2017 ኖቬምበር 22, ረቡዕ

የምዕራፍ ሁለት(የ17ኛ) ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ውድድር

*በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፫*

_ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ሰነበታችሁ?? ሰላማችሁ ይብዛ!!_

_፨የምዕራፍ ሁለት/17ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር 

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
_↪ ጥ.ተራ (ቁ)1⃣✍ ቅዱስ ሉቃስ ስንት መጻህፍት ጽፏል ❓_
   _፨መልስ፨  መልስ ሁለት የሉቃስ ወንጌል እና የሐዋሪያት ስራ።✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)2⃣✍ ቅዱስ ሉቃስ ወንጌሉን የጻፈው ለማን ነው❓_

       _፨ መልስ ፨ለቅዱስ ቴዎፍሎስ_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ) 3⃣✍ለመጀመርያ ጊዜ ስዕለት የተሳለ አባት ማን ይባላል❓_

         _፨መልስ፨ አባታችን ያዕቆብ ነው ዘፍጥረት 28፥20_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)4⃣✍ ሄኖክ ማለት ምን ማለት ነው?? መጽሐፈ ሄኖክስ በስንት ዓ.ም ተጠረዘ❓_

       _፨መልስ ፨ሄኖክ ማለት አዲስ ማለት ነው።ሲሆን መጽሐፈ ሄኖክ በ4014 አመተ አለም ቅድመ ልደት ክርስቶስ ነው የተፃፈው። የተፃፈበት ቦታ ደብረ ቅዱስ ይባላል ይህ ቦታ ከገነት ትዮዩ የሆነ ቦታ ነው።_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ) 5⃣✍ከሚከተሉት  ከ፲፪(ከአስራ ሁለቱ)የሐዋርያት ወገን  የቱ ነው❓_

ያልሆነውሀ) ጳውሎስ 
ለ) ጴጥሮስ
ሐ) በርተሎሜዎስ
መ) ዮሐንስ

       _፨መልስ፨ ሀ) ጳውሎስ ✅_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)6⃣✍ሐዋርያ ማለት ምን ማለት ነው❓_

ሀ) የተላከ 
ለ) ልዑክ 
ሐ) ሂያጅ 
መ) ሁሉም መልስ ነው

        ፨መልስ፨መ) ሁሉም መልስ ነው ✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)7⃣✍ቅዱስ ሉቃስ ማነው❓_

_ሀ. ወንጌላዊ ነው_
_ለ. ሰአሊ ነው_
_ሐ.  ሀኪም ነው_
_መ. ከ 72 አርድት መካካል ነው_
_ሰ. ሁሉም መልስ ነው_

        ፨መልስ፨.........መ) 

_↪ጥ.ተራ(ቁ)8⃣✍ የብሔረ ብፁሀንን ታሪክ የፃፈው አባት  ማን ይባላል ❓_
 _የፃፈው ቅዱስ አባትስ ከብሔረ ብፁሀን ሲመለስ ምን አጋጠመው❓_ያጋጠመው

       ፨ መልስ፨
 ቅዱስ ዞሲማስ ነው። ሲመልስ 
 ከሰራዊቱ ጋር    ሁኖ ሲመለስ ዲያቢሎስ የብሔረ ብፁሀንን ታሪክ  መጽሐፍንም  ሊወስድበት ከጀለ ነገር ግን በእግዚአብሔር  እና በመላእክትናን ተራዳኝነት ሰይጣንን ድል አድርጓል። ✅


_↪ ጥ.ተራ(ቁ)9⃣✍በኃጢአያት  የሚያደርገን ምንድነው❓_

_ሀ/  ምክንያተኝነት_
_ለ/  ለመንፈሳዊ ነገሮች ያለንን ከበሬታ መቀነስ_
_ሐ/  ወደ ኃጢአያት የሚመራንን ነገር አለማቑረጥ_
_መ/  ሁሉም መልስ ነው_ዳዊት


         _፨መልስ፨ መ/ ሁሉም  ነው።✅_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)🔟✍ከአብረሀም እስከ  ያለው ዘመን ምን ይባላል❓_

_ሀ/  ዘመነ አበው ይባላል_
_ለ/  ዘመነ ነቢያት ይባላል_
_ሐ/  መልሱ የለም_

          _፨መልስ፨ ሀ/ ዘመነ አበው  ይባላል።_✅

_↪ጥ.ተራ(ቁ)1⃣1⃣✍በሙሴ ስም ከሚጠሩት ቅዱሳንይ መካክል የምታውቀውን ጥቀስ/ሽ❓_


        _፨መልስ፨_👇
1-ሊቀ ነቢያት ሙሴ 
2-አቡነ ሙሴ ዘድባ 
3-አቡነ ሙሴ ዘገርአልታ 
4-ሰማዕቱ አቡነ ሙሴ 
5-አቡነ ሙሴ ዘትግራይ
6-አቡነ ሙሴ ጸሊም
7-አቡነ ሙሴ ዘቡልጋ
8-አቡነ ሙሴ ዘገዳመ ሲሐት

