ በዘመነ ካህናት ጊዜ የነበሩ የቤተ  ክርስቲያን ጠላቶች ምን ተብለው ይጠራሉ??

ሀ/ ፈሪሳውያን

ለ/ ሰዲቃውያን

/ ኤሲያውያን

መ/ አይታወቁም

*//መልስ//*

ሀ/ ፈሪሳውያን የሐዋርያት 👉 ሥራ 15÷5 ላይ ይገኛል

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣8⃣አስራ ሦስቱ/ 13/ የጌታችን ህማማተ መስቀል የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ//*

13ቱ ሕማማተ መስቀል

1ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
2ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
3ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይመውደቅ)
4ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድመረገጥ)
5ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋርመላተም)
6ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
7ኛ. ተቀሰፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
8ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
9ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
10ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
11ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
12ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይመሰቀል)
13ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትንመጠጣት)ጊዜ

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣9⃣በሐዋርያት ጊዜ  የነበሩ የመጀመርያዎቹ  መናፍቃን ምን ተብለው ይጠራሉ??

ሀ/ ግንስቲኮች

ለ/ ቢጽ ሐሳውያን

/ አርዮሳውያን

መ/ ሁሉም

*//መልስ//*
*ለ/*👉ቢጽ ሐሳውያን ሐሰተኛ ወንድሞች ይባሉ ነበር። እነዚህም መናፍቃን ከአይሁድ ወገን ክርስትናን በመቀበል ካመኑና ከተጠመቁ በኋላ ተመልሰው ወደ አይሁድ ሃይማኖት ያዘነበሉ ናቸው።

✅ ጥ ተራ (ቁ) 2⃣0⃣ የግዝት በዓላት የማባሉት ስንት ናቸው?? ምን ምን ?

*//መልስ//*👉� አምስት (5) ናቸው
 1ኛ👉� የወልድ በዓል ወር በገባ በ29 ቀን
2ኛ👉�የመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓል ወር በገባ በ21
3ኛ👉�የመላአኩ ቅዱስ ሚካኤል በዓል ወር በገባ በ12 ቀን
4ኛ👉�እለተ ቅዳሚት ሰንበት
5ኛ👉�እለተ እሁድ ሠንበት ክርስቲያስቲያን ናቸው።

_ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አረሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነኝ_
.
_ወስብሐት ለእግዚአብሔር_


 aramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ ሁለት(12ኛ) ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የማጣርያ ጥያቄና መልስ

*_✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

_✅የምዕራፍ ሁለት/12ኛ/ ዙር  የማጣርያ የሽልማት የጠቅላላ እውቀት የጥያቄና መልስ ውድድር እንደ ሚከተለው ነው_

*_✍ምድብ አንድ የቅድስት አርሴማ ልጆች👇_*
 *ጥያቄ*

_1⃣➡✍ዲዮቅልጥያኖስ ለጣፆት አንሰግድም ብለው እንቢ ባሉ ክርስቲያኖች ላይ ያወጀው አዋጅ ምን የሚል ነበር ቢያንስ ሦስቱን/3/ጥቀስ/ ጥቀሽ_

*//መልስ//*✍

ሀ. አቢያተ ክርስቲያን እንዲደመሰሱ

ለ. ክርስቲያኖች እርስ በእርሳቸው እንዳይገናኙ

ሐ. ስለ ክርስትና ሃይማኖት የሚናገር መጻፍት ሁሉ እንዲቃጠል

መ. የቤተ ክርስቲያን ንብረት የሆነ ሁሉ እንዲወረስ

ሠ. ማንኛውም የሮማ ዜጋ ክርስቲያን ከሆነ ከመንግስት ስራ እንዲወገድ

ረ. ባሮች ክርስትናን ከተቀበሉ ነፃ የመውጣት መብት የላቸውም

ሰ. ክርስቲያን ምንም ሕጋዊ ምክንያት ቢኖራቸውም በማንም ላይ ክስ መመስረትና ስለ መብታቸው መከራከር አይችሉም የሚል ነበር።

_2⃣➡✍ የዓለም አብያተ ክርስቲያን አንድነት ንቅናቄ ማህበር መቼ ተመሠረተ??_

*//መልስ//*✍ በ20/፳ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው።

*_✍ምድብ ሁለት የድንግል ማርያም የአስራት ልጆች_*👇

   *መልስ*

_1⃣➡✍ቆስጠንጢኖስ ለቤተክርስቲያን ከሰጣቸው መብቶች ውስጥ ቢያንስ ሦስቱን ጥቀስ/ጥቀሽ??_

*//መልስ//*✍
ሀ. ቤተ ክርስቲያን ከግብር ነፃ ናት

ለ. ከመንግስት ገቢ ለቤተክርስቲያን ድርሻ አላት

ሐ. ዕለተ እሁድ/ ሰንበት/ በንጉሠ ነገሥቱ ግዛት ውስጥ ሥራ እንዳይሰራባት አወጀ

መ.ከክርስቲያን ወገን በሕይወትንም ሆነ በሞት ንብረቱን ለቤተ ክርስቲያን አወርሳለሁ የሚል ምእመን ካለ ቤተ ክርስቲያን ኑዛዜ የመቀበል፣ ውርስ የመውረስ መብት አላት

ሠ. በክርስቲያኖች መካከል ለሚፈጠሩ አንዳንድ አለመግባባቶች ቢኖሩ ለኤጲስ ቆጶስ የዳኝነት ሥልጣን ሰጥቷል።

_2⃣➡✍የመላው አፍሪካ አብያተ ክርስቲያን  ጽ/ቤት የት ይገኛል ??_

*//መልስ//*  _✍በናይሮቢ ኬንያ ይገኛል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዚህ ጊባኤ መሥራችና ቋሚ አባል ናት።_

*_✍ምድብ ሦስት እምነት በስደት የድንግል ማርያም ልጆች_*👇

         *ጥያቄ*

_1⃣➡✍ሐዋርያውያን አበው ከሚባሉት መካከል ሦስቱን ጥቀስ/ጥቀሽ_

*//መልስ//*በርናባስ፣ -ሄርማስ፣ ቀለሚንጦስ ዘሮም፣ ፓሊካርፐስ፣ ፓፒያስና አግናጥዮስ(ምጥው ለአንበሳ) ተጠቃሾች ናቸው።

_2⃣➡✍የአለም አብያተ ክርስቲያን አንድነት ጉባኤ ጽ/ቤት የት ይገኛል??_

*//መልስ//* _✍ በሃንጋሪ ፕራግ በተባለ ከተማ ነው። ጉባኤው በየጊዜው እየተሰበሰበ ቤተ ክርስቲያን ስለ ዓለም ሰላምና ስለ ሰው ልጅ ደህንነት ያላትን አቋም ያሳውቃል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዚህ ጉባኤ ቋሚ አባል ናት።_

*_ምድብ አራት ከተለያዩ ማህበር የመጡ ልጆች_*👇 *ጥያቄ*.

_1⃣➡✍የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ምንጮች ከምንላቸው መካከል ሦስቱን ጥቀስ/ጥቀሽ???_

*//መልስ//* 👉

1ኛ👉የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት

2ኛ👉የሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት

3ኛ👉በየጊዜው የተደረጉትን የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎችንና ውሳኔዎቻቸው

4ኛ👉የቤተ ክርስቲያን አባቶች የፃፏቸው የታሪክ  መጽሐፍቶች.

5ኛ👉በየጊዜው የሚገኘት የክርስቲያኖች መቃብራት፣ መቅደሶች፣ ሥዕሎች ወ.ዘተ

6ኛ👉መንፈሳውያንም ሆኑ ዓለማውያን ነገስታት በቤተ ክርስቲያን ላይ የደነገጓቸው ልዩ ልዩ ሕግጋት ወ.ዘተ ታሪኮች ናቸው።

2⃣➡✍ቅዱሳን ሐዋርያት እስከ  መጨረሻ በመጽናት ለክርስቶስ ምስክር ለመሆናቸው ዋና ዋና ምክንያቶች ምን ምን ናቸው???_

*//መልስ//*✍

1ኛ👉በአይናቸው አይተውታልና

2ኛ👉በእጃቸው ዳሰውታልና

3ኛ👉ትምህርቱን በጆሮአቸው ሰምተውታልና/ዮሐንስ 1፥2/

4ኛ👉በእርሱ ተልከዋልና/ማቴ 10፥6-4/

5ኛ👉ከትንሣኤው በኋላ አይተውታልና/ዮሐ. 21/

6ኛ👉በስሙ ተአምራት ሲፈጽሙ ኖረዋልና/2ኛ.ቆሮ. 12፥12/

*ውድ ተወዳዳሪዎች ሆይ የጥቄቃው ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አርሙኝ*

*ወስብኃት ለእግዚአብሔር*saramareyama.890@gamail.com

የምዕራፍ 2ት(11ኛ)ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

*_ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

*_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን አላችሁ??*_

*_የምዕራፍ ሁለት (የ11ኛ) ዙር የቃል ጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል👇_*

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣ንስጥሮስ ወላዲተ ሰብእ ናት ብሎ በእመቤታችን ላይ የተናገረውን የክርደት ትምህርት የገለጠው ቅዱስ አባት ማን ይባላል??

*//መልስ//*👉ቅዱስ ቄርሎስ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 2⃣ አርዮስ እና ተከታዮቹ የተወገዙበት ጉባኤ ___ነው??

ሀ/ ጉባኤ ኒቅያ
ለ/ ጉባኤ ኤፌሶን
ሐ/ ጉባኤ ቁስጥንጥንያ
መ/ ሁሉም

*// መልስ//*👉መ ሁሉም ነው መልሱ 1ኛ👉 በ325 ዓ.ም የኒቂያ ጉባዬ ፦  አሪዮስ የተወገዘበተ

2ኛ👉381 ዓ.ም ቁስጥንጥንያ፦ የዚህ ጉባየ አላማ የነበረው የመንፈስ ቅዱስ ፍፁን አምላክነት ለካደው ለመቅድንዮስ ምላሽ ለመስጠት ነበር።

3ኛ👉431 ዓ.ም ኤፌሶን ጉባዬ ፦ ክርስቶስ ሁለት አካል ሁለት ባህሪይ የሚለውን የሐሰት ትምህረት በመቃወም ቅዱስ ቄርሎስ። የረታበት ጉባኤ ናቸው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 3⃣ ለመናፍቃን መልስ ከሰጡ ታላላቅ ቅዱሳን አባቶች መካከል ሦስቱን ጥቀስ/ ጥቀሽ??

*//መልስ//*👉አባ አትናቴዎስ፣ቅዱስ ቄርሎስ፣ ጎርጎርዮስ ዘእንዚዙ/ነባቤ መለኮት/፣
✍ጥ ተራ(ቁ)4⃣ ከኤፌሶን ጉባኤ በኋላ የተደረጉትን ጉባኤያት አምስቱ/5ቱ/ እኅት የምስራቅ አብያተ ክርስቲያናት እንዴት ያዩታል??

ሀ/ አይቀበሉትም
 ለ/ ይቀበሉታል
 ሐ/ እንደሁኔታው ይለያያል
መ/ ሁሉም

*//መልስ//*👉ሀ) አይቀበሉትም።

✍ጥ ተራ(ቁ) 5⃣በብሉይ ኪዳን ዘመን የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ያልሆነው የትኛው ነው??

ሀ/ የኖህ መርከብ
 ለ/ የአሳ ማጥመጃ መረብ ሐ/ ደብረ ሲና
መ/ የሙሴ ደብተራ ድንኳን

*//መልስ//*👉ለ) የአሳ ማጥመጃ መረብ

✍ጥ ተራ(ቁ)6⃣በሐዲስ ጌታችን ካስተማራቸው ትምህርቶች ውስጥ ስለጥቀስ ቤተክርስቲያን በምሳሌነት ከሚጠቀሱት መካከል ቢያንስ ሦስቱን /ጥቀሽ??

*//መልስ//*👉የአሳ ማጥመጃ መረብ/ማቴ. 13፥47/

👉ታላቅ የስንዴ አዝመራ /ማቴ.13፥24/

👉የከበረ ዕንቁ/ማቴ. 13፥45/

👉የሰናፍጭ ቅንጣት /ማቴ. 13፥31፣/ሉቃ. 13፥18/

👉የሠርግ ቤት/ ማቴ. 22፥1-10፣ዮሐ. 2፥1/

👉ሙሽራ /ኤፌ. 5፥21-33፣ራእ.21፥9-14 ወ.ዘተ ናቸው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 7⃣እንደ ቤተክርስቲያን ስዕራት   መሰረት ስንት አይነት ስግደት አለ??

ስግደት በ 3 ይከፈላል
1. የአምልኮ (የባህርይ ስግደት )ይህ ስግደት ለፍጡር ሳይሆን ለፈጣሪ ለአምላካችን ለእግዚአብሔር ብቻ የሚሰገደው ስግደት ነው፡፡
2.የፀጋ ስግደት ፡-ይህ ስግደት ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ለቅዱሳን መላእክት ፡ ለጻድቃን ሰማዕታትን የምንሰግደው ስግደት ነው፡፡
3.የአክብሮት ስግደት ፡-ይህ ደግሞ እርሰበርሳችን የምንለዋወጠው አክብሮታዊ ሰላምታ ነው፡፡
ከነዚ ሶስቱ የስግደት ዓይነቶች ቀጥለን የምንመለከተው በሁለተኛ ተራ ቁጥር ላይ የገለጥነውን የጸጋ ስግደት ነው፡፡

✍ጥ ተራ (ቁ)8⃣ የአራቱ/4ቱ/ አበይት ነብያት የትንቢት መጽሐፎች ስንት ምዕራፍ ቁጥር  አሏቸው??

*//መልስ*👉1ኛ 👉የነብዩ ኢሳያስ 66 ምዕራፍ አለው።

2ኛ 👉ነብዩ ኤርሚያስ ነው 52 ምዕራፎች አሉት።

3ኛ👉ሕዝቅኤል 48 ምዕራፎች አሉት።

4ኛ👉ነብዩ ዳንኤል ነው 12 ምዕራፎች አሉት።

✍ጥ ተራ(ቁ) 9⃣ኢየሱስ ክርስቶስን አማኑኤል ብለው ይጠሩት የነበሩት እነማን ናቸው??

