2018 ፌብሩዋሪ 27, ማክሰኞ

የእንቆቅልሽ/ህ መረሀ ግብር

⏩እንቆቅልሽ
     ✍🏾ምን አውቅልሽ❓
የጌታዬን ፊቱን በጨርቅ ባብስ
መልኩ ተስሎበት ያገኘሁት ወደ ቤቴ ስደርስ እኔ ማን ነኝ?

   *መልስ*✍🏾የጲላጦስ ሚስት  ቬሮኒካ ነሽ።

✍🏾 እንቆቅልሽ

     ⏩ምን አውቅልሽ❓
✍🏾ቢበሉት ቢጠቱን የማያልቅ
ቢለብሱት የማያረጅ ቢሸከሙት የማይከብድ
ከጨለማ ከዓለም የሚያላቅቅ
ከክፉ የሚያድን የሚጠብቅ ምንድነው ታውቂዋለሽ?

  *መልስ*⏩ ላመነ ለተቀበለ ለተረዳው
ልቡን ላስማረከ ላላቅማማው
ጠላትን መዋጊያ ጋሻ ጦር ወንጌል ነው

⏩እንቆቅልሽ
     ✍🏾ምን አውቅልሽ❓
⏩በፋሲካ ምሽት ጌታን አሳልፎ የሚሰጠው ማን እንደሆነ የጠየቀ
የወንጌሉ ቋንቋ ፅር የሆነ
በህይወቱ መጨረሻ በእስያ ሀገር በኤፌሶን ያስተማረ  ይሄ ቅዱስ ማን ነው

*መልስ*✍🏾ወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ ነው።

✍🏾 እንቆቅልሽ
     ⏩ምን አውቅልሽ❓

✍🏾የሰማዕታትን መከራ ተጋድሎቸውን አይታ
ለመኖር የወሰነች እንደእነርሱ ጸንታ
መኮንኑ ወብቷን አይቶ
አልፈልግም ስትለው እጅግ ቢያሰቃያት መከራን አብዝቶ ሥገዋን
 ተልትለው ዘቅዝቀው  ሲሰቅሏት
 መልሰው በፈላ ውሃ ሲከቷት
ከሰማያት አክሊል በነጭ እርግብ አምሳል
የወረደላት ያም ውሃ ጥምቀት የሆነላት
ይቺ ቅድስት እናት ማናት ታውቂያታለሽ❓

*መልስ*⏩የጣኦት አምላኪው የዳኪዎስ ልጅ
በአንፆኪያ ተወልዳ ያደገች
በዕስር ሆና ዘንዶ ውጦ የተፋት
ሴጣንን በፀጉሩ ይዛ የቀጠቀጠች
ጌታ ቃል ኪዳንን የገባላት
እናታችን ቅድስት መሪና ናት

⏩እንቆቅልሽ
     ✍🏾ምን አውቅልሽ❓

⏩አውሬ ከባህር ሲወጣ አየሁ!
ባህር የተባለው ማነው?
አውሬውስ ማን ነው?

  *መልስ*✍🏾ይሄ አለም ሲሆን  ባህር የተባለው
አውሬው ደግሞ የሰው ልጅ ባህሪ ብሎም ሀሳዌ መሲህ ነው!!

✍🏾 እንቆቅልሽ
     ⏩ምን አውቅልሽ❓
✍🏾 ጌታ ሲጠራው 56 ዓመቱ
ከአለም ሲለይ ዕድሜው ሰማንያ ስምንት
መሰረተ ቤተክርስትያን የተባለ
በ66ኛው ክፍለ ዘመን  ሰማዕትነት የተቀበለ?

*መልስ*⏩እኔስ እንደ አምላኬ ሽቅብ አትስቀሉኝ
ስለማይገባኝ ከዕርሱ አታወዳድሩኝ
ባይሆን ስለ ፍቅሩ መሞቴ ካልቀረ
እራሴን ወደታች ዘቅዝቃችሁ ቸንክሩኝ
በማለት በሮም አደባባይ ህይወቱን የሰጠ
ፍቅሩን እስከመስቀል ይዞ የዘለቀ
አባታችን ቅዱስ ጴጥሮስ ነው

⏩ እንቆቅልሽ
     ✍🏾ምን አውቅልሽ❓
⏩እመቤታችን ፊደል ናት ምክንያቱም
ወንጌልን ስለወለደችልን
መባረክ የጀመርንባት
ወደቤተ መቅደስ መግባት ያስተማረችን
የእናት መጀመሪያዋ 
ትህትናን ያስተማረችን እርሷ ስለሆነች ያለው ቅዱስ ማን ነው❓

*መልስ* አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ

✅ @Teyakaenamels
✅ @Teyakaenamels
✅ @Teyakaenamelssaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ ሦስት/የ24ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን አላችሁ?? እነሆ.... የምዕራፍ ሦስት/የ23ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል  መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር።

 ✅✍ጥ.ተራ ቁ👉1⃣ጌታ ቅዱሳን ሐዋርያትን ወደ ዓለም ዳርቻ ለወንጌል አገልግሎት ሲልካቸው ስንት ስንት አድርጎ ነው??

