2018 ሴፕቴምበር 25, ማክሰኞ

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ አደረሳችሁ አደረሰን

#መስቀሉ_አበራ

እዮሐ አበባዬ    መስከረም ጠባዬ (2)
መስከረም ሲጠባ ተተክሎ ደመራ
ህዝበ ኢትዮጵያን እዩት ችቦውን ሲያበራ
በታላቁ ብርሃን በመስቀል ደመራ (2)

#በኃጢአት_ጨለማ  አበራ መስቀሉ  ለእኛ አበራ
#ተውጠን_ሳለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የክርስቶስ_መስቀል  አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ብርሃን_ሆነልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ትምህርተ_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሆኖን_ላመንነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በቃሉ_ለምንድን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የእግዚአብሔር_ኃይል_ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል ባንዲራችን
   የነጻነት አርማችን (2)

#በኢየሩሳሌም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አይሁድ_አብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ያዳናቸውን_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አናውቅም_ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የድሉን_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ከመሬት_ቀብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስሏቸው_ነበር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ውጦ_የሚያስቀረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በቀራንዮ ጎልጎታ
   ጠላታችን ድል ተመታ (2)

#ንግሥቲቷ_እሌኒ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በጣም_የታደለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ደመራን_አቁማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ፍለጋ_ጀመረች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀለ_ክርስቶስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ወዴት_ነው_እያለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በጣን_ጢስ_ተመርታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀሉን_አገኘች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል መከታ
   ቆስጠንጢኖስ ድል ተመታ (2)

#ነገር_ግን_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተቀብሮ_አልቀረም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተራራ_አፍርሶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጠላት_አሳፈረ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል_ሲወጣ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ታላቅ_ሁካታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ድውይ_ሲፈወስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አንካሳው_ዳነ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሙታን_ተነሱ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይመስገን_ጌታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ
    ክርስቲያኖች እልል በሉ (2)

#መስቀል_መከታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይሁን_ጋሻችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እንዳይደፈር_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ዳር_ድንበራችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኢትዮጵያ_ኑሪ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእምነት_ፀንተሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጌታ_በመስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የባረከሽ_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀሉ አበራ
    እንደ ፀሀይ ጮራ (2)

#መስቀሉን_አምነን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተሳልመነዋል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ከክብሩ_ዙፋን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእርሱ_ባርኮናል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እንሰግድለታለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የፀጋ_ስግደት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእርሱ_ላይ_ስላለ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኃይለ_መለኮት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል የእኛ ጋሻ
    የዲያብሎስ ድል መንሻ (2)

#የኢትዮጵያን መኩሪያ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኑ_ተመልከቱልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የመስቀሉን_ብርሃን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ነፀብራቁን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እፀ_መስቀሉ _ው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የእኛ_መከታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የተሰጠን_ለእኛ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ምልክታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል እንመካለን
    እንድንበታለን (2)

#የዳዊት ልጅ ያዕቆብ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የሀገራችን ኩራት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የኢትዮጵያ ንጉሥ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጌታን የሚፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሀገሪቱን ሲዞር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ድካሙን ሳይፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ብርሐን እያበራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ፍቅር
   በእኛ ላይ ይደር (2)

#መናገሻ_እንጦጦ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የረር አምባ አመራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሲፈለግ_ሰንብቶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የመስቀል_ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጊሸን ላይ አገኘ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የአምባሰል_ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ግማደ_መስቀሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አርፏል_ከዚያ_ስፍራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል መስቀላችን
   የክርስቲያን ኃይላችን (2)

#የመስቀል_ለታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የደመራው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኢትዮጵያውያን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተደስተው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በሀገር_ልብሳቸው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አምረው_ደምቀው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በአደባባዩ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተሰብስበው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይዘምራሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል_ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ደመራ
    በኢትዮጵያ ሲያበራ (2)
Watch "የመስቀል ኮሌክሽን መዝሙሮች" on YouTube
https://youtu.be/_YnPAwv1sZE