*// መልስ//* 👉ነብያትና እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም ናች።
ትንቢተ ኢሳይያስ

7:14  ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥  ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።
አንገትም
8:8  እየጐረፈም ወደ ይሁዳ ይገባል፤ ወንድእያጥለቀለቀም ያልፋል፥ እስከ  ይደርሳል፤ አማኑኤል ሆይ፥ የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች።

የማቴዎስ ወንጌል

1:23  እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥  አማኑኤልይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ስሙንምትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣0⃣ቅዱስ ዮሐንስ ለምን አፈወርቅ ተባለ በምንስ ??

*//መልስ//*  ◆◊◆ “አፈወርቅ” የመባሉም ታሪክ እንዲህ ነው:- አንድ ዕለት
ንስጥሮስ የቁስጥንጥንያ ፓትሪያርክ ሆኖ በተሾመበት ዘመን አንዲት
በሴቶች ከሚደርሰው ግዳጅ ( ከወር አበባዋ) ያልፀዳች ሴት ስለ
ቤተክርስቲያንና ስለ ስጋወ ደሙ ፍቅር ስጋወ ደሙን ልትቀበል ወደ
ካህናት ተጠጋች፡፡ በዚህ ጊዜ መንፈስ ቅዱስ እንደ ጥላ ሲሽሽ ታየ፤
ይህንንም የተመለከተው ንስጥሮስ ወደሷ ቀርቦ “እንዲህ መንፈስቅዱስ
የሽሽው ምን ብትሰሪ ነው?” አላት፡፡ እርሷም “ ስለ ቤተክርስቲያን ፍቅር
ከግዳጄ ሳልነፃ ወደ ስጋወ ደሙ በመቅረቤ ነው” አለች፡፡ በዚህ ጊዜ
ንስጥሮስ ተቆጣ በፊት ያጠናው የነበረውን የምንፍቅና ትምህርት
አምጥቶ ለህዝቡ ሁሉ “ እግዚአብሄር እንዲህ መንፈስቅዱስን
ከሚያሳዝን የሴት ማህፀን ወጣ የሚል የተረገመ ይሁን” አለ፡፡ በዚህም
የክርስቶስን ፍፁም ሰው ፍፁም አምላክነት ሻረ፡፡ ከማርያም የተወለደው
እግዚአብሄር አይደለም በማለት ፍፁም ክህደትን አስተማረ፡፡ ያቺንም
ሴት እርቃኗን ቁልቁል አሰቅሎ ሁሉም ህዝብ እየመጣ በአንቀፀ ስጋዋ
ላይ ምራቁን እንዲተፋ እያዘዘ የማርያምን ወላዲት አምላክነት እንዲሽሩ
አዘዘ፡፡ ክርስቶስንም ከነቢያት አንዱ ነው አለ፡፡ በዚህ ወቅት አንድ ካህን
የነበረ ስሙ ዮሃንስ የሚባል ወደ ሴቷ ቀረበና “እኔስ እግዚአብሄር ወልድ
እንደ ህፃናት ስርአት በማህፀን ተወለደ ብየ አምናለሁ” በማለት የሴቲቷን
አንቀፀ ስጋ የወር አበባ ያላት መሆኗን እንኳን ሳይፀየፍ ሳመ፡፡ በዚህ ጊዜ
በቤተክርስቲያን የነበረች ስእለ ማርያም አንደበት አውጥታ “አፈወርቅ”
ብላ ጠራችው፡፡
ዳግመኛ በከበረ ስዕሏ ተገልፃ " ሰናይ ተናገርከ ዮሐንስ አፈወርቅ
ዮሐንስ ልሳነወርቅ " ብላ አመስግነዋለች፡፡ አንዳንድ ጹሁፎችም
ከሚያስተምረው የትምህርቱ ጣዕም የተነሣ “አፈወርቅ፣ ጥዑመ ልሳን”
ተብሏል የሚሉ አሉ፡፡
12

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣1⃣በአዲስ  ኪዳን 28 ምዕራፍ ያለው መጽሐፍ የትኛው ነው??

*//መልስ//*👉የሐዋርያት ሥራና የማቴዎስ ወንጌል።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣2⃣ተክለ ሃይማኖት ማለት ምን  ነው?? የተክለ ሃይማኖት እናትና አባት ማን እና ማን  ይባላሉ የትውልድ ሃገራቸውስ???

*//መልስ//*👉ተክለ ሃይማኖት ማለት፦ ተክለ አብ ተክለ ወልድ ተክለ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው።  አባቱ ጸጋ ዘአብ እናታቸው እግዚእኅረያ ይባላሉ። ሀገራቸው ቡልጋ ጽላልሽ (ዞረሬ) ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣3⃣የኢየሩሳሌምን የመጀመርያውን  መቅደስ የሰራው ማን ነው?? ያፈረሰውስ ማን ነው??

*//መልስ//*👉የርራው ጠቢቡ/ ንጉስ ሰሎሞን። 👉ያፈረሰው ናቡከደነጾር ነው ።

✍ጥ ተራ (ቁ)1⃣1⃣⃣ከ7ቱ የጸሌት ጊዚያት መካከል የ6ሰዓትና የ3ሦስት ሰዓት ጸሎት ምንን አስመልክቶ ነው??

ጸሎት  ”የስድስት ”  የሚባል ሲሆን። በቀትርከፀሀይ ሙቀት የተነሳ ሰውነት ሲዝልሃሳብ (አእምሮ) ሲበተን  ያንን የመናፍስት ጦርለመከላከል በተለይም ጊዘው

አጋንንትስለሚሰለጥኑ-ሄኖክ ቤተመቅደስ ያጠነበት- ይልቁንም ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስክርቶ ዓለምን ለማዳን ሲልበቀራንዮ አደባባይ  ሠዓትስለሆነ ህማማተ መስቀሉን እያሰብንየምንጸልየው ጸሎት ነው።    ሁለተኛዉ ጸሎት ደግሞ ”ዳንኤል የሦስት ሠዓት” ጸሎት የሚባል ሲሆን ይህን  ስንጸልይ፦ የሁሉ እናት ሄዋንየተፈጠረችበት ሠዓት፣ ነብዩ  በምርኮ በሚኖርበት በባቢጸሎትሎን ሳለበእየሩሳሌም አቅጣጫ ያለዉንመስኮቱን ከፍቶ የጸለየበት ሠዓት፣እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያ ከመላአኩ ከቅዱስ ገብርኤል ሠማያዊ ብስራት የሰማችበት ሠዓት፣ጌታችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስክርስቶስ በጲላጦስ ፊት የተገረፈበ ሰዓት ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣እያሱ ጽሐይን ያቆመበት ቦታ ማን  ይባላል??

*//መልስ//*👉በግብፅ በገባኦት ሥፍራ  ላይ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣6⃣ቅዱስ ያሬድ ከጸረ-አርያም በወረደ ጊዜ ለመጀመርያ ያዜመው ዜማ ምን ይባላል??

*//መልስ//*ቅዱስ ያሬድ የመጀመረያ ዜማው አራራይ ዜማ ሲሆን ያዜመውም ሃሌ ሉያ ለአብ፣ ሃሌ ሉያ ለወልድ፣ ሃሌ ሉያ ወመንፈስ ቅዱስ  ቀዳሚሃ ለጽዮን ሰማየ ሣረረ ወበዳግም አርአዮ ለሙሴ ዘከመ ይግብር  ግብራ ለደብተራ/ ይህም ማለት አለም ሳይፈጠር ለነበረና አለምን አሳልፎ ለዘላለም ለሚኖር ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድም ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፣ ከጽዮን አስቀድሞ ሰማይን ፈጠረ፤ ዳግመኛም ደብተራ ኦሪትን እንዴት አድርጎ መሥራት እንዳለበት ለሙሴ አሳየው ማለት ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣7⃣ደዊይ በስንት ይከፈላል??

*//መልስ//* ደዌይ በአራት ይከፈላል፦

👉1ኛ 👉ደዌይ ዘሐሰት ኢዮብ የደረደበት መከራ (ኢዮብ 2፥10)

2ኛ👉ደዌይ ዘመቅሰፍት ለምሳሌ ሳኦልና ሄሮድስ የደረሰባቸው የሞት መቅዘፍት
ይባላል
3ኛ👉ደዌይ ዘምጽ ጢሞጢዎስ እና ጳውሎስ የደረሰባቸው ህመም ደዌይ ዘምጽ

4ኛ👉ደዌይ ዘኃጢአት ይህ ማለት እነ መጻጉ 38 አመት አልጋላይ የቆዩት ማለት ነው

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣8⃣ቄርሜሎስ ማለት ምን ማለት ነው??

*//መልስ//*ቄርሜሎስ ማለት ፍሬአማ ተራራ ማለት ነው
በሌላ አነጋገር ደግሞ ይቺ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ፍሬ የምናፈራበት ማለት ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣9⃣አብርሀምና ሎጥ ያላቸውን ዝምድና ግለፅ/ ግለጭ???

*//መልስ//*👉
የአባታችን አብርሀም የወንድሙ የሃራን  ልጅ ነው። ዘፍ 11፥27 ይገኛል።

✍ጥ ተራ (ቁ) 2⃣0⃣በኖህ ዘመን ሠዎች በንፍሮ ውሃ ለመጥፋታቸው ምክንያት የሆነው ምንድነው???

*//መልስ//*👉 በኖህ ዘመን ሠዎች በንፍሮ ውሃ ለመጥፋታቸው ምክንያት የሆነው የእግዚአብሔር ትዛዝ ዘንግተው በኃጢአት ስለረከሱ ነው።
ዘፍ 6፥11

*_ማጠቃለያ መልስ ይህንን ይመስላል_*

*ወስብኃት ለእግዚአብሔር*saramareyama.890@gmail.com

የ10ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ


https://youtu.be/bxtabq_vFB4  👆👆   *_በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

*_ፍፁም የእግዚአብሔር ሰላም የእናታችን የድንግል ማርያም ምልጃና ጥበቃ ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን_*

*እነሆ የአስረኛ (10)ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል  ጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ መልስ 👇👀*
////////👇👇/////

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣ሰኔ 30 የሚከበረው  የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ክብረ በዓል ምንንን አስመልክቶ ነው??

*//መልስ//*

👉ሰኔ 30 ልደቱ ለዮሐንስ መጥምቀ መለኮት

በዚህች ቀን የጌታን መንገድ ጠራጊው፤ ሐዋርያው፤ ነብዩ ሰማዕቱ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ቀኑ ነው፤ መስከረም 2 አንገቱ የተቆረጠበት ነው ሚያዚያ 15 እረፍቱ ነው፤ አንገቱ ከተቆረጠ በኋላ የተቆረጠች አንገቱ ክንፍ አውጥታ ለ15 ዓመት በሳውዲ አረቢያና አካባቢው ወንጌልን ሰብካለች፤ የካቲት 30 ቀን የዮሐንስ ራስ የተገለጸችበት ቀን ነው። ከነዚህ አራት በዓላት ሁለቱን ቤተክርስቲያን ታቦተ ህጉን አውጥታ በደማቁ ታከብረዋለች እነዚህም ሰኔ 30 ልደቱና መስከረም ሁለት አንገቱ የተቆረጠበትን ቀን ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 👉2⃣ ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያንን ሠርቶ የመሰረተልን ማንነው??

*// መልስ//*👉እራሱ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 👉3⃣ትውፊት ማለት፦ ምን ማለት ነው?

*//መልስ//*👉ትውፊት የሚለው  ቃሉ የግሪኩ ፓራዶሊስ የሚለው ሲሆን ትርጉሙም መቀበል፣መረከብ ማለት ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 👉4⃣የመጀመርያዎቹ  የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት የተፃፉት...በ... ነብይ ዘመን ነው??

*//መልስ//*👉በነብዩ ሙሴ ዘመን ነው።

✍ ጥ ተራ(ቁ)👉5⃣አራቱ(4) የቤተ ክርስቲያን አካላት ተብለው የሚጠሩት ማን ማን ናቸው???

*//መልስ//*👉ጳጳሳት፣ ካህናት ፣ ዲያቆናት እና ምእመናን ናቸው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉6⃣ቅዱስ ጳውሎስ ለደቀ መዛሙርትነት ሲመረጥ እድሜው ስንት ነበር??

*//መልስ//*👉 በ55 አመቱ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉7⃣ቅዱስ ጴጥሮስ ያስተማረባቸውን ቦታዎች ስም ጥቀስ/ጥቀሽ??

*//መልስ//* በከፊል ለመጥቀስ ያህል👉ሶርያ ፣ ገላትያ ፣ ፍልስጤም ፣ ቢታንያ ፣ ኢዮብ ፣ ቂሳርያ ፣ ሊድያ ፣ ሮሜ ፣ እየሩሳሌም ልዳ ፣   ቂሳርያ ፣ ጳንጦስ ፣  ኢስያ ወ.ዘተ ናቸው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉8⃣ በስርአተ ቅዳሴ ጊዜ/ ወንጌል ሲነበብ ሻማ/ጧፍ ለምን ይበራል???

*//መልስ//*👉1ኛ👉ክብር ይግባውና ጌታችና መድኃኒታችን እኔ የአለም ብርሃን ነኝ ስላለን ነው።

2ኛ✔ሐዋርያትና ሰማዕታት ለወንጌል የከፈቱን ዋጋ/መሰዋትነት የምናስበበት ነው። ይህ ማለት ሻማው እየበራ ይቀልጣል ቅዱሳን ሰማዕታትም ለአለም ብርሃን ብለው ደማቸውን ማፍሰሳቸውን ይዘክራል።

✍ጥ ተራ (ቁ)👉9⃣ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ለቤተ ክርስቲያን ከፃፏቸው መጽሐፍት ውስጥ ቢያንስ /አምስቱን 5/ቱን ጥቀስ/ጥቀሽ??