//መልስ//፡- ሁለት ሁለት አድርጎ ነው፡፡ ማቴ.10÷1

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉2⃣ነቢዩ ኤልያስ ፣ ፃድቁ ሄኖክ ፣ ዮሐንስ ወንጌላዊ እስከ ዕለተ ምጽአት የሚቆዩበት ቦታ ምን ይባላል?

///መልስ//፡- በብሔረ ሄዋን ነው፡፡

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉3⃣የጌታችንን ሥነ ስቅለት የሳለው ማን ነው ?የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምንስ?

//መልስ//፡- ወንጌላዊው ዮሐንስ እና ቅዱስ ሉቃስ ናቸው፡፡

 ✅✍4⃣አንድ ሰው ሱባኤ ገባ ሲባል ምን ማለት ነው? አንድ ሱባኤስ ስንት ቀን ነው?

//መልስ//፡- ከእግዚአብሔር ጋር ለመነጋገር ከሰው ተለይቶ ቤቱን ዘጋ፣ጸለየ ማለት ሲሆን አንድ ሱባኤ ሰባት ቀን ነው።

 ✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉5⃣የመጀመሪያዋን የኢየሩሳሌምን ቤተመቅደስ  ሰው ማን ነበር? ያፈረሰውስ ማን ነው??

//መልስ//፡- ጠቢቡ የሠራውሰሎሞን ሲሆን ያፈረሰው የባቢሎኑ ንጉሥ ናቡከደነፆር ነው።

 ✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉6⃣ሩሐማ ማለት………ምን ማለት ነው??…. ሎሩሃማ ማለትስ………… እና ናታኒም ማለት …………. ምን ማለት ነው??

//መልስ//. ሩሐማ ማለት………….  ማለት………… እና ናታኒም ማለት …………. ነው፡፡
መልስ፡- ሩሐማ ማለት ምሕረት የሚገባት ሎሩሃማ፣ሎሩሃማ ማለት ምሕረት የማይገባት ሲሆን ናታኒም ደግሞ የቤተመቅደስ አጽጂ ማለት ነው፡፡


✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉7⃣የነቢዩ ዮናስ አባት አማቴ እንደሚባል በመጽሐፍ ቅዱስ ተገልጻል አማቴ ማለት በዕብራይስጥ ምን ማለት ነው??

//መልስ//👉አማቴ በዕብራይስትጥ እውነት ወይም እውነት ተናጋሪ ማለት ነው።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ.8⃣ነብዩ ዮናስ  ወደ ተርሴስ ሲኮበልል የተሳፈረበት  የኢዮጴ ወደብ ዛሬ የት ይገኛል ስሙስ ማን ይባላል???

//መልስ// ከጤግሮስ  ወንዝ በስተምስራቅ  በአዲሲቷ ሞስል ከተማ  በተቃራኒ ትገኛለች ነነዌ ማለት የዮናስ ከተማ ማለት ሲሆን እሱም ናምሩድ ነው።

.✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉9⃣ነብዩ ዮናስን የዋጠው  ዓሳ ነባሪ በየት በየት አድርጎ  ተጉዞ ነቢዩን ነነዌ ከተማ ዳር ተፋው??

//መልስ//👉ዮናስ ከኢዮጴ ወደብ ተሳፍሮ ወደ ተርሴስ/ስፔን/ ሲጓዝ
ወደ ባህር ተጥሎ በዓሳ አንበሪ ሆድ ውስጥ ለሶስት ቀን
ቆይቶ ነነዌ ከተማ ጥግ ሊተፋ  የዋጠው ዓሳ
ነባሪ በሜድትራያንን ባህር አድርጎ…..በምዕራብ አፍሪካ
አድርጎ..በደቡብ አፍሪካ በኩል የቻለውዞሮ…ነው፡፡ ነነዌ/አሁን
ኢራቅ ውስጥ ነው የሚገኘው/ ከተማ ጥግ
የተተፋው….ለምን በቀይ ባህር  አያልፍም ቢሉ…
ሁለቱን አሀጉራት የሚያገናኘው ቦታ ያኔ ደረቅ ሲሆን
በዕርግጥ አሁን ተቆፍሮ የስዊዝ ካናል ተሰርቶበታል።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉🔟የጋብቻ ዋና ዓላማ ምንድን ነው??

//መልስ//👉የጋብቻ ዓላማ
የጋብቻ ዓላማዎች ሦስት ናቸው፡
1. የመጀመሪያው “የሚመቸውን  እንፍጠርለት” እንዲል ለመረዳዳት ነው። መረዳዳት ሲባልም በሥጋ ብቻ አይደለም በነፍስም ጭምር ነው። ለሥጋቸው በሥራ ሲረዳዱ ረዳትለነፍሳችው ደግሞ በጸሎት ይረዳዳሉ። ለምሳሌ ይስሐቅ ሚስቱ ርብቃ ለሃያ ዓመታት መክና ልጅ አልወለደችለትም ነበር። በዚህም ምክንያት ስለ ርብቃ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ፤ እግዚአብሔርም ተለመነው፤ ርብቃም መንታ ፀነሰች ይላል።  ፳፭፡ ፳፩።