2018 ሴፕቴምበር 23, እሑድ

መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
@Teyakaenamels
@Teyakaenamels

1ኛ) አምሥቱ(5) አዕማደ ምስጢር የሚባሉት ምን ምን ናቸው?  መልስ፦  ሚስጥረ ሥላሴ
ሚስጥረ ስጋዌ
ሚስጥረ ጥምቀት
ሚስጥረ ቁርባን
ሚስጥረ ትንሳኤ ሙታን ናቸው።
2ኛ) ቤተ ክርስቲያን ስንት ባህሪ አሏት? መልስ፦ቤተ ክርስቲያን  4 ባህሪ አሏት እነሱም 1ኛ፦ በመጀመርያ ቤተ ክርስቲያን አንዲት ነች።
2ኛ፦ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ነች።
3ኛ፦ቤተክርስቲያን ኩሉውይት ነች።
4ኛ፦ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያት ነች ማለት ነው።
3ኛ) እናታችን ቅድስት አርሴማ  ሰይፍ  ከአረፈባተ በኋላ ለስንት ስዓት ቆመች? የናታችን የአርሴማ ሃገርስ የት ነው? መልስ፦ እናታችን ቅድስት አርሴማ ሰይፍ ከአረፈባት በኋላ ለ3 ስዓት ቁማለች ሃገሯ ደግሞ አርመንያ ነው።
4ኛ)  የእመቤታችን በዓላት ስንት ናቸው? መልስ፦  33 ናቸው።
5ኛ) ማርያም ፊደል የሚለውን ቃል የተናገሩት አባት ማን ናቸው (ማን) ይባላሉ? መልስ፦ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ናቸው።
6ኛ) ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ክርስትና የተመለሰው ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርገት በኋላ በስንተኛው አመት ነው?  መልስ፦በ8ኛ አመቱ ነው።
7ኛ) መጽሐፍ ነገስት በስንት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል? መልስ፦በ3 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል።
8ኛ) ዜና መዋል ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦ የእለት ዜና ማለት ነው።
9ኛ) ምናሴ ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  ማስረሻ ማለት ነው።
10ኛ)መስፍን ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  ፈራጅ፤ አስተዳዳሪ ማለት ነው።
11ኛ) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከዘንዶ አፍ ያዳናት ልጅ ስማ ማን ትባላለች? መልስ፦ ብሩክታይት ትባላለች።
12ኛ) አኬልዳማ ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  የደም መሬት ማለት ነው።
13ኛ) ፃዲቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ በስንት አመተ ምህረት ወደ ኢትዮጵያ ገቡ? መልስ፦  በ480 ዓ.ም ነው።
14ኛ ከነአን የምን ምሳሌ ናት?መልስ፦የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ናት።
15ኛ) ላንች የማይገዛ ህዝብና መንግስት ይጠፋል። ይህን ሃይለ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኛዋለን? ምዕራፍና ቁጥሩን? መልስ፦ኢ.ሳ 60፥12 ላይ ነው።
16ኛ)በጨረቃ በከዋክብት ላይ ስልጣን የተሰጠው መላክ ማን ነው? መልስ፦ ቅዱስ ሩፋኤል ነው።
17ኛ) ቁርባን ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦ በሱርስት ቋንቋ መባ፤ስጦታ ማለት ነው።
18ኛ) ደስታ በስንት ይከፈላል? መልስ፦ ደስታ በሁለት(2) ይከፈላል መንፈሳዊ ደስታ እና ሥጋዊ ደስታ ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭) የ42ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፫

የምዕራፍ (፭)/የ42ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃልና የጹህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር⤵

@ምንጭ ማኅበረ ቅዱሳን 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ⤵

ማጠቃለያ መልስ🖊
➡1⃣ዮሴፍ የሚባል አንድ ሌዋዌ በሐዋርያት አጠራር ትርጉሙ "የመጽናናት ልጅ" የሚሆን ስም ተሰጠው። የዚህ ሐዋርያ ስም ማን ነው?