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣2⃣✍ዮሴፍ የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ ድንግል ማርያምን  አላወቃትም፤ ሲል ምን ለማለት ነው❓_

        _፨መልስ፨_👇
_ _፦ድንግል ማርያም ንጹሕ ብርሌን_ _ትመስላለች:: ብርሌ_
_የተለያየ ቀለም ያለው ፈሳሽ_ _ቢያስገቡበት ቀለሙ አብሮ_
_ይቀያየራል:: እመቤታችንም_ _ጌታን ጸንሳለችና ሕብረ_
_መለኮቱ ሲለዋወጥ መልኩዋ_ _አብሮ ሲለዋወጥ እያየ_
_ዮሴፍ ይደነግጥ ነበር::_

_+'እርሷ ማን ናት? በማሕጸኗ። __ያለውስ ማን ነው?' _እያለ_
_ይጨነቅ ነበር:: ጌታን_ ከወለደች_ _በሁዋላ ግን አንድ_
_ሕብረ መልክ ሆናለችና::_ _አስቀድሞ ማን እንደ ነበረች_
አላወቀም::_

_+አሁን ግን ልጇ አምላክ_ _ዘበአማን: እርሷም ወላዲተ_
_አምላክ መሆኗን አወቀ ማለት ነው።✅_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣3⃣✍_
_በታምረ ማርያም ፀሎት ላይ 3_ _ጊዜ እሰግድ ለኪ(3)!_
_ብለን እንሰግዳለን፣ይህንን_ _ሰግደት ያሰተማረን ቅዱስወርቅ አባት_ _ማን ይባላል❓_እንዴትስ ተጀመረ❓

      _፨መልስ፨_✍
 _ዮሀንስ አፈ  አሀዛብን በሚያስተምርበት ወቅት የእመቤታችን ስዕል አፍ አውጥታ "አፈ ወርቅ! ልሳነ ወርቅ! አፈ በረከት!" ስትል ተናገረች… እርሱም ታጥቆ 3 ጊዜ የሰገደላትን ለማስታወስ ነው።_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣4⃣✍የሚስጥረ ትንሳኤ ሙታን አፈፃፀም ከመፃፍ ቅዱስ ውስጥ ቅዱስ ጳውሎስ ከፃፈው ሁለቱን ጥቀሱ ❓_
           _፨መልስ፨_👉ወደ ኤፊ_ 2፥1 በበደላችሁና _በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ በእነርሱም በዚህ አለም እንዳለው ኑሮ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሰራው መንፈስ አለቃ እንደኮነው በአየር ላይ ስልጣን እንዳለው አለቃ ፍቃድ በፊት ተመላለሳችሁባቸው_ 

 _ሮሜ 1፥4_
_ይህም ወንጌል በስጋ ከዳዊት_ _ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና_ _መንፈስ ግን ከሙታን መነሳት_ _የተነሳ በሀይል የእግዚአብሔር_ _ልጅ ኮኖ ስለተገለጠ ስለ ልጁ_ _ነው እርሱም ጌታችን ኢየሱስ_ _ክርስቶስ ነው።_
_ሮሜ 1 ፥3-4ይህም ወንጌል በሥጋ ከዳዊት ዘር ስለ ተወለደ እንደ ቅድስና መንፈስ ግን_ _ከሙታንሥራው መነሣት የተነሣ በኃይል የእግዚአብሔር ልጅ ሆኖ ስለ ተገለጠ ስለ ልጁ ነው፤ እርሱም ጌታችን ኢየሱስ_ _ክርስቶስ ነው።_

_2ኛ ቆሮ 1፥9 ወዘተ..._✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣5⃣✍እግዚአብሔር የመንገዱ መጀመሪያ አደረገኝ፥ በቀድሞ  መጀመሪያ…ከጥንቱ *ከዘላለም* ጀምሮ_ *_ተሾምሁ* ፤ ምድር _ከመፈጠርዋ_ አስቀድሞ።_
_ቀላያት ገና ሳይኖሩ እኔ_ _*ተወለድሁ* ፥ የውኃ ምንጮች ገና ሳይፈልቁ… ተራሮች ገና_ _ሳይመሠረቱ፥ ከኮረብቶች በፊት_ _*እኔ ተወለድሁ፥* የሚለውን ቃል *እግዚአብሔር ወልድ* ከተጥንት ከአባቱ ከእግዚአብሔር አብ_ _*መወለዱን* በመንፈስ ቅዱስ የገለፀለት ቅዱስ ማን ይባላል❓_