2. ሁለተኛው ከፍትወተ ሥጋ ወይም ከዝሙት ለመጠበቅ። ፩ኛ ቆሮ ፯፡ ፰ - ፱፤ ፩ኛ ቆሮ ፭፡ ዘፍ፩፤ ምሳሌ ፮፡ ፴ - ፴፪።

3. ሦስተኛው ደግሞ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፤ እግዚአብሔርም ባረካቸው፤ እንዲህም አላቸው “ብዙ ተባዙ፤ ምድርንም ሙሏት” እንዲል ዘር ለመተካት ነው። ዘፍ ፩፡ ፳፰። እነዚህም እንደ ሦስት ጉልቻዎች የሚቆጠሩ ናቸው።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣1⃣ ሥላሴ ለቅዱሳን በፈለጉት መልክ የሚታዩት (የሚገለጡት)በየትኛው ሰማይ ሆነው ነው?


//መልስ//👉 መንበረ ስብሐት


 ✅✍ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣2⃣ለመናብርት አለቃ ሆኖ የተሰየመው መልአክ ማን ነው?

//መልስ//🖊ቅዱስ ሩፋኤል

✅✍ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣3⃣ቅዱስ ሉቃስ ጌታን ከመከተሉ በፊት ሥራው ምን ነበር??

//መልስ//👉ዶክተር/ሃኪም ነበር።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣4⃣እግዚአብሔር ከመልከ ጼዴቅ ጋር ያደረገው ኪዳን ምንድን ነው??

//መልስ//👉መልከ ጼዴቅ የእግዚአብሔር ካህኑ  ምሳሌው የሆነ የሳሌም ንጉስ ነው በ15 አመቱ መንኖ አጽመ አዳምን ይዞ በቀራንዮ በህብስትና በወይን. ያስታኩት ነበር. እግዚአብሔር የክርስቶስምለመልከ ጼዴቅ በሐድስ ኪዳን ለምትሰራው ክህነትና ምስጢር ቁርባን ምሳሌ. አድርጎ በቃል ኪዳን አትሞታል በዚሕም ተሰውሮ ይኖራል እንጂ. ሞትን እስካሁን አልቀመሰም. ይህም ካሕኑ መልከ ጼዴቅ. ከአብርሃም ጋር በተገናኙበት  ጊዜ ተገልጧል.  ዘፍ 14፡17 እና ዕብ 7፥1

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣5⃣ቅዱስ ሉቃስ ለምን ዘላህም/ላም እየተባለ ይጠራል??

//መልስ//👉 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በበረት፣በላምና በአህያ መካከል መወለዱን አጉልቶ በመጻፉ።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣6⃣እግዚአብሔር በብሉይና በሐዲስ ኪዳን እኔነኝ ብሎ ከተናገራቸው መካከል ጥቀስ/ሽ

//መልስ//👉እኔ ለአንተ ጋሻህ ነኝ። ዘፍ ፲፭፣፩
👉እኔ ኤልሻዳይ ነኝ።. ዘፍ ፲፯፣፩
👉የአባቶችህ አምላክ እግዚአብሔር እኔ ነኝ። ዘፍ ፵፮፣፫
👉ያለና የሚኖር እኔ ነኝ። ዘጸ ፫፣፲፬
👉እኔ እግዚአብሔር ነኝ። ዘጸ ፮፣፫
👉ከግብጽ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁህ እግዚአብሔር አምላክህ አኔ ነኝ። ዘጸ ፳፣፪
👉እኔ እግዚአብሔር አምላክህ ቀናተኛ አምላክ ነኝ።

👉በሐዲስ ኪዳንም ኢየሱስ ክርስቶስ እኔ ነኝ ብሏል

👉የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ። ዮሐ ፮፣፴፭
👉እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ። ዮሐ ፰፣፲፪
  👉እኔ የበጎች በር ነኝ። ዮሐ ፲፣፯
👉መልካም እረኛ እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፣፲፩
 👉ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፩፣፳፭
   👉እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ። ዮሐ ፲፬፣፮
👉እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ። ዮሐ ፲፭፣፩
👉እኔ…..እንዲህ… ነኝ ብሎ የተናገረና መናገር የሚችል አምላክ ብቻ ነው። ምክንያቱም፡-
፩. የማይለወጥ /የማይወሰን ስለሆነ፡
እንዲህ / እዚህ ነበርኩ። እንዲያ / እዚያ እሆናለሁ… አይልም። ቦታ ጊዜ ሁኔታ አይገድበውም።
እግዚአብሔር አይለወጥም፡ አይወሰንም።
ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬም እስከለዘላለምም ያው ነው።… ዕብ ፲፫፣፰

፪. ሁሉ በእጁ / በእርሱ ስለሆነ፡
እግዚአብሔር ሁሉን ፈጥሮአል፣ ሁሉን ይመግባል።
ኢየሱስ ክርስቶስ ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ሮሜ ፲፩፣፴፮።
፫. ከእርሱ በላይ ማረጋገጫ ስለሌለ፡
አንድ ነገር. ነው አይደለም የሚል ልዩነት ቢፈጠር በሦስተኛ በበላይ አካል እንዲረጋገጥ ይደረጋል።
እግዚአብሔር ሌላ አስረጅ፣ ምስክር አያስፈልገውም። ከእርሱ በላይ የሚያረጋግጥ ስለሌለ።
፬. ነኝ ያለው የሆነውን ስለሆነ
ሁልጊዜ የነበረውን፣ የሆነውን፣ ወደፊትም የሚሆነውን ነኝ አለ።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣7⃣በደብተራ ኦሪት ታቦተ ጽዮንን እንዲያገለግሉ የተመረጡት ሁለቱ ካህናት ስማቸውን ማን ይባላል አባታቸውስ ማነው???