*//መልስ//*
በእግዚአብሔር በሰጣቸው በመንፈሳዊ ጸጋ ብዙ መጽሐፍትን እንደ ፃፉ ይነገራል ከነዚያ መካከል፦
👉መጽሐፈ ውዳሴ መስቀል፣ አርጋኖ፣ መሐፈ ሰዓታት፣ መጽሐፈ እንዝራ፣የሰባቱ ጊዜያት የጸሎት መጽሐፍትመዐዛ ቅዳሴው   ወ.ዘተ የመሳሰሉትን  ጽፈዋል።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉🔟እያሱ ማለት ምን ማለት ነው???

*//መልስ//*👉እያሱ ማለት፦ መድኃኒት ማለት ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣1⃣ አሪዎስ ወልድ ፍጡር ነው ብሎ የተናገረበት ምክንያት ምንድነው???

*//መልስ//*👉መ.ምሳሌ ም. 8፥22 እግዚአብሔር ለሥራው የመንገዱ የመጀመሪያ አድርጎ ፈጠረኝ፥ የሚለውን ሃይቃል በመጠቀም ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 👉1⃣2⃣ ጻዲቁ አባታችን አቡነ ሀብተ ማርያም የትውልድ ሀገራቸው የት ነው?? እናትና አባታቸውስ ማን እና ማን ይባላሉ??

*//መልስ//*👉በመንዝ አውርጃ ነው የተወለዱት👉አባቱ ፍሬ ቡሩክ እናቱ ዮስቴና ይባሉ ነበር። ፍሬ ብሩክና ዮስቴና በህገ እግዚአብሔር በሃማኖት በትሩፋት በምግባር ፀንተው የሚኖሩ ደጋግ ክርስቲያኖች ነበሩ።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣3⃣ የመጀመርያው  የቅዱስ ጴጥሮስ ደቀ መዝሙር የነበረው የሐዲስ ኪዳንን መጽሐፍትን ቆጥሮ ያስረከበው ቅዱስ ማን ይባላል???

*//መልስ//*👉ቅዱስ ቀለሚንጦስ (ፊሊጲንስ 4፥1-3 ላይ ይገኛል።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣4⃣ ታምረ ማርያምን የፃፈው ቅዱስ አባት ማን ይባላል??

*//መልስ//*👉ደቅስዮስ ይባላል።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣  አትሮኖስ ማለት ምን ማለት ነው?? ጥቅሙስ ምንድን ነው?? ምሳሌነቱስ ምንድን ነው??

*//መልስ//*👉ልዑካን በቅዳሴ ሰዓት ቅዱሳት መጻሕፍትን ሊያነቡ ያጠቀሙበታል፡፡ መዘምራንም በቅኔ ማሕሌት በአገልግሎት ጊዜ የሚያስፈልጉ መጻሕፍትን በማስቀመጥ የሚዜመውን ያዜማሉ የሚነበበውን ያነቡበታል በብሉያ ኪዳን በደብተራ ኦሪትና በታላቁ ቤተ መቅደስ መጻሕፍት ማንበቢያነት ያገለግል ነበር፡፡ በሐዲስ ኪዳንም በቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በላዩ ይዘረጉና ያነቡበታል፡፡
ምሳሌነቱም ፡-
አትሮኖስ የጌታ ዙፋን
መጽሐፉ የጌታ አንድም
አትሮኖስ የእመቤታችን
መጽሐፉ የጌታ ምሳሌ ነው በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ማህፀን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን ተቀምጧልና፡፡

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣6⃣ልጇ ሐዋርያ ቤቷ ቤተ ክርስቲያን የነበርላት ከቅዱሳት አንስት መካከል የሆነች እናት ማን ትባላለች???

*//መልስ//*👉የቅዱስ ማርቆስ እናት ማርያም ነት።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣7⃣⃣ክርስትና በምንነሳበት ጊዜ ሦስት ዓይነት ከረር ያላቸው ክሮች ከአንገታችን ላይ እናስራለን የነዚህን ክሮችን ከረር ጥቀስ/ጥቀሽ ምሳሌነትቱንም ጭምር??

*//መልስ//*👉(1ኛ)ጥቁር ክር፦በክርስትና የምንቀበለው የመከራ ህይወት ምሳሌ ነው (2ኛ)ነጭ ወይም ቢጫ፦በጥምቀት ያገኘነውን የኃጢአት ስርየት የመመስከራችን ምሳሌ ነው (3ኛ)ቀይ ክር፦በክርስቶስ ደም የመገዛታችን ወይም የመዳናችን ምሳሌ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣8⃣  ነገረ ማርያምን የፃፈው ቅዱስ ማን ይባላል??

*//መልስ//*👉ቅዱስ ዮሐንስ አፈወቅ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ)👉1⃣9⃣  ሚስጢረ ትንሳኤ ሙታን ማለት ምን ማለት ነው?? ትንሳኤ ሙታንስ በስንት ይከፈላል??

ሚስጢረ ትንሳኤ ሙታን ማለት በዓለም መጨረሻ የፈጣሪያችውን የእግዚአብሔርን ድምጽ ሰምተን ነፍስና ሥጋችን ተዋህዶ ከመቃብር የምንነሳበትና የዘላለም ሕይወትን የምናገኝ መሆናችንን የምንማርበትና የምናምንበት ምስጢር ነው። ትንሳኤ ሙታን በሁለት(2) የከፈላል እነርሱም፦ ትንሳኤ ዘለክብርና ትንሳኤ ዘለሀሳር በመባል ይታወቃል

✍ጥ ተራ(ቁ)👉2⃣0⃣ ማህበረ ጽዋ ማለት ምን ማለት ነው??

*//መልስ//*👉የተጀመረው በሐዋርያ ዘመን  ሲሆን ምእመናንና ነድያን በአንድነት ተሰብስበው በፍቅር በአንድነት ማአድ የሚካፈሉበት ነው ይከውም በጌታችን ስምና በቅዱሳን ስም መታሰቢያ የሚደረግበት የፍቅር ማአድ ማለት ነው።

*✍ማጠቃለያ መልስ*




saramareyama.890@gmail.com

የ9ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

https://youtu.be/pm3m3DPMzBQ

👆👆👂

*_✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ሰነበታችሁ? እንደምንስ አላችሁ??_

_እነሆ የ9ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀትየቃ መንፈሳዊ  የጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ መልስ👇👁_

✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣👉ከዘመነ መሳፍንት ቀጥሎ ያለው ዘመን ዘመነ ምን ይባል ነበር??

*/መልስ/*

✍መልስ፡- ከዘመነ መሳፍንት ቀጥሎ ያለው ዘመነ ነገሥት ይባላል፡፡ ልዩነታቸው በዘመነ መሳፍንት የሚፈርድ ንጉሥ የለም፡ በዘመነ ነገሥት ከሕዝቡ መካከል የተመረጠ ንጉሥ አለ፡፡

✔ጥ ተራ(ቁ) 2⃣👉መጽሐፈ ሩትን የፃፈው ? ማነው? መጽሐፉስ ስንት ምዕራፎች  አሉት? ሩትስ ማን ነች?

*/መልስ//*

✍መልስ፡- መጽሐፈ ሩትን የጻፈው ነቢዩ ሳሙኤል ነው፡፡ ሩት በዘመነ መሳፍንት የነበረች ሞዓባዊት ሴት ነበረች፡፡ መጽሐፉም 4 ምዕራፎች አሉት፡፡

✔ጥ ተራ( ቁ)3⃣ 👉"በክርስቶስ ኢየሱስ የእዝአብሔር  ልጆች ናችሁ፣ ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋል፤ ይህንን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኘዋለን?? ምዕራፍና ቁጥሩን??

*//መልስ//*

/ገላ. 3፥26_27/

✔ጥ ተራ(ቁ) 4⃣👉
"ጥበብ ቤቷን ሰራች ሰባቱንም ምሶሶዎችንም አቆመች፣ ፍሪዳዎችንም አረደች፣ የወይን  ጠጇንም ደባለቀች፣ ማዕድዋንም አዘጋጀች። ባርያዎቿንም ልካ በከተማይቱ ከፍተኛ ሥፍራ ላይ ጠራች /ምሳ 9፥1/ የሚለው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ቃል ሲተነተን✍👉ጥበብ የተባለው ማነው?
👉ቤት የተባለውስ?   👉ምሶሶዎች የተባለው
 ምሥጢራትስ ምንድነው?

👇👇👇👇
ጥበብ የተባለው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ቤት የተባለችው ቤተ.ክርስቲያን ናት። ምሶሶዎች የተባሉትም ምሥጢረ ቤተ.ክርስቲያን ናቸው ለምሳሌ👉 ምሥጢረ ጥምቀት👉ምሥጢረ ሜሮን 👉ምሥጢረ ንስሀ👉ምሥጢረ ቁርባን 👉ምሥጢረ👉ወዘተ እያልን የምጠራቸው ናቸው።

✔ጥ ተራ(ቁ) 5⃣👉 በፍልስጤማውያንና በእስራኤላውያን መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው??

👇👇👇

✍መልስ፡- እስራኤላውያን በግርዛት ለእግዚአብሔር የተለዩ ሲሆኑ ፍልስጤማውያን ያልተገረዙና በጣዖት የሚያመልኩ ናቸው፡፡

✔ጥ ተራ(ቁ)6⃣👉ሶምሶም ፍልስጤማውያንን እንቆቅልሽ ጠይቋቸው ነበር ለመሆኑ የጠየቃቸው እንቆቅልሽ ምን የሚል ነበር?

👇👇👇👇

✍መልስ፡- ከበላተኛ ውስጥ መብል ወጣ ፣ ከብርቱም ውስጥ ጥፍጥ ወጣ አላቸው፡፡ መሳ.14÷14

✔ጥ ተራ( ቁ) 7⃣👉 ፅዮን የሚለው ቃል በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ለ4 ነገሮች ተነግሯል ለምን ለምን??

👇👇👇👇👇

↪❤1ኛ ከተማ ጽዮን

✔💟ጥቂቶቹን ጥቅስ ለመግለጽ 《ሚኪ 3 ፡ 12》፣ 《2ኛ ሳሙ 5 ፡ 7》 ፣ 《2ኛ ዜና 5 ፡ 2》 ፣《 ኢሳ 64 ፡ 10》

↪❤2ኛ ሰባተኛይቱ ሰማይ ጽዮን

✔💟ጥቂቱን ለመግለጽ 《መዝ 46/50 ፡ 2》 ፣ 《ራዕ 14 ፡ 1》

↪❤3ኛ ቤተ እስራኤል ጽዮን

✔💟አንዱን ለመግለጽ 《መዝ 149/150 ፡ 1》

↪❤4ኛ ድንግል ማርያም ጽዮን
ጽዮን
✔💟ሰው ሁሉ እናታችን  ይላል በውስጥዋም ሰው ተወልዷልና 《መዝ 86/87 ፡ 5》

✔ጥ ተራ (ቁ) 8⃣👉በሰኔ 20 እና 21 ቀን የሚከበርበት  የእመቤታችን ቅድስት  ማርያምን አመታዊ በዓልን ምክንያት አስረዳ/አስረጅ???

ድንግል👇👇👇👇👇👇

..በዓሉ እንዴት ነው ቢሉ፦       እመቤታችን ባረገች በ4 ዓመት ጳውሎስና በርናባስ ፊልጵስዩስ ገብተው አስተማሩ፤ ሕዝቡም አምነው ተጠመቁ እንግዲህ ወዲህ ወደ ቤተ ጣዖት አትሂዱ አሏቸው የለመድነውን ከከለከላችሁንማ መካነ ጸሎት ስጡን አሏቸው፡፡  እንዲህ ብንላቸው እንዲህ አሉን ብለው ወደ ጴጥሮስና ዮሐንስ ላኩ አልቦ ዘትገብሩ ወኢምንተኒ ዘእንበለ ትዕዛዙ ወምክሩ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ጌታችን ፈቃድ አንዳች ልታደርጉ አይገባም እናንተም ጸልዩ እኛም እንጸልያለን ብለው ላኩባቸው፡፡ ሱባዔ ሲጨርሱ በዚህ ዕለት ጌታ በሩቅም በቅርብም ያሉ ደቀመዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ ሰበሰባቸው፡፡ ዮሐንስ ጌታዬ ለምን ሰበሰብከን ብሎ ጠየቀ ጌታም በእናቴ ስም ጽንፍ እስከ ጽንፍ አብያተ ክርስቲያናት እንዲታነጹ ፈቃዴ ነውና ሕንጻ ቤተክርስቲያን ላሳያችሁ ሥርዓት ላስተምራችሁ ነው አለው፡፡
   ይህንን ብሎ ወደ ምስራቅ ወሰዳቸው ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፣ በተአምራት አቀራርቦ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ሠጣቸው እሳት እንዳየው ሰም ከእጃቸው እየለመለሙ /እየተሳቡ/ ቁመቱን 24 ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ሠርተውታል፡፡ ከእንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ ብሏቸው ዐረገ፡፡
   በማግሥቱ እመቤታችንን መንበር ጴጥሮስን ተራዳኢ ካህን እስጢፋኖስን ሠራዒ ዲያቆን አድርጎ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡

✔ጥ ተራ(ቁ) 9⃣👉አምስቱ(፭) ሐራ ሲኦል ነገስታት የሚባሉት ማን ማን ናቸው??

👇👇👇

ፈርኦን በኤርትራ የሰመጠው፣ ሰናክሬም፣ አንጥያኮስ፣ ሔሮድስ፣ ዲዮቅልጥያኖስ ናቸው።

✔ጥ ተራ(ቁ)1⃣0⃣👉አምስቱ(፭) አርዕስተ አበው የሚባሉት ማን ማን ናቸው?  ስማቸውን ጥቀስ/ሽ ?

