2018 ኤፕሪል 30, ሰኞ

ጥያቄና መልስ

ጥያቄና መልስ👇👇

1. አብርሃም ይስሐቅን ለመሥዋዕትነት ያቀረበበት ቦታ የት ነው? እዚህ ቦታ ላይ ሌላ ምን የተሰራ ነገር አለ?
መልስ፡- የሞሪያ ተራራ ሲሆን ሰሎሞን የመጀመሪያዋን ቤተመቅደስ እዚህ ቦታ ላይ የሠራው፡፡  ዘፍ.22÷2  ፣ 2ኛ ዜና 3÷1
2. በአብርሃምና በሎጥ መካከል ያለው ዝምድና አስረዳ?
መልስ፡- ሎጥ የአብርሃም የወንድሙ የሐራን ልጅ ነው፡፡ ዘፍ.11÷27
3. ለአዲስ ኪዳን ቁርባን ምሳሌውን ለአብርሃም ቀርቦ ያሳየን የብሉይ ኪዳን ካህን ማን ነበር?
መልስ፡- መልከጼዴቅ ነው፡፡ ዘፍ.14÷18 ፣ መዝ.109÷4   ፣ ዕብ.7÷1
4. የአብርሃም ልጅ ይስሐቅ የወለዳቸው ሁለት መንትዬች ማንና ማን ናቸው? እናታቸውስ ማን ትባላለች?
መልስ፡- ኤሳውና ያዕቆብ፡፡ እናታቸው ርብቃ ትባላለች ። ዘፍ.25÷22

5. አስራ ሁለቱ ነገደ እስራኤል በመባል የሚታወቁት እነማን ናቸው?
መልስ፡- ሮቤል፣ስምዖን፣ ሌዊ፣ይሁዳ፡፡ ዘፍ.29፣30፣35 በሙሉ፡፡

6. እስራኤላውያን ወደ ግብፅ የወረዱት በማን አማካኝነት ነው? ተመልሰው የወጡትስ በማን አማካኝነት ነው?
መልስ፡- በዬሴፍና በሙሴ፡፡ ዘፍጥረት እና ዘፀአት በሙሉ፡፡

7. ከ12 ነገደ እስራኤል ማለትም ከያዕቆብ ልጆች በግብፅ የሞቱት ስንት ናቸው? ማንና ማን ናቸው?
መልስ፡- ሁለት ሲሆኑ ዬሴፍና ሮቤል ናቸው፡፡

8. ከዕፀ በለስ ውጭ በገነት ውስጥ የነበሩት ሁለት ዕፅዋቶች ምንና ምን ነበሩ?
መልስ፡- ዕፅ እና ዕፀ ሕይወት ናቸው፡፡

#ሌሎች ጥያቄና መልሶችን ለማግኝነት ሊንኩን ይጫኑ👇#ሽር #በማድረግም #ለሌሎችም #ያድርሱልን👇
የኢ/ኦ/ተ/ቤተ/ን  ጥያቄና መልሶች የሚተላለፉበት ቻናል

https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjAsara mareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 25, ረቡዕ