//መልስ//👉አፋኒን እና ፊንሐስ ናቸው። አባታቸውም፦ካህኑ ኤሊ ነው።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣8⃣ሰባ ሰገል ለጌታችን ያመጡለት ወርቅ፣ ዕጣን፣ ከርቤ ከየት የመጣ ታሪካዊ አመጣጡ ከየት ነው?? ??

//ልመስ//🖊ይህ ወርቅ እጣን ከርቤ አመጣጡ አዳም ከገነት ሲባረር
መለአከ ቅዱስ ሚካኤል፥ መለአከ ቅዱስ ገብረኤል ፥መለአከ
ቅዱስ እሩፋኤል አምጥተው ሰጡት እሱም ለሔዋን እደ ጥሎሽ
አበረከተላት <ሔዋን ለሴት <ከሴት ሲዋረድ < ከኖህ ደረሰ <
ኖህ ከመርከብ ከወጣ ቦሀላ < ለሴም ሰጠው <  ለመለከ
ፃድቅ ለአብረሀም
ከአብረሀም ሲወርድ ሲዋረድ ከዳዊት ና ከሰሎሞን ደረሰ።
ሴምበአከአዝ ዘመን ቴሌጌልፌልሰር ማርክ ወስዶ በቤተ
መንግስት አኑሮት ነበር።
የሰባ ሰገል አባታቸው #ዥረደሸት ይባላል።ፈላስፋ ነበር።
አንድ ቀን ከውሀ ዳር ሆኖ ሲፈላሰፍ በሰሌዳ ኮከብ ድንግል
ህፃን ታቅፋ አየ ያየውንም በሰሌዳ ቀርፆ አስቀመጠው።ሲሞት
ለልጅ ልጆቹ እድህ አለ ኮከብ ሲወጣ ባያችሁ ጊዜ ሰማያዊ
ንጉስ ይወለዳልና ይሄንን ወስዳችሁ እጅ ንሱ ብሎ ወርቅ፥ እጣን
፥ ከርቤውን ሰቷቸው አልፏል።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣9⃣ አስራ-ሦስቱ/13/ ሕምማተ መስልቀ የሚባሉት ማን ማን ነው???

//መልስ//🖊🖊13ቱ ህማማተ መስቀል
1 የሾክ አክልል መድፋቱ
2 ራሱን በዘንግ መመታት
3 በጥፍ መመታቱ
4 ምራቅ መተፋቱ
5 መራራ ኃሞት መጠጣቱ
6 ወደኋላ መታሰሩ
7 ጀርባን መገረፉ
8 ጎኑን በጦር መወጋቱ
9 ሳዶር
10 አላዶር
11 ዳናት
12 አዴራ
13 ሮዳስ
ከ 9_13 ያሉት አምስቱ ቅንዋቶች ናቸው።

✅✍ጥ.ተራ.ቁ👉2⃣0⃣ ስለ ጋብቻ ከተነገሩት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ጥቅሶች መካከል ቢያንስ ሦስት ጥቀሱ/ሽ??....መልሱን ለእናንተ....?


ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ ሦስት/የ23ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን✝

🖊ይህ የምዕራፍ ሦስት የ23ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥቄቃና መልስ ውድድር እንዲህ ይቀርባል።

1⃣↪ ፆም  ማለት  ምን  ማለት  ነው⁉

2⃣↪ ኮዳዴ  ማለት  ምን  ማለት  ነው⁉

3⃣↪ ዐብይ ማለት  ምን  ማለት  ነው⁉


4⃣↪ የዐብይ ፆም ስንት ሳምንታት አሉት⁉

5⃣↪ ሰትጦሙም እንደ ግብዦች አትጠውልጉ:: ለሰዎች እንደ ጦመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና  እውነት እላችኇለሁ ዋጋቸውን ተቀብለዋል:: አንተ ግን ስትጦም በስውር ላለው አባትህ እንጅ እንደጦመኛ ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ያስረክብሃል። ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል⁉

6⃣↪ፆምን ቀድሱ ፤ጉባኤውንም አውጁ፥ ሸማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ጩኹ። ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል??

7⃣↪ ትንቢተ  ኢሳያት  58፥ 3,,,8  ያለው  ሀይለ  ቃል ምን ይላል⁉

8⃣↪የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤
ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ። ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል??


9⃣↪ ለሰዎች ኃጢአት ይቅር ብትሉ፤
የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤
ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፤
አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም። ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል??