👇👇👇
አዳም፣ ሄኖክ፣ ኖህ፣ አብርሃም፣ ሙሴ ናቸው።

✔ጥ ተራ (ቁ)1⃣1⃣አምስቱ(፭)ሐብታት የሚባሉት ምን ምን ናቸው???

ሐብተ ፈውስ፣ ሐብተ ክህነት፣ ሐብተ ትንቢት፣ ሐብተ መዊእ፣ ሐብተ መንግስት ናቸው።

✔ጥ ተራ (ቁ)1⃣2⃣✔ አምስቱ (፭)  ህሩያነ ነገስታት የሚባሉት ምን ምን ናቸው???

*/መልስ//*

ሕዝቅያስ፣ ኢዮስያስ፣ ዳዊት፣ ሰለሞን፣ ንግስተ ሳባ/አዜብ/ማክዳ። ናቸው

✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣3⃣👉ቃለ ሕይወት ያሰማልን ምን ማለታችን ነው? /ቃለ ሕይወትን ያሰማልን ማለት ምን ማለት ነው??

*/መልስ/*

//መልስ///👉 ቃለ ህይወት ያልሰማልን ማለት👉 የእግዚአብሔርን ቃል ጠብቀው እንደቃሉ ለኖሩ
 ልብን የምመረምር እኔ ለእያንዳንዳችሁ እንደ ሥራችሁ ለመክፈል (ራዕ.22፥32) እስክመጣ ድረስ በፍቅር ኑሩ ያለውን ለፈጸሙ ....በአጠቃላይ በጌታ ለኖሩ ፍሬዎች...የሰው ልጅ በክብር በሚመጣበት ጊዜ (ማቴ.25፥31) በጎቹን ከፍየሎች በሚለይበት ጊዜ (ማቴ.25፥34) <<ኑ እናንተ የአባቴ ቡሩካን ኑ ዓለም ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ::>> ብሎ ጌታ የሚፈርደው ፍርድ የሕይዎት ቃል ይባላል::
ሥለዚህ ቃለ ሕይዎት ያሰማልን ማለት ይህን የተወደደ፣ ዘለዓለማዊ  የሚሰጥ ቃል ያሰማልን፤ ከቀኙ ከሚቆሙት ቅዱሳን ይደምርልን እንደማለት ነው።

✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣4⃣👉የእግዚአብሔር ጠባይ/ጸባይ ስንል ምን ማለታችን ነው??

*/መልስ/*

// መልስ ///፦የእግዚአብሔር ጠባይ ስንል በማናቸውም  ለእግዚአብሔር  እንጂ ለፍጡር የማይነገር የእርሱ የብቻው የባሕርይው መገለጫ ወይም
በእግዚአብሔር ባህርይ ውስጥ የሚገለጡትን ሁኔታዎች የሚያመለክት ነው።

✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣5⃣👉በዓል ማለት ምን ማለት ነው?? የመጀመርያዋ በዓልስ ማናት??

*/መልስ/*

//መልስ ///፦ በአል ማለት፦ አብዐለ፤ አከበረ ፤ አበለጠገ፣ ዕለትን በዓል አደረገ፤ ከሚለው ግስ የወጣ ስም ነው። በቁሙ ሲፈታም የደስታ፤ የዕረፍት ቀን ፣ የዓመት፣ የወር፣ በሳምንት የሚከበር፣ ያለፈ ነገር የሚታሰብበት ተዝካር ማለት ነው።
የመጀመርያዋ በልዓ ቀዳሚት ሰንበት ናት። እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባረከው ቀደሰውም፤ እግዚአብሔርሰንበትን ሊያደርገው ከፈጠረው ቀደሰውም በእርሱ ዐርፎአልና> እደተባለ እግዚአብሔር  ለይቶአክብሯታል ቀድሷታልም። ዘፍ. 2፥3 ስለዚህ ይህ የበአል መጀመሪያ ሆነ።

✔ጥ ተራ (ቁ) 1⃣6⃣👉ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል ሦስት ትርጉም አለው። ምን ምን ??

*//መልስ//*

1ኛ👉የክርስቲያን መሰብሰቢያ/የጸሎት ቤት

2ኛ👉 እራሱ ሕንፃው ቤተ ክርስቲያን ይባላል

3ኛ👉ምዕመናን ቤተ ክርስቲያን ይባላል

✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣7⃣👉ክብር ይግባውና ጌታችና መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የብዙ ቅዱሳንን ምልጃ ተቀብሏል። ምልጃቸውን ከተቀበለላቸው ቅዱሳን  ቢያንስ ሦስቱን ጥቀስ/ጥቀሽ???

*/መልስ/*

👉የአብርሃምን (ዘፍ 18፥23)
👉የሙሴ የአብርሃም፣የይሳቅ፣እና የያዕቆብን ስም እየጠራ የማለደውን /ዘጸ. 32፥11-13)፣ ሙሴ ለእህቱ ለማርያም ሲል ያቀረበው (ዘኁ. 12፥10)፣ ሳሙኤል ስለ ሕዝቡ ያቀረበውን/ 1ኛ ሳሙ. 7፥5/ ኢዮብ/ ኢዮብ 42፥7/፣ ዳዊት ስለ ሕዝቡ/2ኛ ሳሙ. 24፥17/  ብዙ መቅጥቀስ ይቻላል

ውስጥ✔ጥ ተራ(ቁ) 1⃣8⃣👉
ጉባኤ ቃና ማለት ምን ማለት ነው?? ጉባኤ ቃና በሁለት ክፍል ይከፈላል። ምን ምን ???

*/መልስ/*

 ቃና ማለት የፈጣሪ ጉባኤ ተቃና፣ የቅኔ ትምህርት ተጀመረ፣ ተለካ ጉባኤው ተቃና ማለት ነው። ጉባኤ ጉባኤቃና በሁለት ክፍል ይከፈላል። ይኸውም ግእዝ  ቃና፣ ዕዝል ጉባኤ ቃና ወይም አጭር ጉባኤ ቃና፣ ረጅም ጉባኤ ቃና በመባል ይጠራል።
.

✔ጥ ተራ(ቁ)1⃣9⃣👉የማሕሌት ሰባቱ/፯/ ደረጃዎች የሚባሉት ምን ምን ናቸው???

*/መልስ/*

1ኛ 👉ቁም ዜማ

2ኛ👉ዝማሜ

3ኛ👉ቁም ጸናጽል

4ኛ👉መረግድ

5ኛ👉ጽፋት

6ኛ👉አመላለስ

7ኛ👉ወረብ ናቸው።

✔ጥ ተራ(ቁ) 2⃣0⃣👉
ማሕሌት እንዴት ተጀመረ? ማን ጀመረው? የት ተጀመረ??

*/መልስ/*

ማሕሌት በመላእክት ዘንድ እንደተጀመረ ጀማሪዎችም እነርሱ በሆናቸውን የቃሉ ትርጓሜ ምስጋና ማለት መሆኑን ቅዱሳት በጻሕፍት ይነግሩናል።

*ማጠቃለያ መልስ ይህ ይመስላል ስተት ካለበት አርሙኝ*

*ወስብኃት ለእግዚአብሔር*

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=689617831227746&substory_index=0&id=391288387727360

👁ፔጅ⤴

https://www.facebook.com/sara.mareyame.54
✍00971 50 17 21 032saramareyama.890@gmail.com

የ8ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር

saramareyama.890@gmail.comhttps://youtu.be/r_wP_d9IlM0

*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

_8ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር_

*_ማጠቃለያ መልስ_*👀

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣ 👉ቅዱስ ዮሐንስ መልእክ የፃፈላቸው ሰባቱ (7)  አብያተክርስቲያናት ማን ማን ናቸው??

*✍/መልስ/*👇

1. ⛪የኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን
2.⛪ የሰርሞኔስ ቤተ ክርስቲያን
3. ⛪የጴርጋሞን ቤተ ክርስቲያን
4. ⛪የትያጥሮን ቤተ ክርስቲያን
5. ⛪የሰርዴስ ቤተ ክርስቲያን
6. ⛪የፍልድልፊያ ቤተ ክርስቲያን
7. ⛪የሎዶቂያ ቤተ ክርስቲያን
"

✍ጥ ተራ (ቁ) 2⃣👉አምስቱ (5) እቀባተ መስቀል የተባሉት እነማን ናቸው በዝርዝር አስረዳ/ጅ??

*✍/መልስ/*👇

👉1ኛ ጣዖት ማምለክ

👉2ኛ አፍቅሮ ነዋይ

👉3ኛ ተጣልቶ አለመታረቅ

👉4ኛ ሰው መግደል

5ኛ👉እናትን እና አባትን አለማክብር ናቸው።

♥♥♥♥♥♥

✍ጥ ተራ (ቁ)3⃣👉መስቀሌን በመስቀለኛ ቦታ ላይ አስቀምጥ ተብሎ በእራይ የተነገረው አባት ማን ይባላል??

*✍/መልስ/*👇

👉አፄ ዘርያእቆብ ነው።

♥♥♥♥♥♥

✍ጥ ተራ (ቁ) 4⃣👉በሀገራችን ኢትዮጵያ የመጀመርያው ሊቀ ጳጳስ ማን ይባላል??

*✍/መልስ/*👇

👉አባ ሰላማ ከታሳቴ ብርሀን ይባላሉ።

♥♥♥♥♥♥♥

✍ጥ ተራ (ቁ) 5⃣👉በመጽሐፍ ቅዱሳችን ውስጥ ካሉ የተባረኩ ጋብቻዎች ውስጥ ሁለቱን ጥቀስ(ሽ)

*✍/መልስ/*👇

✍የኢያቆምና የሐና፣ የዘካሪያስና የኤልሳበጥ ጋብቻ

♥♥♥♥♥♥

✍ጥ ተራ (ቁ)6⃣👉 በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን ዲያቆን እድሜው ስንት ሲሆን ቅስና ይሾማ??

*✍/መልስ/*👇

በሰላሳ አመቱ (30) ይሾማል።

✍ጥ ተራ (ቁ)7⃣👉በኦሪቱ ታቦት የሚባለው ምንድነው ጽላት የሚባለውስ??

*✍/መልስ*/👇
በኦሪቱ ታቦት የሚባለው ጽላት የሚቀመጥበት ማደሪያው ነው። ዘጸ 40፥20-21፣25፥20-22፣መዝ131፥8፣ 2ቆሮ6፥16፣ ዕብ9፥4፣ ራዕ 11፥9 ጽላት  የሚባለው ደግሞ እግዚአብሔር ለሙሴ  አስርቱ ቃላተ ኦሪትን በእጁ የሰጠው ቃሉ ተጽፎ የሚገኝበት ከእብነበረድ የተቀረጸው ነው። ዘጸ31፥18፣24፥12-25፣10፥22አስቀድሞ፣34፥1-29

✍ጥ ተራ (ቁ) 8⃣👉መስዋዕተ ቁርባን ማቅረብ የተጀመረው በማን ነው??

*✍/መልስ/*👇

👉በአባታችን አዳም ነው።

✍,ጥ ተራ (ቁ)9⃣👉 በቅዳሴ ሰዓት ወንጌል ስንሳለም ምን ማለት አለብን??

*✍/መልስ/*👇

👉ነአምን በወንጌክ በቅዱስ እንላለን።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣0⃣👉 ቅጽር ግቢና የውጭ አደባባይ ገበያ ዘርግቶ ንግድ መነገድ ክልክል እንደሆነ  ከሚያስዱ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች በቤተክርስቲያንውስጥ 3ቱን ጥቀሱ???

*✍/መልስ/*👇

👉ኤር 7፥11፣ ማቴ 21፥12-14፣ ማር11፥15-17፣ ሉቃ19፥45-46፣ ዮሐ2፥13-18... እናገኛለን

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣1⃣👉ሰባቱ(7) አባቶች የሚባሉት/  ማን ማን ናቸው???

*✍/መልስ/*👇

"ሰባቱ አባቶች"
1ኛ👉ልዑል እግዚአብሔር
2ኛ👉 የንስሐ አባት
3ኛ👉ወላጅ አባት
4ኛ👉 የክርስትና አባት
5ኛ👉የስልጣንየጡት አባት
6ኛ 👉 (የቆብ) አባት
7.ኛ👉የቀለም አባት

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣2⃣👉የክህነት አላማና ጥቅም ምንድነው??

*✍/መልስ/*👇

👉 ሰዎችን ከኃጢአት ከሰይጣን ስራ ሁሉ በመለየት በማስተማር በመቆጣጠር በመጠበቅ በመቀደስና በማንጻት በማናዘዝና በመፍታት
ለጨለማው ብርሃን ለመሆን ፣አልጫ የሆነውን ዓለም ለማጣፈጥ፣ ምስጢራተእንዲሆኑ ቤተክርስትያንን በመፈጸም  ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ማሰጠት የእግዚአብሔር ልጆች የመንግስቱ ወራሾች  ለማብቃትና ድኅነተ ነፍስ ለማሰጠት ፣  እግዚአብሔርን ለምእመናንበቅዳሴና በውዳሴ ለማመስገንና መንፈሳዊ አገልግሎት ለመፈጸም ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣3⃣👉⃣አምስቱ (5) ፍኖተ ኃጢአት የተባሉት እነማን /ምን ምን ናቸው??

*✍//መልስ//*👇

1ኛ👉 ትቢት

2ኛ👉ስስት

3ኛ👉ምቀኝነት

4ኛ👉ስርቆት

5ኛ👉ዝሙት ናቸው።

✍ጥ ተራ (ቁ)1⃣4⃣👉⃣ሥጋዊ ፍላጎቶችን ማሸነፍ ለአክሊለ ሕይወት የሚያበቃ ሰማዕትነት ነው። ብሎ የተናገረው አባት ማን ይባላል??

*✍መልስ//*👇

👉ብፁ አቡነ ጎርጎርዮስ ካአል ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣👉ለመጀመርያ ጊዜ ካህን  ሁኖ  የተሾመው ቅዱስ አባት ማን ይባላል???

*✍/መልስ*/👇

👉ካህኑ መልከ ጸዲቅ ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣6⃣👉ለመጀመርያ ጊዜ የተጻፈው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የትኛው ነው? ወይም የማን መጽሐፍ ነው??