ሀ. ፋሮስ
ለ.እስክንድሮስ
ሐ.አጵሎስ
መ. በርናባስ

✅መ

➡2⃣"ጌታ ሆይ በኢየሩሳሌም በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ ነገር እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ከብዙዎቹ ሰምቻለሁ። በዚህም ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ከካህናት አለቆች ሥልጣን አለው።" ተብሎ የተነገረው ስለ ማን ነው?

ሀ. ሐናንያ
ለ.ስምዖን
ሐ.ሳውል
መ.በርስያስን

✅ሐ

➡3⃣የሞት አያት ማን ነው?

ሀ. ኃጢአት
ለ.ተንኮል
ሐ.ምኞት
መ.ቁጣ

✅ለ

➡4⃣አጋቦስ ይባል የነበረው ነቢይ ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ በመውረድ ምን ተነበየ?

ሀ. ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚታሰር
ለ. በምድር ላይ ራብ እንደሚመጣ
ሐ. ኢየሩሳሌም በሮማውያን ወታደሮች ፈጽማ እንደምትጠፋ
መ.ክርስትና በዓለም እንደሚሰበክ

✅ለ

➡5⃣አይሁድን ደስ ያሰኝ ዘንድ በክርስቲያኖች ዘንድ መከራን ያጸናው ንጉሥ ማን ነው?

ሀ. ሄሮድስ አንቲጳስ
ለ. ሄሮድስ ቀዳማዊ አግሪጳ
ሐ.ሄሮድስ ዳግማዊ አግሪጳ
መ.ጲላጦስ

✅ሐ

➡6⃣ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን?" ያለው ሐዋርያ ማን ነው?

ሀ.ፊሊጶስ
ለ.ታዴዎስ
ሐ.ቶማስ
መ.ናትናኤል

✅መ

➡7⃣ከሐዋርያት መካከል  አስቀድሞ "አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ" ብሎ የተናገረው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ. ቅዱስ ቶማስ
ሐ.ቅዱስ ናትናኤል
መ. ቅዱስ ፊልጶስ

✅ሀ

➡8⃣በሁለተኛው የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ አብሮ የነበረው ማን ነው?

ሀ.አቂላስ
ለ.ሲላስ
ሐ.ጵርስቅላ
መ.በርናባስ

✅ሐ

➡9⃣በሕልሙ የመቄዶንያ ሰው ለእርዳታ ሲጠራው ያየው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጳውሎስ
ለ.ቅዱስ ቲቶ
ሐ.ቅዱስ ሉቃስ
መ.ቅዱስ ጋይዮስ

✅ሀ

➡🔟ቅዱስ ጳውሎስ በአንድ ከተማ በሚመላለስበት ወቅት ሰዎች "ለማይታወቅ አምላክ" ብለው ጽፈው በመመልከቱ በማዘን ትምህርት አስተምሯቸዋል።
ከተማው የትኛው ነበር?

ሀ. ተሰሎንቄ
ለ.ቆሮንቶስ
ሐ.ኤፌሶን
መ.አቴና

✅መ

➡1⃣1⃣ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር አብረው ድንኳን ይሰፉ የነበሩት ማንና ማን ናቸው?

ሀ.ሲላስ እና ጢሞቴዎስ
ለ.አጵሎስ እና በርናባስ
ሐ. አቂላ እና ጵርስቅላ
መ.ማርቆስ እና ሉቃስ

✅ለ

➡1⃣2⃣ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልሞና በጻፈው መልእክቱ ማንን ይቅር እንዲል መክሮታል?

ሀ. አገልጋዩ ግያዝን
ለ.ውሸተኞች ወንድምችን
ሐ. አገልጋዩ አናሲሞስን
መ.መልስ የለም

✅ሐ

➡1⃣3⃣የክፋት ሁሉ ሥር ምንድን ነው?