   _፨መልስ፨_......ንጉሥ   ሰሎሞን ነዉ።
መፅሀፈ ምሳሌ ምዕ8:22—23

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣6⃣✍*1*/, ነብዩ ኤርሚያስ አገልጋዩን ጠርቶ ለንጉስ ኢዮአቄም ትንቢቱን እንዲያነብለት አዘዘው፤ይህ የኤርሚያስ አገልጋይ ማን ይባላል ?ንጉስ ኢዮአቄምስ ትንቢቱን ሰምቶ ምን አደረገ❓_
   _ፍንጭ ኤር(36፤23)_

             _፨መልስ፨_👇
_~የኤርሚያስ አገልጋይ ባሮክ ሲሆን ንጉሱም ትንቢቱን ሰምቶ በእሳት አቃጠለው ፤እሱም ተቀሰፈ_

_ባሮክም ትንቢቱን ከኤርሚያስ  እንደገና ፃፈው_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣7⃣✍በአንድ ወቅት የሶርያው ንጉስ በብዙ ሺ ሠራዊት  እስራኤልን ከበበ ፤የኤልሳ ደቀመዝሙር የነበረው ግያዝም የሰራዊቱን ብዛት አይቶ ጌታዬ ዛሬስ መጥፋታችን ነው ! እያለ ጮህ ይህን ግዜ ኤልሳ ለግያዝ ምን አለው ? ልባምላክ ዳዊትስ ይህን በተመለከተ በመዝሙሩ ላይ ''ይትዓየነን መልአክ እግዚአብሔር አውዶሙ ልእለ ይፈርሆ ወይአድሃኖሙ'' ብሎ ዘመረ ምን ማለት ነው❓_
   _ፍንጭ 2ኛ ነገስት (6፤16)፣(መዝ 33፤7)_

       _፨ መልስ፨_👇
_ከእኛ ጋራ ያሉት ከነርሱጋር_ _ካሉት ይበልጣሉና አትፍራ_
_1ኛ ነገስት (6፤16)_✅

_↪ጥ.ተራ (ቁ)1⃣8⃣✍እኛ ከየት ይሆን የተጠራነው እንደ ኤርሚያስ ከማሀፀን ? ወይስ ከአለም እቅፍ ?ከሀጢያት ባሀር ወይስ ከሞት አፋፍ ? ከአፈር እና _ከትብያ ላይ ወይስ ከምን_ _ይሆን የተጠራንው_
_ሙሴ እና ዳይት_ _ከእረኝነት፤ጴጥሮስን እና_ _እንድርያስን ከአሣ አጥማጅነት_ _የጠራ እግዚአብሔር ኤልሳዕን_ _ከምን ነበር የጠራው ?_በሬ _ጳውሎስ እና ሙሴ ፀሊምንስ❓_

          _፨መልስ፨_
_ኤልሳዕን 12 ጥማድ  እያረሰ ፤_
_ጳውሎስን ካሳዳጅነት ፤ሙሴ_ _ጸሊምን ከሽፍታነት_

_↪ ጥ.ተራ (ቁ)1⃣9⃣✍በቅዳሴ ላይ እንዲህ እያልን_ እናመሰግናለን_ _ሱራፌልይጸርውሁ ይሰግዱ_ _ሎቱ ወክሩቤል ይሴብሕዎ _ _እንዘይበሉ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ_ _እግዚአብሔር ,,,ይሄንን_ _ምስጋና በመፃፍ ቅዱስ የትኛው ምእራፍ ላይ እናገኘዋለን ❓_

                _፨መልስ፨_👇
_በትንቢተ ኢሳያስ ምእራፍ 6 ላይ ነው ፤ወንጌሉ እና ቅዳሴው እርስ በራሳቸው ይናበባሉ ለእያንዳዱ የቅዳሴ ዜማ እራሱን የቻለ የመፃፍ ቅዱስ ጥቅስ አለው።_

_↪ጥ.ተራ (ቁ)2⃣0⃣✍ዲያቆናቱ በቅዳሴ ላይ ስለዝናብ እንማልዳለን ፣ስለተጨነቀች ነፍስ እንማልዳለን ፣ስለታመሙ እና ስለድዊያን እንማልዳለን ---እያሉ ይጸልያሉ ፤ንጉስ ሰለሞን ቤተክርስቲያንን ከሰራ ቡሀላ እራሱ እንደ ዳቆን ሆኖ ይህንን ፀሎት ጸልዮ ነበር ፣እግዚአብሔር ለዚህ ጸሎት የሰጠው ምላሽ ምን ነበር ❓_
  _ፍንጭ 1ኛ ነገስት (8፤35)፤_ _1ኛ ነገስት (9፤3)_

            _፨መልስ፨_👇
_በፊቴ ያቀረብከውን ልመናና ፀሎት ፤አይኖቼ እና ልቤ ዘወትር ወደ ሰራከው ቤተመቅደስ ይሆናሉ   1ኛ ነገስት (9፥3)_✅
.890@gmail.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...