*✍/መልስ//*👇

👉መጽሐፈ ሄኖክ ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣7⃣ሀሌ ሉያ ማለት ምን ማለት ነው???

*✍//መልስ//*👇

👉ሃሌ ሉያ ማለት እግዚአብሔር  ይመስገን ማለት ነው።

እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን። ሃሌ ሉያ (መዝሙር 150፥6)

✍ጥ ተራ (ቁ)1⃣8⃣👉 በቅዳሴ ጊዜ 5ት/አምስት መስዋቶች አሉ። ምን ምን ናቸው??

*✍/መልስ//*👇

1ኛ👉 የቁርባን መሰዋት

2ኛ👉 የከንፈር መሰዋት

3ኛ👉 የመብራት መሰዋት

4ኛ👉 የእጣን መሰዋት

5ኛ👉 የሰውነት መሰዋት ናቸው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣9⃣👉 ኤልሻዳይ ማለት
👉ያህዌ ማለት
ምን ማለት ነው የሱሞችን ትርጉም አስረዳ/ጂ??

*✍//መልስ//*👇

ቅ✍🏻_*ኤልሻዳይ*ማለት ምን ማለት ነው??

//መልስ//✔ _ኤልሻዳይ ማለት ሁሉን ቻይ ማለት ነው_
አብርሀምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለአብራም ተገለጠለትና፦ እኔ ኤልሻዳይ ነኝ፤ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤
((ዘፈጥረት 17፤1))

✍🏻ያህዌ* ማለት ምን ማለት ነው??.

//መልስ//✍🏻ያህዌ ማለት የነበረ ያለና የሚኖር ማለት ነው።" አብርሃምም ያንን ቦታ ያህዌ ይርኤ ብሎ ጠራው፤ እስከ ዛሬም ድረስ በእግዚአብሔር ተራራ ይታያል ይባላል።"
(ኦሪት ዘፍጥረት 22:14)

♥♥♥♥♥♥♥

✍ጥ ተራ (ቁ) 2⃣0⃣እምነ ጽዮን ማለት ምን ማለት ነው????

*✍/መልስ//*👇

✍🏻_*እምነ* ጽዮን ማለት ነውምንም ማለት ነው_??

//መልስ//እምነ ጽዮን ማለት እናታታችን ጽዮን ማለት ነው፡፡ በመጀመሪያይቱ የሰው ልጆች ሁሉ እናት ሔዋን አማካኝነት ከርስታ ን ወጥተን መጠጊያ አጥተን ነበግ በዳግማዊ ሔዋን በድንግል ማርያም ደግሞ ወደ ርስታችን ተመልሰናል። እናታችን ጽዮን እንላለን።

♥♥♥♥♥♥♥

*ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አርሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነን።*

የ7ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

https://youtu.be/l1IoBZtsdro👂👆

*✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

_✍7ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ  ጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ  መልስ።_

✍/ ጥ ተራ (ቁ)1⃣👉 እሕቴ ሙሽራ የተቆለፈ ገነት የተዘጋ ምንጭ የታተመም የውኃ ፈሳሽ ናት"  መኃ 4፥ 10 የሚለው ጥቅስ ምንን ያመለክታል??

ሀ/ የእመቤታችን ፍፁም ድንግልናል

ለ/ እመቤታችን ጌታን መውለዷን

ሐ/ ለእመቤታችን የተሰጠ ቃል ኪዳን.

መ/ የእመቤታችን ስደት

*//መልስ*

👉ሀ/ የእቤባታችን ፍፁም ድንግልናን።

✍ ጥ ተራ (ጥ) 2⃣👉 ከሰው ወገን ለመጀመሪያ  ጊዜ ለእመቤታችን ምስጋና ያቀረበው ____ነው??

ሀ/ ቅዱስ ኢያቄም

ለ/ ቅድስት ሐና

ሐ/ ቅዱስ ዮሴፍ

መ/ ቅድስት ኤልሳቤጥ

*//መልስ//*👇
.
👉መ/ ቅድስት ኤልቤባጥ

✍ጥ ተራ (ቁ) 3⃣👉 ቅዱስ አግናጥዮስ በኤፌሶን ፣ በፊላደልፊያ ፣ በማግኒስያ፣ በቴራሊስ፣ በሮምና  በመሳሰሉት ሀገራት ውስጥ ላሉ ክርስቲያኖች ሰባት መልእክታትን በሰባት ዓይነት አርዕስት ጽፎላቸዋል። እነዚህ ሰባት መልእክታት ምን ምን  ናቸው??

*//መልስ//*

👉 መናፍቃንን በፍፁም መቀዋወም እንደሚገባ።

👉ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን መገዛት እንደሚገባ።

👉ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ፍፁም ድንግልና።

👉ስለ ጌታችን ፍፁም ሕማምና መከራ።

👉ስለምሥጢረ ቁርባን።

✍ጥ ተራ (ቁ) 4⃣👉የአለም አብያተ ክርስቲያን አንድነት ጉባኤ ጽ/ቤት የት ይገኛል??

*//መልስ//*

👉በሆላንድ ሀገር  / በጆኔቫ ይገኛል።

.
✍ጥ ተራ(ቁ) 5⃣👉 ከገነት ፈሳሽ ወንዞች መሀል ኢትዮጽያን የከበበው ወንዝ ማን ይባላል?
ከመጽሀፍ ቅዱስ ማስረጃ ጥቅስ ??

*//መልስ*//

👉*ግዮን ይባላል*
*ዘፍ 2:13*

✍ጥ ተራ (ቁ) 6⃣👉የክርስቲያን  የችግርና የመከራ  መፍቻ ምንድነው??

*//መልስ//*

👉ፆም ፀሎት ሥግደት እግዚአብሔርን በትዕግስት ማገልገል ዘ.ዘተ ናቸው።


 ✍ጥ ተራ (ቁ) 7⃣👉ጥቂት የሰሌን ፍሬዎች እየተመገበ  በበረሀ በተጋድሎ ሲኖር የነበረው ፃድቅ ማነው ይባላል ለስንት አመትስ በተጋድሎ  ኖረ??

*//መልስ//*

👉ፃዲቅ አቡናፍር ናችው።

👉በምድር ላይ 60 አመት ኑረዋል።

✍ጥ ተራ(ቁ) 8⃣👉 ጠፈርን የሚያቀዘቅዘው  ወንዝ ማን ይባላል??

*//መልስ//*

👉ዋኖስ ይባልላ።

✍ጥ ተራ(ቁ) 9⃣ 👉እርፈ መስቀል ማለት ምን ማለት ??

*//መልስ//*

👉የጌታችን ቅዱስ  ክቡር  ደሙ የሚሰትበት ማንኪያ ማለት ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣0⃣👉የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ጥናት በስንት ይከፈላል ጥቀስ/ጥቀሽ?

*//መልስ//*

በሦስት ይከፈላል እነርሱም፦ 1ኛ 👉የጥንት ቤተክርስቲያን ታሪክ ጥናት

2ኛ👉የመካከለኛ ቤተ  ታሪክ ጥናት

3ኛ👉አዲስ  ታሪክ ጥናት በመባል ይታወቃሉ።
ክርስቲያን
የቤተክርስቲያን
✍ ጥ ተራ (ቁ) 1⃣1⃣👉የአጹማት ማውጫ የሚሆኑ 7 ቀመሮች አሉ  እነርሱን በዝርዝር አስምቀጥ / አስቀምጭ??

*//መልስ//*👇

👉ዓውደ እለት

👉ዓውደ ወርቅ

👉ዓውደ አመት

👉ዓውደ ምክቲ

👉ዓውደ ፀሐይ

👉ዓውደ መሀተብ

👉ዓውደ አብይ ይባላሉ።

✍ጥ ተራ(ቁ)1⃣2⃣👉 የቅዱስ ላሊበላ ውቅር ቤተ ክርስቶያኖች  11አሉ የእነርሱን ቅዱሳን ስም ስያሜ  ዘርዝሩ ??

*//መልስ//*

*እነሱም፦*
1ኛ ቤተ መድሀኒአለም
2ኛ ቤተ ማርያም
3ኛ ቤተ መስቀል
4ኛ ቤተ ደናግል
5ኛ ቤተ ጎለጎልታ
6ኛ ቤተ ቀራኒዮ
7ኛ ቤተ ጊዮርጊስ
8ኛ ቤተ ገብርኤል
9ኛ ቤተ አማኑኤል
10ኛ ቤተ መርቀሪዎስ
11ኛ ቤተ አባ ሊባኖስ ይባላሉ።👆🏻

 ✍ጥ ተራ(ቁ)1⃣3⃣👉 ለመጀመርያ ግዜ እግዚአብሔር ይፍታ ያሉት አባት ማን ይባላሉ??

*//መልስ//*

👉አባ ጼጥሮስ ይባላሉ።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣4⃣👉⃣ የቤተክርስቲያንናችን ሊቅ የዜማው ደራሲ ብርሀነ አለም ቅዱስ ያሬድ የመጀመርያው ዜማው ምን በመባል ይጠራል??

*//መልስ//*👇

👉አራራይ ይባላል። አራራይ ማለት፦ የማትጠፋ ማለት ነው።

✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣👉⃣የብሉይ ኪዳን መጽሀፍ ከእብራይስጥ ቋንቋ ወደ ግሪክ  እነማን ናቸው ?ማን በነገሰ  ዘመን ቀየሩ??

*//መልስ//*👇

*በዘመኑ የነበሩት  7ቱ ሊቃውንት  ናቸው። ጥሊሞስ በነገሰ ዘመን ነው ከእብራይስጥ ወደ ግርክ ያስቀየረውና የቀየሩት።*

ሊቃውንት✍ጥ ተራ (ቁ) 1⃣6⃣👉ኢትዮጵያ የሚለው ቃል የእያንዳንዱን የፊደል ትርጉም ዘርዝሪ/ ዘርዝር??

ለምሳሌ ኢ ማለት
ት ማለት ምን ማለት ነው?

*//መልስ//*

ኢ= ማለት ለሊሁ ተንሣኢ ወለሊሁ አንሣኢ ማለት ነው።

ት= ማለት ትፍሥሕት ወሐሴት ማለት ነው።

ዮ= ማለት የድ የማነ እግዚአብሔር ማለት ነው።

ጵ= ማለት ጵርስፎራ ማለት ነው።

ያ= ማለት አንተ ኬንያሁ ማለት ነው።

ከፊደላት ትርጓሜ የተወሰደ።

✍ ጥ ተራ (ቁ) 1⃣7⃣👉ሊቅና ፃዲቅ አባ ጊዎርጊስ ዘጋስጫ የት ሀገር ተወለዱ በስንት? ዓ.ም ?? ተወለዱ? የእናትና  የአባታቸው ስም ማን ይባላል የመጀመሪያው ድርሰታቸው ምን ይባላል??

*//መልስ//*👇

👉የትውልድ ሃገራቸው ኢትዮጵያ ሲሆን በ 1357 ዓ.ም በወሎ ክፍለ ሀገር በቦረና ወረዳ ሰግላ በተሰኘው ቦታ ተወለዱ አባታቸው ህዝበ ጽዮን ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ አምሀ ጽዮን ይባላሉ። የመጀመርያ ድርሰታቸው አርጋኖን ይባላል ።

✍ጥ ተራ (ቁ)1⃣8⃣👉መጽሐፈ ቀለሚንጦስ ከ81 መጽሐፍ ቅዱስ አንዱ ሲሆን የጻፉት ቅዱስ አባት ማን ይባላል???

*//መልስ//*👇

👉መጽሐፈ ቀለሚንጦስን የጻፉት ቅዱስ  ቀለሚንጦስ ሲሆን ቅዱስ ቀለሚንጦስ የተወለዱት  ሮም ውስጥ ነው።

 ያደጉትም በሮምና አካባቢዋ ነው። ቅዱስ ቀለሚንጦስ የሮም አራተኛ ሊቀ ጳጳስ ሲሆን የቅዱስ ጴጥሮስ ረድዕ(ደቀመዝሙር) ነበሩ። ፊሊ 4፥3።  ክህነታቸውንም የተቀበሉት  ከመምህራቸው  ከቅዱስ ጴጥሮስ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 1⃣9⃣👉የዓለም አብያተ ክርስቲያን አንድነት ጉባኤ ዓላማ ምንድን ነው??

*//መልስ//*👇

👉የአለም አብያተ ክርስቲያን አንድነት ጉባኤ  ዋና አላማ፦  ከሁሉም በላይ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን ለማቋቋም ሳይሆን ጥላቸውን እንዲቀንስ፣ የሃይማኖት ጦርነት እንዳይኖር የክርስቶስን ሰላም ቤተክርስቲያንየሚፈጠሩትን እንዳታጣ የዓለም ክርስቲያኖች ሁሉ በወንድማማችነት የራሳቸው ባላቸው መንፈስ እየተሰበሰቡ በመካከላቸው የተፈጠሩትንና ለወደፊትም  ችግሮች ለማስወገድ ነው።

✍ጥ ተራ(ቁ) 2⃣0⃣👉የፕሮቴስንቲዝም ሃይማኖት መነሻ የሆነው  ማነው??

*//መልስ//*👇

*//መልስ//*👇

👉ማርቲን ሉተር ነው።

*ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል።ስተት ካለብኝ አርሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነኝ!!*

*ወስብኃት ለእግዝአብሔር*saramareyama.890@gamail.com

የ6ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

saramareyama.890@gamail.com
*✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

6ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር ማጠቃለያ መልስ*❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣)👉ዕፀ በለስ ለምን ተፈጠረች ምክንያቱን አስረዳ/አስረጅ???