🔟↪በዚህ በመሰዊያው ፊት መባህን ትተህ ሒድ  አስቀምጠህም ከወንድምህ ታረቅ  ይህ ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል?? ⁉

1⃣1⃣↪ ልጄ ሆይ ሕጌን አትርሳ ልብህም ትእዛዜን ይጠብቅ ብዙ ዘመናትና ረጅም እድሜ ሰላምም ይጨምምሩልሃልና። ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል ⁉


1⃣2⃣↪ እግዚአብሔር  የፃድቁን ነብስ  አያስርብም  የኃጥአንን ምኞት ግን  ይገለበብጣል ይህን ቅዱስ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል❗❓

1⃣3⃣↪ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለምን 40 ቀን እና ሌሊት ፆመ❗❓
ማጠቃለያ መልስ🖊👇

1⃣መተው መከልከል መታቀብ ማለት ነው።

2⃣ኩዳዴ ማለት ሰፊ እርሻ ማለት ነው።

3⃣ዓብይ ማለት ታላቅ ከፍ ያለ ማለት ነው።

4⃣8ት ናቸው። እነርሡም፦ ዘወረደ፣ ቅድስት፣ምኩራብ፣ መጻጉ፣ደብረ ዘይት፣ ገብርሔር፣ኒቆዲሞስ፣ሆሳህና ናቸው።

5⃣ማቴዎስ 6፤16)📝 ስትጾሙም፥ እንደ ግብዞች አትጠውልጉ፤ ለሰዎች እንደ ጾመኛ ሊታዩ ፊታቸውን ያጠፋሉና፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ዋጋቸውን ተቀብለዋል።

6⃣ ት.ኢዮኤል 1፥14))ጾምን ቀድሱ፥ ጉባኤውንም አውጁ፤ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ።

7⃣ት.ኢሳይያስ 58፤3_____8)📝
ስለ ምን ጾምን፥ አንተም አልተመለከትኸንም? ሰውነታችንንስ ስለ ምን አዋረድን፥ አንተም አላወቅህም? ይላሉ። እነሆ፥ በጾማችሁ ቀን ፈቃዳችሁን ታደርጋላችሁ፥ ሠራተኞቻችሁንም ሁሉ ታስጨንቃላችሁ።
 እነሆ፥ ለጥልና ለክርክር ትጾማላችሁ በግፍ ጡጫም ትማታላችሁ፤ ድምፃችሁንም ወደ ላይ ታሰሙ ዘንድ ዛሬ እንደምትጾሙት አትጾሙም።
እኔ የመረጥሁት ጾም ይህ ነውን? ሰውስ ነፍሱን የሚያዋርደው እንደዚህ ባለ ቀን ነውን? በውኑ ራሱን እንደ እንግጫ ዝቅ ያደርግ ዘንድ ማቅንና አመድንም በበታቹ ያነጥፍ ይህ ዘንድ ነውን? በውኑ ይህን ጾም፥ በእግዚአብሔርም ዘንድ የተወደደ ቀን ትለዋለህን?
እኔስ የመረጥሁት ጾም  አይደለምን? የበደልን እስራት ትፈቱ ዘንድ፥ የቀንበርንስ ጠፍር ትለቅቁ ዘንድ፥ የተገፉትንስ አርነት ትሰድዱ ዘንድ፥ ቀንበሩንስ ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን?
እንጀራህንስ ለተራበ ትቈርስ ዘንድ፥ ስደተኞቹን ድሆች ወደ ቤትህ ታገባ ዘንድ፥ የተራቈተውንስ ብታይ ታለብሰው ዘንድ፥ ከሥጋ ዘምድህ እንዳትሸሽግ አይደለምን?
 የዚያን ጊዜ ብርሃንህ እንደ ንጋት ይበራል፥ ፈውስህም ፈጥኖ ይበቅላል፥ ጽድቅህም በፊትህ ይሄዳል፥ የእግዚአብሔርም ክብር በኋላህ ሆኖ ይጠብቅሃል።

8⃣መ.መክብብ 12፤1-2)📝የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጕብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፤ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤
ፀሐይና ብርሃን ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፥ ደመናትም ከዝናብ በኋላ ሳይመለሱ፤

9⃣ማቴዎስ 6፤14-15)📝 ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ፥ የሰማዩ አባታችሁ እናንተን ደግሞ ይቅር ይላችኋልና፤
 ለሰዎች ግን ኃጢአታቸውን ይቅር ባትሉ፥ አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።

🔟 ማቴዎስ 5፥24)📝በዚያ በመሠዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፥ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ፥ በኋላም መጥተህ መባህን አቅርብ።