ሀ. ትዕቢት
ለ.ቁጣ
ሐ.ዝሙት
መ.ገንዘብን መውደድ

✅መ

➡1⃣4⃣የልስጥራን ሰዎች ሁለት ሐዋርያትን ድያ እና ሄርሜን በማለት በአማልክቶቻቸው ስም ሰይመዋቸዋል። ሐዋርያቱ እነማን ነበሩ?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ዮሐንስ
ለ.ቅዱስ ጢሞቴዎስ እና ቅዱስ ቲቶ
ሐ. ቅዱስ እንድርያስ እና ቅዱስ ታዴዎስ
መ.ቅዱስ በርናባስ እና ቅዱስ ጳውሎስ

✅መ

➡1⃣5⃣ከሐዋ መካከል በሰማዕትነት ያላለፈው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ.ቅዱስ ያዕቆብ
ሐ. ቅዱስ እንድርያስ
መ.ቅዱስ ዮሐንስ

✅መ

➡1⃣6⃣ቅዱስ ጳውሎስ "የእግዚአብሔር ጦር ዕቃ ብሎ የሰየመው የትኛውን ነው?

ሀ. የእውነትን ቀበቶ
ለ.ለእግዚአብሔር ቃል
ሐ.የእምነት ጋሻ
መ. ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

➡1⃣7⃣በሐዋርያት ስም ዝርዝር የመጀመሪያውን ቦታ ይዞ የሚገኘው ማን?

ሀ. ቅዱስ እንድርያስ
ለ.ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐ. ቅዱስ ጳውሎስ
መ. ቅዱስ ፊልጶስ

✅ለ

➡1⃣8⃣ዐበይት ነቢያት የሚባሉት ማን ማን ናቸው?

✅ኢሳያስ፣ ኤርምያስ፣ሕዝቅኤልና ዳንኤል  ናቸው።

➡1⃣9⃣ የተራራው ሥብከት ዐሥሩ ዐበይት ክፍሎች ማን ማን ናቸው??

✅ክፍል አንድ፦ ስለ አንቀጸ ብፁዓን/ማቴ 5፥3-12/

ክፍል ሁለት፦ስለ አንቀጸ ምግባር/ማቴ 5፥13-16

ክፍል ሦስት፦አጽንኦተ ሕግ/ማቴ 5፥17-48

ክፍል አራት፦ ሦስቱ አናቅጸ ምግባራት/ ማቴ 6፥1-8

ክፍል አምስት፦እግዚአብሔርን ማስቀደም እንዲገባ/ማቴ 6፥19-34

ክፍል ስድስት፦ አትፍረዱ/ማቴ.7፥1-6

ክፍል ሰባት፦ እንድንጸልይ መታዘዛችን/ ማቴ.7፥7-12

ክፍል ስምንት፦ቀጭን መንገድ በጠባቡ በር/ማቴ. 7፥13-14

ክፍል ዘጠኝ፦ መልካም ፍሬ ከመልካም ዛፍ/ ማቴ.7፥15-20

ክፍል አስር፦ ጽድቅ በተአምራት ሳይሆን በሥራ ስለመሆኑ/ማቴ 7፥21-29

➡2⃣0⃣በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ በገና፣ዋሽን፣ጸናጽል፣ከበሮ፣እምቢልታ፣ ነጋሪት፣መለከት፣ መሰንቆ ተጽፎ የምናገኘው በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው?

✅በገና፣መሰንቆ፣ነጋሪት፣ጽናጽል 2ኛ.ሳሙ 6፥5
ዋሽንት፣ክራር ት.ዳ. 3፥5/ ዘፍ.4፥21/ከበሮ፣እንቢልታ/ኢሳ.5፥12/ዘዳ.15፥20/መለከት/1ኛ.ነገስት 1፥40/

ወስብሀት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!saramareyama.890@gmail.com

የመስቀል መዝሙሮች !