*//መልስ///* 1ኛ👉 አዳምመስራት ለእግዚአብሔር ያለውን ፍቅር እንዲገልፅ  ይህም ስንል አዳም ትእዛዜን እግዝአብሔርን እወዳዋለሁ ካለ ትእዛዙን ማክበር  የአዳም ፉቅር  ትእዛዝ  ስለነበረበት  ምክንያቱም አምላካችን ከወደድከኝ  ጠብቁ ይላልና            2ኛ👉🏻 እንዲገለፅየአዳም ፉጡርነት ይታወቅይታወቅ ዘንድ ዳቢሎስ ፈጣሪነትን ተመኝቶ ነበር ስለዚህ ዕፀ  በለስን  ምልክት አድርጎ አስቀመጠ   ብሎት ስለነበር  በላይ አምላክ  ለማሳወቅ 
3ኛ👉🏻 የአዳም ነፃ ፈቃዱ  ዘንድ  ግዛምክንያቱም እግዚአብሔር ከገነት ዛፉ ሁሉንሁሉ ብላ ነገር ግን ከአንድቱዋ እፅ በባላህ ቀን የሞት ሞትንsaramareyama.890o@gmail.com  ትሞታለህ ብሎ ነፃ ፈቃድ ሰጥቶት ነበርና።

✍ጥ ተራ ቁ(2⃣)👉ስንት ዓይነት ሰማዕትነት አለ??? ምን ምን??

*//መልስ//*ሦስት ናቸው👉 እነርሱም📚አበይት ሰማህታት
📚ንዑስ ሰማህታት
📚ሊቃውንት ሠማህታት ይባላሉ።

✍ጥ ተራ ቁ(3⃣)👉ንጉስ ቆስንጠንጢኖስ በስንት ዓ.ም ተወለደ በስንት አመቱስ ነገሰ???

*//መልስ//* በ272 ዓ.ም ተወለደ በ18 አመቱ በ316 ዓ.ም  በአባቱ ቦታ ሐምሌ 25 ቀን በ316 ዓ.ም በሮም ምዕራብ ክፍል በገላትያ ነገሰ።

✍ጥ ተራ ቁ(4⃣)👉በመጽሐፍ ቅዱስ ታሪክ ለመጀመርያ ጊዜ ሙት ያስነሳ ነብይ ማን ይባላል??

*//መልስ//* ነብዩ ኤልያስ ነው።

✍ጥ ተራ ቁ(5⃣)👉ከእመቤታችን አንስቶ ወደ ኋላ ሰባተኛ ትውልድ የሆኑት ማንና ማን ናቸው??

ሀ/ ሲካርና ሔርሜላ

ለ/ ቶናህና ደርዳ

ሐ/ ቴክታና ሄኤሜን

መ/ ቴክታና ጴጥርቃ

ሠ/ ሔርሜላና ጴጥርቃ

*//መልስ//* መ/ቴክታና ጴጥርቃ

✍ጥ ተራ ቁ( 6⃣)👉ቤተ ክርስቲያን የሚለውን ቃል በመጀመርያ የተጠቀመበት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  እንደሆነ ቅዱስ ወንጌል ያስረዳናል። ማቴ. ፩፮፥፩፰። ( ደቀመዛሙርት) ለመጀመርያ ጊዜ ክርስቲያን የተባሉት___ ነውና/ በየት ሀገር ነው?

*// መልስ//* በአንፃኪያ ነው። በዋርያት ሥራ ላይ እናገኘልለን።

✍ጥ ተራ ቁ(7⃣)👉ዘመነ ጰራቅሊጦስ የሚባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ ከ____ ቀን ጀምሮ እስኪ ___ ቀን ድረስ ያሉት ቀናት ናቸው።

*//መልስ//*
ዘመነ ጰራቅሊጦስ የሚባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ ከ50 ቀን ጀምሮ እስኪ ሠኔ  7 ቀድ ድረስ ያሉት ቀናት ናቸው።

✍ጥ ተራ ቁ(8⃣) 👉እስራኤል በጽኑ ተአምራት ከግብፅ ባርነት በጥተው የኤርትራን ባሕር በተሻገሩ ጊዜ በመዝሙር ለእግዝአብሔር ምስጋና ያቀረበቸው ነብይት ማናት መዝሙሩስ ምን የሚል ነበር??

*//መልስ//* ነብይት  የሙሴእህት ማርያም ናት ንሴብሆ ለእግዝአብሔር የሚለውን መዝሙር ነው የመዘረች።

✍ጥ ተራ ቁ(9⃣)👉በተወለድን ወንዶች በ40 ቀን ሴቶች በ80 ቀን ለምን እንጠመቃለን?? ምክንያቱን አስረዳ/አስረጅ?

*//መልስ//*በ 40 እና በ80 ቀን የሆነበት ምክንያት አዳም በተፈጠረ በ40 ቀን ሔዋን በተፈጠረች በ80 ቀን ገነት እንዲገቡ ስለተፈቀደላቸው ነው (ኩፋ
4፣9)።
እንዲሁም በኦሪት ይደረግ የነበረው ሥርዓት ለሃዲስ
ምሳሌ በመሆኑ(ዘሌ12፣12 1-8. ሉቃ 2፣22)። ልጆችም እንደየጾታቸው በ 40 እና በ 80 ቀን የጸጋ ልጅነት ያገኛሉና ነው።(ዘሌ 12፣1-8)።

✍ጥ ተራ ቁ(🔟) የግብፅ መንበር በዱቅስ ማርቆስ ሲጠራ የኢትዮጵያ መንበር በማን ይጠራል??

*//መልስ//* በመንበረ ተክለ ሃይማኖት ይጠልራ።

✍ጥ ተራ ቁ( 1⃣1⃣) ማሕሌተ ጽጌን የደረሱት ታላቁ ሊቅ ማን ናቸው??

*//መልስ//*አባ ጽጌ ድንግል ናቸው ሙሉ ታኩን ገድለ ዜና ማርቆስ ላይ ይመልከቱ።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣2⃣) ኤፍታህ ማለት ምን ማለት  ነው??

*//መልስ//* ተከፈት ማለት ነው። 👉የማርቆስ ወንጌል (7፥35-36) ላይ ይገልኛ።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣3⃣)👉አቡነ  ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከግብፅ  ሲመጡ ያረፉበት /የተቀመጡበት ቦታ የት ነው?? የተቀበሩበት ቦታስ የት ነው??

*//መልስ//* የተቀመጡበት ቦታ ዝቋላ ደብረ ከዋክብት ሲሆን የተቀበሩበት ቦታ ምድረ ከብድ ይባላል።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣4⃣)👉ሰባቱ ሰማያት የሚባሉትን ከታች ወደ ላይ ጥቀስ???

*//መልስ//* ኤረር፣ ራማ፣ ኢዮር፣ አለም፣ መላእክት፣ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት፣ ሰማይ ውዱዝ፣ ጽርሐ አርያም፣  ናቸው።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣5⃣)👉ኢየሱስ ክርስቶስ ተጠምቆ ከፆመ በኋላ በመጀመሪያ ያደረገው ታአምር ምንድነው??

*//መልስ//* የቃና ዘገሊላውን ተአምር። የዮሐንስ ወንጌል 2፥1_12 ላይ ይገልኛ።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣6⃣)👉ሐዋርያት ለመጀመርያ ጊዜ ተሰብስበው ውሳኔን ያስተላለፉት መቸ ነው???

*//መልስ//* በማቲያስ ምርጫ ጊዜ የሐዋርያት ሥራ 1፥15-26 ላይ ይገልኛ።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣7⃣)👉ኢየሱስ ክርስቶስ  አርባ ቀንና ሌሊት ከፆመ በኋላ ድል ያደረገው ሦስት ታላላቅ ኃጢአቶች ምን ምብ ናቸው??

*//መልስ//*፩ኛ  ስስት፣ ፪ኛ ትዕቢት፣ ፫ኛ ገንዘብ መውደድ። የማቴዎስ ወንጌል 4፥1-15 ላይ ይገኛል።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣8⃣) 👉ከስምንቱ የአቢይ ፆም ሳምንታት የመጀመርያው ሳምንት ሁለት ስን አለው ምንና ምን ናቸው??

*//መልስ//* ጾመ ሕርቃንና ዘወረደ  በመባል ይታወቃል።

✍ጥ ተራ ቁ(1⃣9⃣)👉ከ36ቱ ቅዱሳን አንስት አንዷ የሆነቸው የአስቆሮቱ ይሁዳ እናት ስሟ ማን ይባላል??

*//መልስ//* ሣራ/ሶፍያ/ ትባላለች

✍ጥ ተራ ቁ(2⃣0⃣)👉በቅዱስ ቅባት ተቀብተው የነገሡ ፬(4) ነገስታት ማን ማን ናቸው??

*//መልስ//* ሳኦል፣ዳዊት፣ አዛኤልና ኢዩ ናቸው

*❤ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አርሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነኝ*

*ወስብኃት ለእግዝአብሔር*

የ5ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የማጣሪያ ውድድር

https://youtu.be/wlZ-cp5t-dE


*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

_❤ውድ ተወዳጆች ሆይ እንደምን ቆያችሁ?? ሰላማችሁ ብዝት ይበል አሜን፫_

*5ኛ ዙር የማጠርያ/ የማበላለጫ የተወዳዳሪዎች ጥያቄ የማጠቃለያ መልስ እንደሚከተለው ይቀርባል፦*👇
፨፨፨፨፨፨፨♥♥♥፨፨፨፨፨


✍የጥ ተራ (ቁ) 1⃣  ✔መልስ✔ ጌታችና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ከአብርሀምና ከዳዊት ዘር መወለዱን ለማስረዳት ከአብርሃም እስከ ቅድስት ድንግል ማርያም ድረስ በሰፊው ስለ ፃፈው ከጥንት ጀምሮ ማቴዎስ በገጸ-ሰብእ ተመስሏል። ከሦስቱ ወንጌላውያን ይልቅ በማቴዎስ ወንጌል ክርስቶስ ወልድ እጓል እመሕያው ልጅ በመባል ብዙ ጊዜ ስለተጠራ ለማቴዎስ የገጸ-ሰብእ ምልክት ካሰጡት ምክንያቶች አንዱ ነው።

✍የጥ ተራ( ቁ) 2⃣✔  መልስ✔ ቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያና ወንጌላዊ እንደዚሁም ሰማዕት ነው። ቅዱስ ማርቆስ በአንበሳ ተመስሏል ጌታችንተብሎ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  አሸናፊው የይሁዳ አንበሳ  መሰየሙን በራዕይ ዮሐንስ ተጽፏል(፭) ቅዱስ ማርቆስ በአንበሳ የተመሰለበት ዐብይ ምክንያት ደግሞ በግብጽ የነበሩትን የአንበሳ ዕጓል አንበሳ የተባለውን ክርስቶስን በመስበኩ ነው።

✍የ ጥ ተራ(ቁ)✔ መልስ ✔ወንጌላዊ ቅዱስ ሉቃስ በላም ይመሰላል። መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከብቶች በረት መወለዱን በዕለተ ልደቱም የከብት እረኞች ከመላእክት ጋር መዘመራቸውን ከሌሎች ወንጌላውያን ሠፋ አድርጎ ስለሚተርክ ነው። ከዚህም ሌላ ላም በብሉይ ኪዳን የመሥዋዕት እንስሳ ሲሆን ሉቃስም የክርስቶስ መሰዋዕትነት በፊሪዳ ምሳሌ ጽፎታል። በዚህም መሰረት ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ክርስቶስ ቀርነ መድኃኒር እንደሆነ ነቢዩ ዘካርያስየተናገረውን ትንቢት በመግለጽ ስለፃፈ የላም ምልክት እንደተሰጠው መተርጒማን ሊቃውንት ይናገራሉ።



✍የጥ ተራ (ቁ) 4⃣✔መልስ✔ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በንስር ተመስሏል ንስር ከሌሎች አዕዋፍ ሁሉ ተለይቶ ወደ ላይ መጥቶ ይበራል። በላይም ሆኖ በመሬት ላይ ያሉትን ረቂቃን ነገሮች አጣርቶ መመልከት ይችላል። ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስም ሲጽፍ ከወንጌላውያኑ አፃፃፍ በተለየ በምሥጢረ ሥላሴ ይጀምራል ስለ ሥጋዌም ሲጽፍ ወደ ላይ መጥቆ በማሰብ ቅድመ ዓለም ስለነበረው ቃል ይተርክና ያ ቀድሞ የነበረውን ቃል ሥጋ ሆነ በማለት ይጽፋል። ቅዱስ ዮሐንስ ረቂቅና ጥልቅ የሆነውን ትምህርት ያስተምር ነበር።ለዚህም "እግዚአብሔር ፍቅር ነው። ክርስቶስ ሕይወት ነው።"የሚሉትን የመሳሰሉት ናቸው።

_ስለ ቃሉ የቃሉ ባለቤት ልዑል አምላካችን የተመሰገነ ይሁን አሜን፫_

*_አውቄው ሳይሆን ከአነበብኩት ገልብጨው ነው። ይልቁንም ከእናንተ የበለጠውን እማራለሁ_*

*ግልፅ ያልሆነ ነገር ካለ መጠየቅ ይችላል*

*ወስብኃት ለእግዚአብሔር*saramareyama.890@gmail.com

የ4ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የጠያቄና መልስ ውድድር

*✝_በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን_*

 *_አራተኛ (4) ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር_*

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕፀ መስቀል ላይ ሁኖ  ደሙ ሲፈስ የጌታዬ ደም እንዴት ይፈሳል አያለሁ ብሎ በጽዋ የተቀበለው ሊቀ መላእክት ማነው???.

*//መልስ//*

 ቅዱስ ኡራኤል ነው።

✅ ጥ ተራ (ቁ) 2⃣ አዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ከጻፈልን ከመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ የፍቅር ባህሪያትን ጥቀስ/ሽ

*//መልስ//*

ፍቅር👉 ይታገሳል፣ አይቀናም፣ አይመካም፣ አይታበይም፣አይበዳጭም፣ ሁሉን ያምናል።
1ኛ ቆሮ 13፥4 -7

✅ጥ ተራ (ቁ) 3⃣ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የእግዚአብሔር ቅዱስነት፣  ኃያልነት፣ አዋቂነት ጻዲቅነት፣ በጸሎቷ የመሰከረች ሴት/እናት ማናት/ማን ትላባለች??