1⃣1⃣ ምሳሌ 3፤1))📝ልጄ ሆይ፥ ሕጌን አትርሳ፥ ልብህም ትእዛዛቴን ይጠብቅ።

1⃣2⃣ ምሳሌ 10፤3))📝 እግዚአብሔር የጻድቁን ነፍስ አያስርብም፤ የኅጥአንን ምኞት ግን ይገለብጣል።

1⃣3⃣📝/አብነት ሊሆነን
📝/ ጌታ የፆመው ስብከቱን ከመጀመሩ በፊት ነው እኛም ከሁሉ በፊት ፆም ፀሎትን እንድናስቀድም
📝/;ፆም ህግ እንደሆን ለማሳወቅ
📝/የዖሬት አባቶቻችን ነብያቶች የፆሙት አይሁዶችን ምክኒያት ስበብ ለማሳጣት
📝/ነቢዩ ሙሴ የዖሬትን ህግ ለመቀበል ፆሙዋል ጌታችን የአዲስ ኪዳን ህገ ወንጌል ለመስጠት
📝እስራኤላዊያን 40 ቀን እና ሌሊት ተጉዘው ነው ከተስፍይቱ ምድር የገቡት.
📝ነብሳትን ከሲዖል ሊያወጣ
አዳም በ40 ቀኑ ያገኘውን ልጅነት ዲያቢሎስ አጥቷል። ለአዳም የተሰጠውን ልጅነት ለማስመለስ ለካሳ እንደመጣ ለማሳወቅ 40 ሌሊት እና ቀን ፆመ።

ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ከስተታችን አርሙን።

ወስብሐት ለእግዝአብሔር

✅ @Teyakaenamels
✅ @Teyakaenamels
✅ @Teyakaenamels

2018 ፌብሩዋሪ 19, ሰኞ

እርስቴን አልሰጥም

https://youtu.be/q-F5pOd2Cvg

🍁 ርስቴን አልሰጥም 🍁
🎤🎤ተራኪ  ፥ አንድ ደሃ ሰው ነበረ እግዚአብሔርን የሚፈራ
በአካአብ ቤት አጠገብ ያለው የወይን ስፍራ
አንድ ቀን ግን ንጉሱ በመስኮቱ ሲመለከት
ስፍራውን ወደደው መጣ ወደሱ ቤት
ንጉሱም አይቶ ስፍራውን ስለወደደው
ደሃውን ናቡቴን አግኝቶት እንዲህም አለው
🤴🏽አካአብ ፥ በጣም ደስ ይላል እጅግ የሚመስጥ
ቦታው ተስማምቶኛል ከሁሉ የሚበልጥ
ይህን የወይን ቦታ ለኔ ብትሰጠኝ
ክብርህ ከፍ ይላል ታገኛለህ ሲሳይ
ከፈለክ በገንዘብ ካሻህ ደሞ በቦታ
ጨምሬ ልስጥህ ፍጹም አታመንታ
🙎🏽‍♂ናቡቴን፥ የሰማዩስ አምልካ እኔን ምን ይለኛል
የአባቶቼን እርስት ብሰጥ ቅር ይሰኛል
አልፈልግም ገንዘብ ሀብትስ ለምኔ
እርስቴን አልሸጥም እስካለሁኝ እኔ
🎤🎤 ተራኪ፥ አክአብ ተናደደ ባጣምም ገረመው
ይህን ስላለው ብቻ ይበልጡን ወደደው
👸🏽ኤልዛቤል፥ ምን ሆነሃል ውዴ ምነው ተጨናነክ
ምግብ የማትበላው እንደዚህ የሆንክ
ንገረኝ እስኪ ምንድነው ችግሩ
መፍትሄ አይጠፋም ከተመካከሩ
🤴🏽አክአብ፥ ባክሽ ተይኚ ውዴ በጣሙን ጨንቆኛል
ውስጤን የሚረብሽ ነገርም ገጥሞኛል
ከኛ ቤት አጠገብ ያለውን እርሻ
ወድጄው ነበረ ልሰጠው መካሻ
አልፈልግም ብሎ ድርቅ አይል መሰለሽ
ያባቶቼን እርስት ምናምን ብሎ አልሰጥም አለልሽ
👸🏽ኤልዛቤል፥ ቱ ቱ ቱ እንደው ማን ይሙት አንተ አሁን ንጉስ ነህ
የእስራኤል መሪ ቆራጥ ትባላለህ
ለዚች ጥቂት ነገር እንደዚህ መሆንህ
ይገርመኛል እኔ እንዲህ መንጨርጨርህ
🤴🏽አከአብ፥ ምን ላድርግ ውዴ ምን አርግ ትይኛለሽ
አልፈልግም ካለ አላመጣ ከሳሽ
👸🏽ኤልዛቤል፥ ወይ አንተ ምን ያስፈልጋል ለዚህ ለደሃ ሰው
ከሳሽና ተከሳሽ የምታመላልሰው
ንጉሱ አንተ ነህ ሌያውም በከተማ
ስልጣንህን ተጠቀም ከወደድከውማ
አይ ይሄን አልሰራም የምትል ከሆነ
እኔው እራሴ አስልኬ እዛው ድረስ ጭፍሮቹን
ማን እንደሆንክ ያያል አሳየዋለው ልኩን
ደብዳቤ አጽፌ ቦታውን ቶሎ እንዲለቅ
ጨርቄን ማቄን ሳይል ከቦታው እንዲርቅ
🤴🏽አከአብ፥ ምን ልታደርጊ ነው ውዴ ምንስ አስበሻል
አንቺ እንደዚህ ስላልሽ ይሰጥሽ መስሎሻል
👸🏽ኤልዛቤል፥ አይ አንተ አታውቀኝም መሰለኝ እኔ ኮ ኤልዛቤል ነኝ
ምንም ነገር ፈልጌ ወዲያው እንደማገኝ
ይልቁንስ አሁን ሌላውን ነገር ትተህ
ማህተቡን ስጠኝ የጣት ቀለበትህ
የሀሰት ምስክር በሸንጎ አቁሜ
ማን እንደሆንኩ ያውቀዋል ይረዳው አቅሜ
ንጉስን ተሳድቧል ፈጣሪንም ደፍሯል
ይሄ ደሃ ምናምንቴ እጅግ ተገዳድሯል
ብዬ አስ ከስሼው የሀሰት ምስክር
ምን እንደሚሆን ያውቅ የለ ንጉስን መዳፈር
🎤🎤ተራኪ ፥ በሀሰት ምስክር ዳሃው ናቡቴንን
አስደብድበው ገደሎት እግጅ በሚያሳዝን
ይህንን አድርገው አሸከሮች ጭፍሮቹ
ወሬ ውን ለማድረስ ሮጡ ቀቅጥሮቹ
ይህንን ስትሰማ ኤልዛቤል ዘለለች
የደስታንም ሲቃ ለአከአብ ነገረች
👸🏽ኤልዛቤል፥ ደስ ይበልህ ውዴ ተሳካ ምኞትህ
ሂድና ውረሰው ይሁንልህ ሀብትህ
ደሃው ተገሏል በመንገድ ተጥሎ
በጸባይ ሲለመን አልታዘዝ ብሎ
🎤🎤ተራኪ ፥ እግዚአብሔርም አየ በጣምም ተቆጣ
እንዲህ የሚል ድምጽ ለነብዩ መጣ
💗💗በሰማሪያ በአትክልቱ ቦታ አክአብን አግኘው
እግዚአብሔር ይልሃል እንዲህ ብለህ ንገረው
ደሃውን በመግደል ርስቱን ወረስከው
መንገድ ላይ ጎትተህ ለውሻ ሰጠህው
አንተም እሱን ገለህ የትም እንደጣልከው
ውሻውን ለደም በጭካኔ እዳላስከው
ያንተንም ደም ውሾች ይልሱታል
ሚስትህን ኤልዛቤል ውሾች ይበሏታል