ያሬዳዊ መዝሙሮች:
©✝መዝሙር በእንተ መስቀሉ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ©⤵️

©ይቤሎሙ ኢየሱስ

ይቤሎሙ ኢየሱስ/፪/ለአይሁድ/፪/
እመኑ ብየ ወእመኑ በአቡየ አበርህ በመስቀልየ ለእሊአ /፪/
#ወረብ


©ያሬድ ካህን
ያሬድ ካህን /፪/ ፀሐያ ለቤተክርስቲያን/፪/
አሰርገዋ ለኢትዮጵያ በስብሐት ወበሃሌ  ሉያ/፪/

#ዮምሰ
ዮምሰ ለእሊአየ /፪/
አበርህ በመስቀልየ/፬/

      #ወረብ

©ቤተ ክርስቲያን ርእየቶ

ቤተ ክርስቲያን ርእየቶ ቅንወ ለዘበጎልጎታ ደሙ ተክዕወ/፪/
ከመ እግረ ፀሐይ ሥኑ ኀተወ በዓለ መስቀል ዘዮም ትገብር ህልወ/፪/
ትርጉም:- በጎልጎታ ደሙ የፈሰሰውን አምላክ ቤተ ክርሲያን አየችው ደም ግባቱም እንደ ፀሐይ አውታር(ጮራ) አበራ የዛሬው የመስቀል በዓልም ለዘለዓለም ታበራለች

©መስቀሉሰ

መስቀሉሰ ለክርስቶሰ ብርሃን ነአምን ትብሌ ቤቴ ክርስቲያን/፪/
ዛህኑ ለባሕር ወመርሶ ለአሕማር ዝንቱ ውእቱ መስቀል/፪/
ትርጉም:-የክርስቶስ መስቀል ለመናምን ሰዎች ብርሃን ነው መስቀል የባሕር ፀጥታው የመርከቦች ወደብ ነው ትላለች ቤተ ክርስቲያን

©መርሕ ለፍኖት

ሃሌ ሉያ መርሕ ለፍኖት ሞገሶሙ ለጻድቃን ሞገስ/2/
ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአግብኦ ውስተ ገነት/2/
ሃሌ ሉያ መሪ ነው በመንገድ ሞገሳቸው ለጻድቃን ሞገስ/2/
ይኸ መስቀል ነው አዳምን የመለሰው ወደ ገነት/2/

©ብከ ንወግዖሙ

ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ/፪/ ይቤ ዳዊት በመንፈሰ ትንቢት/፪/
በእንተ ዝንቱ  ዕፀ መስቀል ዘተሰቅለ ዲቤሁ ቃለ አብ /፪/

ትርጉም፡- ቅዱስ ዳዊት በትንቢት መንፈስ እንዲህ አለ፣ በአንተ
ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፤ በዚህ የእግዚአብሔር ቃል/ኢየሱስ ክርስቶስ/ በተሰቀለበት፡፡
©ትቤሎ እሌኒ

ትቤሎ እሌኒ ለኪራኮስ ንግረኒ አፍጥን /፪/
ኀበ ሀሎ መስቀሉ ለኢየሱስ/፪/ ክርስቶስ /፬/

ትርጉም፡- ዕሌኒ ኪራኮስን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
የት እንዳለ ፈጥነህ  ንገረኝ አለችው፡፡

©መስቀል አብርሃ

መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሰርገወ ኢትዮጵያ/፪/
እምኩሉሰ ፀሐየ አርአየ ዕፀ መስቀል/፪/

ትርጉም፡- መስቀል አበራ ኢትዮጵያንም  በከዋክብት ሸለመ
 ከሁሉ ይልቅ መስቀል እንደ ፀሐይ ደምቆ/በርቶ/ ታየ፡፡

©ለዕፀ መስቀል

ርእዩ ዕበዮ ለዕፀ መስቀል /፪/
ዘመጠነዝ/፪/ትርሢተ ክብር ትህትና ወፍቅር /፪/

ትርጉም፡-የዕፀ መስቀሉን ክብሩን ትህትናውን ፍቅሩን ሽልማቱን     
ምን ህል እንደሆነ እዩና አድንቁ ወይም ከፍ ከፍ አድርጉት፡፡