*//መልስ//*

ቅድስት ሐና/ እመ ሳሙኤል ናት።

✅ጥ ተራ (ቁ) 4⃣ በአንዲት ትል ተበልቶ የመተው ንጉስ ማን ይባላል??

*//መልስ//*

ንጉስ ሄሮድስ

✅ጥ ተራ (ቁ) 5⃣ለመጀመርያ ጊዜ ማዕተብ ያሰረ አባት ማን ይባላል የምን ሀገር ተወላጂ ነው በስንት ዓመተ ምህረት ነው ማዕተብ ማሰር የተጀመረው??

*//መልስ//*.✍🏻

የሶርያ  ተወላጂ አባት ያዕቆብ አልበረዲ ናቸው 500-578 ዓ.ም ነው።

✅ጥ ተራም (ቁ) 6⃣ቤተክርስቲያን ሶስት በሮች አሏት። እነዚህ ሶስት በሮች የምን ምሳሌ ናቸው??

*//መልስ//*.✍🏻 የሶስቱ አበው አባቶች
የአብርሐም.የይስሀቅ. የያዕቆብ ምሳሌ ናቸው።

✅ጥ ተራ (ቁ)7⃣በቤተክርስቲያናችን ምንጣፍ እና መጋረጃ የምን ምሳሌ ናቸው??

*//መልስ.//*✍🏻ምንጣፍ.ምሳሌነቱ ለጌታችን  ሆሳዕና በአርምያ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የተባረከ ነው እያሉ የዘንባባ ዝንጣፊ ያነጠፉለት ምሳሌ ነው።

✅ጥ ተራ (ቁ)8⃣ጌታችንና ኢየሱስ ክርስቶስን ስዕለ አድህኖ መሳል ምክኒያት የሆነው ሠው ማን ነው??

*//መልስ//*.✍🏻በ14-37 ዓመተ/ምህረት ሮምን ይገዛ የነበረው "ጤባሬዪስ ቄሳር ነው።

✅ጥ ተራ(ቁ) 9⃣የመጀመርያው ኢትዮጵያ ጳጳስ በመሾም ወደ ኢትዮጵያ የተላከው የእስክንድርያ ፓትሪያርክ ማን ይባላል??

*/መልስ/*

✍ቅዱስ አትናቴዎስ

✅ጥ ተራ (ቁ)🔟ከትንሳኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታትን ስያሜን አስረዳ/ጅ??

*//መልስ//*

✍ሰኞ- ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡

ማክሰኞ- ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ስባለመመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29

ረቡዕ- አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡

ሐሙስ- አዳም ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡

አርብ- ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ አርብይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ ፡፡

ቅዳሜ- ቅዱሳት አንስት አልሞተምናይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ  ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
ለመቀባት
እሁድ- ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣1⃣በገነት ውስጥ ስንት አይነት ዛፎች ነበሩ??

*//መልስ//*

በገነት ውስጥ 3 አይነት ዛፎች ነበሩ እነርሱም፦👇

✍1ኛ ዕፀ መብል-እንዲበሉት የተፈቀደላቸው ምግብ

✍2ኛ ዕፀ በለስ -እንዳይበሉ የተዘዙት ነው።

✍3ኛ ዕፅ ሕይወት--እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ የሚመገቡት የዘለዓለም ሕይወትን የሚሰጥ ምግብ ነው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣2⃣እግዚአብሔር ሌሎች ፍጥረታትን አስጎንብሶ ሲፈጥራቸው አዳም አቀንቶ ለምን ፈጠረው??

*//መልስ//*

✍ሌሎችን ፍጥረታት አስጎንብሶ ሲፈጥራቸው አዳምን ለምን አቀንቶ ፈጠረው?፦

👉እርሱ ገዥ እናንተ ተገዥ ናችሁ ሲል ነው፣ እንዲሁም እናንተ ፈርሳችሁ በስብሳችሁ ትቀራላችሁ እርሱ ግን ትንሳኤ ሙታን አለው ሲል አቃንቶ ፈጠረው።

✅ጥ ተራ(ቁ) 1⃣3⃣በሐዋርያት ጊዜ የነበሩት ዲያቆናት ስንት ናቸው እነማን ናቸው???
ዲያ/መልስ/*

✍ሰባት (፯) ናቸው እነርሱም

1ኛ ቅዱስ እስሲፋኖስ

2ኛ ቅዱስ ጰርሜናን

3ኛ ቅዱስ ጵሮኮሮስን

4ኛ ቅዱስ ኒቃሮናን

5ኛ ቅዱስ ጢሞናን

6ኛ ቅዱስ ኒቆላዎስን

7ኛ ቅዱስ ፊልጶስን ናቸው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣4⃣መጽሐፈ መነኮሳት የሚባሉት ስንት ናቸው ስማቸውስ??

*//መልስ//*

✍መፅሀፈ መነኩሳት የባሉት ሦስት ናቸው ፦ከምንኩስና በፊትና ከምንኩስና በኋላ የሚነበቡ መፅሀፍት ሲሆኑ እነርሱም ሶስት ናቸው (1ኛ)ፊልኪስዩስ (2ኛ)ማሪስሀቅ እና(3ኛ)አረጋዊ መንፈሳዊ ናቸው።

✅ጥ ተራ(ቁ) 1⃣5⃣የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ወይም ወንጌል ከፃፉት ቅዱስ ማቴዎስና ቅዱስ ዮሐንስ ከሐዋርያት እንዲሁም ቅዱስ ሉቃስ እና ቅዱስ ማርቆስ ከአርድእት የሆኑበት ምክንያት ምንድን ነው??ለምስ ከሐዋርያት ብቻ ወይም ከአርድእት ብቻ አልፃፉትም??

*//መልስ//*

✔አራቱ ወንጌላውያን ሁለቱ ከአርድእት ሁለቱ ከሐዋርያት መሆናቸው (1ኛ)ስለአርድእት ክብር፦ሐዋርያት ጨርህገ ቢፅፉት አርድእት ለማስተማር በወጡ ጊዜ እኚህማ የውጭ ሰዎች ናቸው የውስጥ ሰዎች ቢሆኑማ ድርጊቱን ህገ ወንጌልን ይፅፉ ነበር ብለው አይሁድ ትምህርታቸውን  እንዳይከለከሉ (2ኛ)ስለወንጌል ክብር፦አርድእት ጨርሰው ቢፅፉት ይህችማ ተርታ ህግ ከመቀበልናት ድርጊቱማ  ሚስጥረ ተዓምራቱን በቤተ ኢያኢሮስ ሚስጥረ ፀሎትን በጌቴ ሰማኔ ሚስጥረ መንግስቱን በደብረ ታቦርሚስጥረ ምፅአቱን በደብረ ዘይት ባዩ ሐዋርያት ልብ ቀርታለች እያሉ አይሁድ ደገኛይቱን ወንጌል ከመቀበል እንዳይከለከሉ

✅ጥ ተራ(ቁ) 1⃣6⃣ማቴ 2፥5-6" ..አንቺ ቤተልሔም የይሁድ ምድር ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሽም ሕዝቤ እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣል"" ተብሎ ሚኪያስ(5፥2) የተነገረው ትንቢት በሐዲስ ኪዳን ከጌታችን ልደት ጋር ያለው ሚስጢራዊ ንፅፅር ምንድን ነው??

*//መልስ//*

✍(1ኛ)ለጊዜው ህዝቡን የሚጠብቅ መስፍን ዘሩባቤል ነግሶባታል ፍፃሜው ግን ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተወልዷል (2ኛ)ዘሩባቤል አህዛብ ገብረውለታል ለኢየሱስ ክርስቶስም ሰብአ ሰገል ገብረውለታል (3ኛ)ዘሩባቤል በቤተልሔም ድንኳን ተክሎባታል በክርስቶስ ጊዜም የብርሃን ድንኳን ተተክሎባታል ይህ ነው ምስጢራዊ ንፅፅሩ

✅ጥ ተራ(ቁ) 1⃣7⃣በብሉይ ኪዳን ለመጀመርያ ጊዜ ስዕል የሳለው ሰው ማን ይባላል የሳለው ስዕልስ ምን ነበር??

*//መልስ//* ✍በብሉይ ኪዳን ዘመን ለመጀመርያ ጊዜ ስዕልን የሳለው ሙሴ ሲሆን   ስዕልም ይህ ነው እግዚአብሔርም ሙሴን አለው ሁለት የድንጋይ ጽላቶች የሳለውእንደፊተኞች አድርገህ ጥረብ፤ በሰበርኸቸውም በፊተኞቹ ጽላቶች የነበሩትን ቃሎች እጽፍባቸዋለሁ። ዘፀ 34፥1-5 ስታነቡት ሙሉውን ታገኙታላችሁ።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣8⃣መጽሐፍ ቅዱስ ሁለት(፪) የኤማውስ መንገደኞች እያለ የሚጠራቸው ሰዎች ማን ማን ይባላሉ??

*/መልስ//*

✍ቅዱስ የሉቃስና ቅዱስ ቀለዮጳ (የሉቃ ወንጌል 24፥13_18 )ላይ ይገኛል

✅ጥ ተራ(ቁ) 1⃣9⃣ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰዓት ከአባቴ ብቻ በቀር ልጅም ቢሆን የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ የሚያውቅ የለም። ማቴ 24፥ 36 የዚህ ቃል አንድምታዊ ትርጉም አብራራ/አብራሪ)??

"""ስለዚያች ቀንና ሰዓት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም""" ማቴ24፥36 ይህንን በመጥቀስ ጌታ የሚመጣበትን ቀን አያውቅም ስለዚህ ሁሉን የሚያውቅ ሁሉን የሚችል አምላክ አይደለም የሚሉ መናፍቃን አሉ ነገር ግን ዮሀ ራዕ1፥8'""ያለውና የነበረው የሚመጣው ሁሉን የሚገዛ ጌታ አምላክ ""' በማለት ሁሉን የሚችል ከእርሱ በላይ ማንም የሌለ መሆኑን ይናገራል በተጨማሪም ጌታ በማቴ24፥1-55 ባለው የምፅአቱን ዋዜማ እንዴት እንደሆነ ግልፅ አድርጎ ተናግሯል ከዚህ የምንረዳው ነገር ቢኖር ክርስቶስ የሚመጣበትን ቀን ማወቁ ነው ታድያ ስለምን ልጅም ቢሆን አያውቅም አለ? (ሀ)ቀኒቱን ከአዳም ልጆችና እና ከመላእክት ሲለያት ነው እንጂ ከወልድና ከመንፈስ ቅዱስ ሲለይ አይደለም የሰው ልጅ ብሎ የአዳምን ልጆች ይጠራልና (ለ)አንድም ወልድ ቅድመ ተዋህዶ አላዋቂ የነበረን ስጋ እንደተዋሐደ ለማስረዳት በእውነት ጌታ የሰውን ባህሪ ባህሪው ማድረጉን ሊያስረዳን ፈልጎ ነው እንዲህ ሲባል ከተዋህዶ በኋላ ስጋ አላዋቂ ነው ማለት አይደለም ከመለኮት ጋር አንድ አካል አንድ ባህሪ ከመሆኑ በፊት ያለውን ሲናገር ነው እንጂ (ሐ)አንድም አብ ለልጁ በመስጠት አውቋታል ወልድ ግን በስራ አላወቃትም ይህም  ማለት ጊዜው እስኪደርስ በልቤ አኖራታለሁ በኋላ ግን በቃልነቴ እናገራታለሁ ሲል ነው አብ ልብ ወልድ ቃል መንፈስ ቅዱስ ህይወት ነውና በቃልነቱ በስራ የሚገልፅበትን ሲናገር ነው (መ)አንድም ወልድ ብቻ ያለ አብ አያውቃትም ሲል ነው ወልድ ከአብና ከመንፈስ ቅዱስ ተለይቶ አያውቃትም በባህሪ በማወቅአንድ ናቸውና ንባቡ '""ወልድም ቢሆን ያለ አብ ብቻውን""' ስለሚል ነው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 2⃣0⃣ ከሐዋርያት ውስጥ ሞትን ያልቀመሰው እና የተሰወረው ቅዱስ ማነው??

*//መልስ//*✍ቅዱስ ዮሐንስ ነው።

*_ውድ የተወደዳችሁና የተከበራችሁ እህት ወንድሞቼ ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አርሙኝ በማንኛውም ሰዓትና ጊዜ ለመታረም ዝግጁ ነኝ_*

*✍ወስብኃት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የ3ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር

*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!!የእግዝአብሔር ፍፁም ሰላም ይብዛላችሁ ይብዛልን_

*ሦስተኛ(3ኛ) ዙር የጠቅላል እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር* _እንደሚከተለው ነው_

_ጥ ተራ (ቁ) 1⃣"አንቺ ሴት ከአንች ጋር ምን አለኝ"? በሚለው ኃይለ ቃል ውስጥ ሴት የሚለው ቃል....ነው??

ሀ/ በእስራኤላውያን የትሕትና አነጋገር ነው።

ለ/ የቁጣ አነጋገር ነው።

ሐ/ ሥጋሽ ከሥጋዬ አጥንትሽ ከአጥንቴ ማለት ነው።

መ/ ሀ እና ሐ መልስ ነው።

*//መልስ//*

መ/ ሀ እና ሐ መልስ ናቸው።
1ኛ👉 በእስራኤላውያን የትሕትና አነጋገግ ነው።

2ኛ 👉አጥንትሽ ካጥንቴ ሥጋሽ ከስጋዬ ማለት ነው። ዘፍ 2፥23 ላይ ማየት ይላልቻ።።

 ጌታችንም  ድንግል ማርያምን አንቺ ሴት ማለቱ ከሥጋሽ ስጋን ከነፍስሽ ነፍስን ነስቼ አካልሽን አካል ባህሪሽን ባህሪ አድርጌ ሰው ሆኛለሁና ማለቱን የሚያመለክ የአክብሮትና የፍቅር ሐይለ ቃል እንደሆነ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን  ያስተምራሉ።

✅ጥ ተራ (ቁ) 2⃣ሃይማኖት ማለት ምን ማለት ነው? ሃይማኖት ከማን የተሰጠ ሥጦታ ነው??