🎤🎤ተራኪ ፥ልብሱን ቀዳደደ አክአብ አለቀሰ
ይህንን ሲሰማ ማቅንም ለበሰ
ፈጣሪ እንዲምረው አዘነ በጣሙን
ከቁጣው መቅሰፍት እንዲያድነው እሱን
በመጸሃፍ ቅዱስ እንደሱ ያለ ከቶ አይገኝም
ሚስቱ የነዳችው ንጉስ አክአብን
እንግዲህ አስተውል ሁሉም ሰው ይህን ይወቅ
እርስትህን አትስጥ ትውፊትህን ጠብቅ
እርስት ማለት ሀገር ናት የነጻነትህ አርማ
የጀግኖች መፍለቂያ መገኛ አውድማ
ርስት ማለት ሀይማኖት ከአበው የወረስናት
እንጠብቅ እንያዛት ሌላ ሳይገባባት
ርስት ማለት ህብረት ነው የአንድነታችን ሚስጢር
ሳንከፋፈል የመቆየታችን ህብር
ርስት ማለት ርስት ማለት ርስት ማለት ሰላም ነው
የሰማዩ ጌታ የሚያከናውነውsaramareyama.890@gmail.com

2018 ፌብሩዋሪ 3, ቅዳሜ

መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን

በድንግል ማርያም የአስራት ልጆች ማኅበር የተዘጋጀ። መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር።👇✅

✍ጥ.ተራ ቁ✅ 1⃣አስተርዮ ማለት ምን ማለት ነው??

*//መልስ///* 👉መታየት መገለጥ ማለት ነው፡፡ ገሐድ የሚለው ቃልም በጾምነቱ ሌላ ትንታኔ ሲኖረውአስተርእዮ ቃሉ የግእዝ ትርጉሙ ያው መገለጥ ማለት ነው፡፡ በግሪክ ኤጲፋኒ ይሉታል፡፡ የኛም ሊቃውንት ቀጥታ በመውሰድ ኤጲፋኒያ እያሉ በዜማ መጻሕፍቶቻቸው ይጠሩታል፡፡ ትርጉሙም ከላይ ከጠቀስናቸው ጋር አንድ ነው፡፡

አስተርአየ የተባለው ግሥ ራሱን ችሎ ሳይለወጥ በአምስቱ አዕማድ የሚፈታ ብቸኛ ግሥ ነው፡፡ ይህም ማለት፡- አስተርአየ፤ ታየ፤ ተያየ፤ አሳየ፤ አስተያየ፤ አየ ተብሎ ይፈታል ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ዘመነ አስተርእዮ ሲያጥር ከጥር 11 ቀን እስከ ጥር 30 ቀን ይሆናል፡፡ በዚህም መሠረት 20 ቀናት ይሆናሉ፡፡ ሲረዝም ደግሞ ከጥር 11 ቀን እስከ መጋቢት 3 ቀን ይሆናል፡፡ ይህም 53 ቀናት ይሆናሉ ማለት ነው፡፡