  ©ርእዩ ዕበዮ
ርእዩ ዕበዮ ለቅዱስ ዕፀ መስቀል /፪/
ዕውራን ይሬእዩ ወጽሙማን ይሰምዑ እለ ለምጽ 
ይነጽሑ እለ መጽኡ ኀቤሁ /፪/

ኑ እዩ የመስቀሉን ተአምራት /፪/
እውሮች ያያሉ ደንቆሮዎች
ይሰማሉ ለምጻሞችም           
ይነጻሉ ወደ እርሱ የመጡ ሁሉ /፪/

©ዮም መስቀል

ዮም መስቀል አስተርአየ እለ ማሰነ ፍጥረተ አሠነየ/፪/
ዮም መስቀል ተኬነወ ወዘተጼወወ ሕዝበ በደሙ ቤዘወ/፪/

ትርጉም፡-ዛሬ መስቀል ተገለጠ የጠፉትን ሰዎች አዳነ ዛሬ
መስቀልብልሃተኛ ሆነ ምርኮኞች ወገኖቹንም
በክርስቶስ ደም አዳነ፡፡

©ወበእንተዝ

ወበእንተዝ አዘዙነ መምህራነ ቅዱስ ወንጌል/፪/
ንስግድ ለመስቀል ወለማርያም ድንግል/፬/

ትርጉም፡- ቅዱስ ወንጌልን የሚያስተምሩ መምህራን
ለመስቀልና  ለድንግል ማርያም እንድንሰግድ ያዝዙናል፡፡

©ሀብሩ ቃለ

ሀብሩ ቃለ ነቢያተ/፪/
ወይቤሉ መስቀል ብርሃን/፪/ ለኵሉ ዓለም /፪/

ትርጉም፡-ነቢያት መስቀል ለዓለም ሁሉ ብርሃን ነው
ብለው በአንድ ቃል  ሆነው  ተናገሩ፡፡

© ኀበ ቀራንዮ

ኅበ ቀራንዮ ደብረ መድኃኒት/2/
ቀራንዮ/2/ ኀበ ቀራንዮ/2/
የመስቀሉ ቃል ለእኛ የእግዚአብሔር ኃይል ነው/4/
ለማያምኑት ሞኝነት ነው ለእኛ ግን ሕይወት ነው/2/
እንመሰክራለን ፈጣሪያችን አለ/4/
እንመነው አንካደው ፈጣሪያችን ቸር ነው/2/
እንመሰክራለን ድንግል አማላጅ ናት/2/
እንመሰክራለን ማርያም  አማላጅ ናት/4/
እንመናት አንካዳት የአምላክ እናት ናት/2/
ኅበ ጥበባት ኀበ ልሳናት/4/
ዮሐንስ/2/ ወንጌለ ስብከት/2/

#በመስቀሉ #ቤዘወነ

በመስቀሉ ቤዘወነ ወበደሙ ተሰሃለነ/2/
አምላከ ምሕረት ውእቱ መድኃኒነ
አምላከ ምሕረት ውእቱ
በመስቀሉ ቤዛ ሆነን ሞትን ሽሮ ከሞት አዳነን/2/
የምሕረት ጌታ ነውና ይቅር አለን
የምሕረት ጌታ ነውና

#ብርሃን ወጣ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ የሚያንጸባርቅ
የአምላክ እና የሰው ልጆች እውነተኛ እርቅ
ደስ ይበለን በመስቀሉ ብርሃን
እልል እንበል በአንድነት ሆነን
ተነሳልን መድኃኒታችን

ከፊት ለፊት በመሳሉ የመስቀሉ ነገር
የሚወደው ሐዋርያ የወንጌል መምህር
ዮሐንስም ስቅለቱን በማየቱ
ሲያዝን ኖረ በምድራዊ ሕይወቱ
ቢያሰቅቀው ሞቱ ግርፋቱ

ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
በዓለም ጥበብ ለሚኖሩት እውነት ተሰኗቸው
ለጠቢብ ሰው በመንፈስ ለሚኖረው
የመዳን ቀን እውነተኛ ዓርማ ነው
ከገሀነም እሳት የሚያድን ነው

እስከመስቀል ላልተለየው ቅዱስ ሐዋርያ
ለዮሐንስ ለወንጌል ሰው የፍቅር ባለሞያ
ምስጋናችን በምድር ይድረሰው
እንድናለን በሰጠው ምሳሌው
ሰዎች ሁሉ

#ኧኸ #በመስቀልከ

ኧኸ በመስቀልከ ኧኸ ጽልመተ አብራህከ
ኧኸ በመስቀልከ ኧኸ ሙታነ  አንሣእከ/፪/
ኧኸ ወዘተዓጉለ ረዳእከ በመስቀልከ/፪/
ትርጉም:-በመስቀልህ ጨለማን አበራህ ሙታንንም አነሣህ የጠፋውንም በመስቀልህ ረዳኸው/አዳንኸው/።

#በኃይለ #መስቀሉ

 በኃይለ  መስቀሉ/2/ይዕቀበነ
በኃይለ መስቀሉ /3/  ይዕቀበነ/2/


      #©መስቀል #ብርሃነ
መስቀል ብርሃነ ለኲሉ ዓለም
መሠረተ ለቤተክርስቲያን/2/

ወሀቤ ሰላም መድኃኔዓለም መስቀል
መድኅን ለእለ ነአምን/2/

መስቀል ብርሃን ነው ለመላው  ዓለም
መሠረተ ነው ለቤተክርስቲያን/2/
ሰላምን ሰጪ ነው መድኃኔዓለም መስቀል
አዳኝ ነው ለኛ ለምናምን /2/

        #©አለው #ሞገስ
አለው አለው ሞገስ  ኧኸ  አለው ሞገስ
የመስቀል በአል ሲደርስ ኧኸ  አለው ሞገስ
አለው አለው አበባ  ኧኸ  አለው አበባ
የመስቀል በዓል ሲገባ  ኧኸ አለው አበባ
አለው አለው ደስታ  ኧኸ አለው ደስታ
መስቀል ሲከብር በእልልታ  ኧኸ አለው ደስታ
አለው አለው ሰላም ኧኸ አለዉ ሰላም
መስቀል ሲታይ በአለም  ኧኸ አለው ሰላም
አለው አለው አለኝታ  ኧኸ አለን አለኝታ
እፀመስቀል መከታ  ኧኧ አለን አለኝታ
እዩት እዩት ሲያበራ  ኧኸ እዪት ሲያምር
የመስቀል በዓል ደመራ  ኧኸ እዪት ሲያበራ
እዪት እዩት ሲያምር  ኧኸ እዩት ሲያም
መስቀል በዓለም ሲከብር  ኧኸ እዪት ሲያምር


   #©አየኸው #ደመራ
አየኸው ደመራ መስቀል ሲያበራ/2/
መስቀል አለ ወይ ቆሟል ወይ
አለእንጂ ለምጽ ያነጻል እንጂ
ያው ቆሟል ድውይ ይፈውሳል
      አምነዋለሁ የት አገኘዋለሁ
አለልሽ እሰሪው በአንገትሽ
ከልብሽ ተሳለሚው አምነሽ
      እኮራለሁ በእፀ መስቀል
ይፈውሳል ሙታንን ያስነሳል
ድል ያደርገል ድውይ ይፈውሳል


#©ዕሌኒ #ንግስት
እሌኒ ንግሥት ሐሠሠት መስቀሉ/2/ኧኸ
ዕንባቆም ነቢይ ዘአንከረ ክብሩ/4/
ትርጉም=ዕሌኒ ንግሰት መስቀሉን ፈለገች
ነቢይ እንባቆም የጌታችንን ሥራ አደነቀ።