*//መልስ/*

“ሃይማኖት ወይም እምነት” አምነ አመነ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ዘር ወይም ስም፤ ፤ ሲሆን ትርጉሙም አንድን እውነት መቀበል፤ በአንድ ክፍል ላይ ተስፋ ማድረግ ወዘተ ማለት ነው።
ስለ እምነት ወይም ሃይማኖት ምሥጢራዊ ትርጉም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚከተለው በግልጽ አስቀምጦታል፡
👉 “እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው” ዕብ.11፡1 በዚህ ቃል መሠረት እምነት ተስፋ የምናደርገው ነገር ሁሉ እርግጠኛ ስለመሆኑ፤ የማናየውንም ነገር የሚተርክ የሚያስተምር ነው።

በመቀጠልም ሐዋርያው “ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደተዘጋጁ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን” ዕብ.11፡3 ይላል ። በመሆኑም እምነት ስለፈጣሬ ዓለማት እግዚአብሔር ያለውን
እውነት እንዲሁም ከእርሱ ዘንድ ያለውን ተስፋችንን
የሚያስረዳ፤ የሚያረጋግጥልን እውነት፤ ሁሉንም የምናይበት የልብ መነጽር ነው። ስለዚህ መንፈሳዊውን  ለማወቅና የአምላክን  ለመሳተፍ ማመን እጅግ ተፈላጊና መሠረታዊ ነገር ወይም ምሥጢር ነው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 3⃣ቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ  ኢትዮጵያ ከሚለው መጠርያ ስሟ ሌላ ማን ማን እየተባለች ትጠራ ነበር??

*//መልስ//*
1ኛ👉የካም ልጅ ፉጥ በኢትዮጵያ ምድር ስለሚኖር #ፉጥ ተብላለች

2ኛ👉 ቶኔቶር ትባል ነበር ቶኔቶር ማለት ሀገረ እግዚአብሄር ማለት ነው።

 3ኛ👉ሊቀ ነብያት ሙሴ ኢትዮጵያን የኩሽ ምድር እያለ ይጠራት ነበር

4ኛ👉ኢትዮጲስ ተብላለች

5ኛ👉ሳባ የተባለ የኩሽ ልጅ ይኖርባት ስለነበር የሳባ ምድር ትባል ነበር

6ኛ👉ሰብታ ወይም አቢስ ይኖርባባት ስለነበር አቢሲኒያ ተብላለች

✅ጥ ተራ (ቁ) 4⃣ የአስራ ሁለቱ ሐዋርያት ሀገረ ሥብከታቸው የት የት እንደሆነ አስረዳ/ጂ??

*//መልሱን በድምፅ /ከቭዲዮመስዋት/ኦ/ አዳምጡ*

✅ ጥ ተራ (ቁ) 5⃣ በቅድስት ሃገራችን ኢትዮጵያ የኦሪት  የሚሰዋባቸው አብያተ ክርስቲያናትን ጥቀስ/ጥቀሽ??

*መልስ*

 (1ኛ)መርጡ ለማርያም

 (2ኛ)ተድባባ ማርያም

(3ኛ)አክሱም ፅዮን

 (4ኛ)ብርብር ማርያም

 (5ኛ)ጣና ቂርቆስ ናቸው

✅ጥ ተራ ( ቁ) 6⃣የጌታችን የመድኃኒታችን 9ኙ ባዕላት የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ/፦*

1ኛ👉�ፅንሠት
2ኛ 👉�ልደት
3ኛ👉�ጥምቀት
4ኛ👉� ደብረ ታቦር
5ኛ👉� ሆሳህና
6ኛ👉� ስቅለት
7ኛ👉� ትንሳኤ
8ኛ👉� እርገት.ክርስቲያን
9ኛ👉�ጲራቅሊጦስ ናቸው።

✅ጥ ተራ ( ቁ) 7⃣ቤተ  ክርስቲንያን ስንት ክፍሎች አሏት?? ምን ምን??

*//መልስ//*

1ኛ 👉መቅደስ
2ኛ 👉ቅድስት
3ኛ👉 ቅኔ ማህሌት

✅ ጥ ተራ (ቁ) 8⃣ ሰባቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ የተናራቸው ነገሮች(ሰባቱ አፅረሃ መስቀል የሚባሉት ምን ምን ናቸው??

*//መልስ/*👇

1,,, ኤሉሄ ኤሉሄ ለማ ሰብቅታኒ /አምላኬ አምላኬ ለምን ተውከኝ ,,,, ማቴዎስ 27፥40

2,,,አባት ሆይ የሚያደርገትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ....ሉቃስ 23፥39..

3,,, ዛሬ ከእኔ ጋር በገነት ትሆናለህ። ሉቃስ 23፥39

4,,, አባት ሆይ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ። ሉቃስ 23፥46...

5,,, እነሆ ልጅሽ...እነሆ እናትህ....ዮሐንስ 19፥26...

6,,,ተጠማሁ፣...ዮሐንስ እና፥28...

7,,,ተፈፀመ...ዮሐንስ 19፥30....

✅ጥ ተራ (ቁ) 9⃣ የቤተ ክርስቲያን አስራ አራቱ/14/ ቅዳሴዎች ምን ምን ናቸው???

*//መልስ//፦*

1ኛ፦ ቅዳሴ ሐዋርያት
2ኛ፦ ቅዳሴ እግዚእ.
3ኛ፦ ቅዳሴ ማርያም
4ኛ፦ ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጎድ
5ኛ፦ ቅዳሴ ሰለስቱ
6ኛ፦ ቅዳሴ አትናቴዎስ
7ኛ፦ ቅዳሴ ባስልዮስ
8ኛ፦ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
9ኛ፦ ቅዳሴ ኤጲፋንዮስዲዮስቆሮስ

10ኛ፦ ቅዳሴ ዮሐንስ አፈወርቅ
11ኛ፦ ቅዳሴ ቄርሎስ
12ኛ፦ ቅዳሴ ያዕቆብ
13፦ ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ
14ኛ፦ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ ካልዕ

✅ጥ ተራ (ቁ) 🔟 ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በእለተ ሆሳዕና  በአህያ ላይ ለምን ተቀመጠ? ለምንስ በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??

*//መልስ//*👇
👉�ትንቢትና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ እጅግ ደስ ይልበሽ። አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልእል በይ እነሆ ንጉስሽ ጻድቅና አዳኝ ነው። ትሑትም ሆኖ በአህያም በአህያይቱም ግልገል በውርንጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመልጣ (ዘካ 9፥9) እንዲል።

•ተንኮለኛ ናት ለጠላትዋም ፈረስ አውድቃ ረግጣ ትገድላለች
•ረጋ ብላ መሄ አችልም ትቸኩላለች
•ልትወጣባት ስትልም ታስቸግራለች አትመችም ተነጣጥረህ ነው የምትወጣባት
•ጌታ የወደደውና በትንአምላክ አህያን መረጠ፡፡

በአህያ መቀመጡ
እደተገለጸው•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝብለው ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ መእመናን አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ  ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ፤እኛ በትእቢት ተይዘን ነው እንጂ በየዋህነት ብንመላለስ እሱ ያድርብን ነበር፡፡ እኛ የእግዚአብሔር ማደርያ ነንና፡፡

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣1⃣ጌታችን በመጣ ጊዜ የምንጠየቃቸው "6"ቃላተ ወንጌል የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ//*
 👉ተርቤ አላበላችሁኝምምዕራፍ

👉ተጠምቸ አላጠጣችሁኝም

👉 የማቴዎስ ወንጌል  25፥33 -46 ላይሙሉውን መመልከት ይቻላል።

✅ ጥ ተራ (ቁ)1⃣2⃣ በ186 ዓ.ም በፍቼ የተወለዱና ከኢትዮጵያ የመጀምርያ አራት ጳጳሳት አንዱና የምሥራቅ ኢትዮጵያ ጳጳስ የነበሩት። በኋላም ፋሺስት ኢጣሊያ በ1928 ዓ.ም በኢትዮያ ላይ የግፍ ጦርነት ባነሳ ጊዜ እምቢ ለሃገሬ ለሃይማኖቴ በማለታቸው ሐምሌ 22 ቀን 1928 ዓ.ም በፋሽስት ኢጣሊያን ሰማዕትነት የተቀበሉት ታላቅ አባት ማን ይባላሉ??

*//መልስ//* 👇

ታሪካቸውን የማንዘነጋው ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣3⃣ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "በኩር" የሚባልበት ምክንያት

ሀ/የአብ አንድያ ልጁ ስለሆነ

ለ/ በእስራኤላውያን መጀመርያ ማኅፀን የሚከፍት ልጅ በኩር ስለሚባል

ሐ/ ሞት የማይገዛው ትንሣኤን ለመነሣት እርሱ የመጀመርያ ስለሆነ

መ/ ሁሉም መልስ ነው።

*// መልስ//*

መ/ ሁሉም

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣4⃣እመቤታችን በስደቷ ወቅት ኢትዮጵያ ውስጥ ረዘም ላለ ጊዜ ያረፈችበት ቦታ__ይባላል??

*//መልስ//*

በጣና ደሴት ሦስት ወር ከአስር(10)ቀን ቆይታለች

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣5⃣የቃል ኪዳኑ ታቦት ከማይነቅዝ እንጨት የተሰራና ከውስጥም ከውጭም  በወርቅ የተለበተ መሆኑን፤ የሚያስረዳን የቅዱስ መጽሐፍ ክፍል የትኛው ነው??

*//መልስ//*

ዘጸ.25፥1-22 ላይ ይነግረናል።

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣6⃣የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የሐዋርያትን ትምህርት 81 የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የምትቀበል ስትሆን ሦስቱን  አብያተ ክርስቲያን ጉባኤያትንም ትቀበላለች። የምትቀበላቸውን የጉባኤያትን ስም ጥቀስ/ጥቀሽ

*//መልስ//*👇
ኒቂያ  ጉባኤ ፣ ቁስጥንንጥንያና አፌሶን ናቸው የነዚህን ጉባኤያት ውሳኔዎቻቸውን ትቀበላለች። ሌሎች ጉባኤዎችን አትቀበልም።

✅1⃣7⃣የሙሴን ሕግ በብዙ ጥንቃቄ እንተረጉማለን የሚሉና ሰውም ሕጉን እንዳይተላለፍ በማለት የራሳቸውን ትእዛዝና ሥርዓት ያወጡ በዘመነ ካህናት ጊዜ የነበሩ የቤተ  ክርስቲያን ጠላቶች ምን ተብለው ይጠራሉ??

ሀ/ ፈሪሳውያን

ለ/ ሰዲቃውያን

/ ኤሲያውያን

መ/ አይታወቁም

*//መልስ//*

ሀ/ ፈሪሳውያን የሐዋርያት 👉 ሥራ 15÷5 ላይ ይገኛል

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣8⃣አስራ ሦስቱ/ 13/ የጌታችን ህማማተ መስቀል የምንላቸው ምን ምን ናቸው??

*//መልስ//*

13ቱ ሕማማተ መስቀል

1ኛ. ተአስሮ ድኅሪት (ወደኋላ መታሰር)
2ኛ. ተስሕቦ በሐብል (በገመድ መሳብ)
3ኛ. ወዲቅ ውስተ ምድር (በምድር ላይመውደቅ)
4ኛ. ተከይዶ በእግረ አይሁድ (በእግረ አይሁድመረገጥ)
5ኛ. ተገፍዖ ማዕከለ ዓምድ (ከምሶሶ ጋርመላተም)
6ኛ. ተጽፍዖ መልታሕት (በጥፊ መመታት)
7ኛ. ተቀሰፎ ዘባን (ጀርባን በጅራፍ መገረፍ)
8ኛ. ተኰርዖተ ርእስ (ራስን በዱላ መመታት)
9ኛ. አክሊለ ሦክ (የሾህ አክሊል መድፋት)
10ኛ. ፀዊረ መስቀል (መስቀል መሸከም)
11ኛ. ተቀንዎ በቅንዎት (በችንካር መቸንከር)
12ኛ. ተሰቅሎ በዕፅ (በመስቀል ላይመሰቀል)
13ኛ. ሰሪበ ሐሞት (መራራ ሐሞትንመጠጣት)ጊዜ

✅ጥ ተራ (ቁ) 1⃣9⃣በሐዋርያት ጊዜ  የነበሩ የመጀመርያዎቹ  መናፍቃን ምን ተብለው ይጠራሉ??

ሀ/ ግንስቲኮች

ለ/ ቢጽ ሐሳውያን

/ አርዮሳውያን

መ/ ሁሉም

*//መልስ//*
*ለ/*👉ቢጽ ሐሳውያን ሐሰተኛ ወንድሞች ይባሉ ነበር። እነዚህም መናፍቃን ከአይሁድ ወገን ክርስትናን በመቀበል ካመኑና ከተጠመቁ በኋላ ተመልሰው ወደ አይሁድ ሃይማኖት ያዘነበሉ ናቸው።

✅ ጥ ተራ (ቁ) 2⃣0⃣ የግዝት በዓላት የማባሉት ስንት ናቸው?? ምን ምን ?

*//መልስ//*👉� አምስት (5) ናቸው
 1ኛ👉� የወልድ በዓል ወር በገባ በ29 ቀን
2ኛ👉�የመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓል ወር በገባ በ21
3ኛ👉�የመላአኩ ቅዱስ ሚካኤል በዓል ወር በገባ በ12 ቀን
4ኛ👉�እለተ ቅዳሚት ሰንበት
5ኛ👉�እለተ እሁድ ሠንበት ክርስቲያስቲያን ናቸው።

_ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ካለበት አረሙኝ ለመታረም ዝግጁ ነኝ_
.
_ወስብሐት ለእግዚአብሔር_saramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...