ጌታን ለሐዋርያት ህፅበተ እግር ያደረገበት ቀንም ከጸሎተ ሐሙስ እስከ ጰራቅሊጦስ ቢቆጠር 53 ቀናት ስለሚሆኑ የእነዚህ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ዮሐንስ በጥምቀት ዕለት ለልዕልና /ጌታ ሰውን ምን ያህል እንዳከበረው/ ለማሳየት እጁን ከጌታ ራስ በላይ ከፍ እንዳደረገ ጌታም ለትህትና እጁን ከሐዋርያት እግር በታች ዝቅ አድርጎ እግራቸውን አጥቧቸዋልና ነው፡፡ ጥምቀት የህጽበት አምሳል ሲሆን፤ /ህጽበት/ መታጠብ በንባብ አንድ ሆኖ ሁለት ምሥጢራት አሉት፡፡

አንደኛ፤- ምእመናን የእንግዳ እግር እንዲያጥቡ ትምህርት ማስተማሩ ሲሆን፤ ሁለተኛው ለሐዋርያት ጥምቀት ነው፡፡

በጸሎተ ሐሙስ ቢጠመቁም መንፈስ ቅዱስ የተቀበሉት የጰራቅሊጦስ ነውና ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ፤ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያን ስለ ቅዱሳን ሐዋርያት ጥምቀት እንደጠየቀውና ጥምቀታቸው ህጽበተ እግር መሆኑን እንደመለሰለት፡፡

በሌላ በኩል ከዘመነ ልደት እስከ ጥምቀት ተወልደ፤ ተሰገወ /ሰው ሆነ/ ይባላል እንጂ አስተርአየ አይባልም፡፡ ከጥምቀት በኋላ ግን አብሮ ተባብሮ ተጠምቀ፤ ተወለደ፤ ተሰገወ አስተርአየ ይባላል፡፡

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅2⃣እመቤታችን በስንት አመቷ አረፈች?? የእረፍት በዓሏስ መቼ ነው የሚከበረው??

*//መልስ//*👉በ64 ዓመቷ አረፈች። በዓለ እረፍቷም ጥር 21 ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅3⃣⃣የነነዌን ፆም ለምን እንፆማለን??

*//መልስ//*👉እኛንም ይቅር እንዲለን እንፆማለን
👉🏻የዓብይ ፆም መዘጋጃ የንስሀ መግቢያ እንዲሆን አባቶቻችን እንድንፆመው ይህን ፆም ሰርተውልናል።

✍ጥ.ተራ.ቄ.✅4⃣ነቢያት በስንት ይከፈላሉ ?ምንና ምን በመባል?

መልስ፡- በሁለት ፡፡ ዐበይት ነቢያትና ደቂቀ ነቢያት፡፡ የጽህፍ ነቢያትና የቃል ነቢያት።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅5⃣ ቅዱስ ጴጥሮስ መንፈስ ቅዱስ ከወረደበት በኋላ 3000 ሕዝብ ያሳመነው በስንት ሰዓት ነው?

*//መልስ//*፡- ከጠዋቱ በ 3 ሰዓት፡፡የሐዋ.2 ÷15

✍ጥ.ተራ ቁ✅ 6⃣መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ድንግል ማርያምን ደስ ይበልሽ ሲላት የመለሰችለት መልስ ምን ነበር?

*መልስ*፡- ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው፡፡ ሉቃ. 1 ÷29

✍ጥ.ተራ.ቁ✅7⃣ በሽተኛው መፃጉ ለመጠመቅ የሄደበት የመጠመቂያ / የፀበል/ ቦታ ምን ትባላለች ?ስንት መመላለሻዎች ነበሯት?

*መልስ*፡- ቤተሳይዳ ሲሆን አምስት መመላለሻ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅.8⃣ ጾመ ነነዌ ወይም የ 3 ቀን ጾም በመባል የምትታወቀው ጾም የተሰየመችው በማን ነው??

*//መልስ//*👉በነነዌ ህዝቦች፡፡
" ዮናስ ለነነዌ ሰዎች ምልክት እንደ ሆናቸው፥ እንዲሁ ደግሞ የሰው ልጅ  ትውልድ ምልክት ይሆናል።"
(የሉቃስ ወንጌል 11፡30)

✍ጥ.ተራ.ቁ✅የነብዩ ዮናስ እናትና አባቱ ማን ይባላሉ?

//መልስ//፦አባቱ አማቴ ሲባል እናቱ ደግሞ ሶና ይባላሉ።


✍ጥ.ተራ.ቁ✅🔟ነብዩ ዮናስ መቼ አረፈ በስንት  አረፍ??
//መልስ//፦👉በ170 ዓመቱ መስከረም "25" ቀን  አረፈ።

✍ጥ.ተራ ቁጥር✅1⃣1⃣ ዮናስ ማለት ምን ማለት  ነው??

//መልስ//፦👉ዮናስ ማለት፦ በዕብራይስጥ     ርግብ ማለት ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅1⃣2⃣ነብዩ ወደ ነነዌ አልሄድም ብሎ የኮበለለባት ተርሴስ አሁን የት ሀገር ውስጥ ትገኛለች??

//መልስ//👉በስፔን ትገኛለች።

ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...