    #©እንተ ተሐንፀት
እንተ ተሐንፀት በስሙ ወተቀደሰት
በደሙ ቤተክርስቲያን/2/
ወተአትበት/2/ በዕፀ መስቀሉ
እስመ ኃይለ እግዚአብሔር ላዕሌሃ/2/
ትርጉም=በስሙ የታነፀች በደሙ የቀደሳት በዕፀ መስቀሉ የተባረከች ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ሀይል በላይዋ አለ።

  #©ከመትባርከነ
ከምትባርከነ በስቀልከ ክቡር/2/
ከመ ይኲን ቤዛ/2/ ለኩሉ አsaramareyama.890@gmail.com

2018 ሴፕቴምበር 9, እሑድ

እንኳን ለዐዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! የዐውድ ዓመት መዝሙሮች

​​🌼#የእንቁጣጣሽ #መዝሙር🌼
                  🌼🌼♥♥♥♥♥♥

እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ

      ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
      ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን

አበባዮሽ 🌼 ለምለም   አበባዮሽ 🌼  ለምለም
እንቆቅልሽ   - -  ንግሥት   ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - -  ንግሥት   እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን -  ንግሥት   አጫወታቸው - -   ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼  ንግሥት  እያሳየችው - -    ንግሥት
መአዛው የሚሸት  - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - -  ለንጉሥ 

          ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
      🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ

እንቆቅልሹ -  -  የሳባ    ከበድም ቢለው -  -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ  ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - -  ሰለሞን   ቢለው ለሎሌው  - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ  - -  ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ  - -   መለሠ     ለተጠየቀው - -  በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - -   አለ     አልተሠወረው      🌼     በእውነት

 🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት   ምስጋና አቅርባ - -   ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት   ንግስተ ሣባ   🌼   ንግሥት
ጥበቡን አይታ - -  ንግሥት   አደነቀችው  - -    ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - -  ንግሥት  ዕንቁ ሰጠችው - -   ንግሥት

      ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
      የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼

የኢትዮጵያ ሠዎች  - -ለንግሥት   ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው     🌼   ለንግሥት   ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - -  ለንግሥት   ሀገር ስትገባ - -  ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - -  ለንግሥት   የፈካ አበባ    🌼ለንግሥት

      🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
      🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼

ኢየሩሳሌም - - ንግሥት   ደርሠሽ መጣሽ - -  ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት   ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት  ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - -  ንግሥት   ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት

      🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
      🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼

🌼የአባቶች ተስፋ - -   ለፃድቃን   የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - -     ለፀሎት   የአሮን በትር  - -   ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት    ይዘሸ የመጣሽ - -   ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ   ለሀገር መሠረት -    በእውነት🌼🌼

 🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
      🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼

በህገ ልቦና  - -   ህጉን     ፈጣሪን አውቀሽ - -  ህጉን
ህገ ነቢያትን - -  ከዓለም  ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን   🌼ለጌታ    መስዋዕት አቅርበሽ - -  ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን-  -በፊት    ይዘሽ ተገኘሽ    🌼    በፊት

      🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
      🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼

ካለፈው ሰህተት - -  ሁላችን    እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት  - -  ለሁሉም   መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው    ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - -  በጊዜው    ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ  - -  በጊዜው  🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት -  -  በጊዜው   ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ  - -  መጥምቁ      ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼

      🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼

ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ    🌼     አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ 🌼እያለች እማማ      አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ    አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ     አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)🌼

 🌼አበባ ለምለም 🌼 ቀጤማ ለምለም
    🌼ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)🌼

አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ🌼
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
🌼
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)

      ከበረው ይቆዩ ከብረው 🌼
       አመት አወደ አመት ደርሰው
      ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
      ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
      የፍቅር ሸማን ለብሰው🌼
      ንስሐ ገብተው ቆርበው
  🌼ከብረው ይቆዩ ከብረው
         
               መዝሙር
      🌼በማህበረ ፊልጶስ🌼saramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...