የይሁዳ ጉዞ ጭውውት

የይሁዳ ጉዞ

ይሁዳ ሆይ ጉዞህ የሞት ሆኖብሃል
በንስሐ ታጥበህ ተመለስ ይልሃል
እድሜውን ጸጋውን አምላክህ ሰጥቶሃል
እውቀቱንም ቢሆን ከጌታ እግር ስር ብዙ ተምረሃል
ታዲያ መች ጠቀመህ ይህ ሁሉ ልፋትህ
ፍቅረ ነዋይ ዐይንህን አውሮብህ
ጉዞህ ፍጻሜው ሞት ነው ያውም የሞት ሞት
አሳልፈህ ስትሸጠው ውስጥህ ቢነድም በጸጸት
አልተመለስህም አልበቃህም ለንስሐ
ይልቅ ይህ ገንዘብ መውደድ አረገህ የመንፈስ ድሃ
ጌታህን ስትሸጥ በ30 ዲናር
ይህ እንዲመጣ አላወቅህም ነበር
የሰጠህን አትረፍርፎ ብዙ ጸጋ
አንተ ግን አቃለልከው አረከስከው ያለዋጋ
ይልቅ በምሴተ ሐሙስ ሚስጥር ተካፍለህ
ክቡሩን ቁርባን አብሮ መግቦህ
ምነዋ ታዲያ እርኩሱ መንፈስ አደረብህ
ታዘዝክለት ጌታህን ልትሸጥ ተስማማህ
ይሁዳ ያንተ ጉዞ የሞት ሞት ነው
የንስሐ እንባ ያላጠበ ያልጎበኘው
የገንዘብ ፍቅር አውሮት የህይወትን ምንጭ የናቀ
ከገዳዮቹ ተባብሮ ጌታውን በመሳም አሳልፎ የሰጠ
ጅማሬው አምሮ ነበር በክብር ከጌታ ጋር ሲመላለስ
ምን ዋጋ አለው ፍጻሜው ግን የሞት ሞት ነው ...
ያውም በገዛው መሬት የገዛ ደሙ ሲፈስ
የይሁዳ ጉዞ ምንም አልጠቀመው
ይልቅ ከእርስቱ ከዘላለም ቤቱ
ለይቶ አስቀረው እንዲሁ በከንቱ
ሁልጊዜ ይሁዳን ስንወቅስ ኖረናል
እኛስ ህይወታችን እንዴት እንደሆነ መች አስተውለናል
ከይሁዳ ከፍተን ጌታችን ስንት ጊዜ እኛስ ሸጠነዋል?
ውስጣችን እንመርምር ጉዟችንም ይቅና
የይሁዳ ጉዞ የሞት ሞት ነውና
እሱንም መውቀሱ አይጠቅመንምና
በንስሐ እንባ ከአምላክ ፊት ወድቀን
ስለ እናቱ ብሎ ስለቅዱሳን
እንደቸርነትህ ማረን ማረን እንበል
ለፍርድ የመጣ ለት በግራ እንዳንቆም
እንጽና በቤቱ እንኑር አአምላክ ጋር ፤
በህይወት መዝገብ ላይ ዘላለም ተጽፈን።
@tibebe11
@tibebe11
@tibebe11sara mareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 18, ረቡዕ

ለውድድር የቀረበ መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

ኤ ፊሶን ቤተክርስቲያን
2➡የሰርምኔስ ቤተክርቲቲያን
3➡የትያጥሮን ቤተክርስቲያን
4➡የሰርደን ቤተክርስቲያን
5➡የሎድቅያ ቤተክርስቲያን
6➡የጼረገሞን ቤተክርስቲያን
7➡የፊልዶፊልያ ቤተክርስቲያን ናቸው.

4⃣2⃣7 ሰባቱ ሰማያት የሚበሉትን ዘርዝሩ??

መልስ➡
1➡ጽርሀ አርያም
2➡መንበር መንግስት
3➡ሰማይ ወጹድ
4➡ሰማያዊ እየሩሳሌም
5➡ኢዩር
6➡ራማ
7➡ኤረር

4⃣3⃣ለመጀመሪያ ጊዜ ለቅዱሳን ሐዋርያት የተመረጡ 7 ሰባቱ ዳቆናት የሚባሉትን ዘርዝሩ

መልስ
1➡ቅስዱ እስጢፋኖስ
2➡ቅዱስ ጴጥሮስ
3➡ቅዱስ ኒቃሮስ
4➡ቅዱስ ጢሞና
5➡ቅዱስ ጴርሜና
6➡ኒቆላዎስ
7➡ቅስዱ ፊልጶስ

4⃣4⃣7ሰባትጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን እኔ ነኝ እኔነ ኝ እያለ ባንድ በቱ የተናገራቸው እነማን ናቸው ዘርዝሩ???

መልስ➡
1➡የህይወት እንጀራ እኔ ነኝ
2➡የአለም ብርሀን እኔ ነኝ
3➡እኔ የበጓች በር እኔ ነኝ
4➡መልካም እረኛ እኔ ነኝ
5➡ትንሳኤ ህይወት እኔ ነኝ
6➡እኔ መንገድና እውነት ህይወት እኔ ነኝ
7➡እውነተኛ የህይወት ግንድ እኔ ነኝ።

4⃣5⃣7ሰባቱ አባቶች የሚባሉት እነማን ናቸው?? ዘርዝሩ

መልስ
1➡ልኡል እግአዚብሔር
2➡የንስሀ አባት
3➡ወላጅ አባት
4➡የክርስትና አባት
5➡የጡት አባት
6➡የስልጣን አባት
7➡የቀለም አባት

4⃣6⃣እግዚአብሔር 7 የሚጠላቸው ነገር አሉ። ሰባተኛውን ግን አጥብቆ ይፀየፈዋል እነሱም ምን ምን ምን ናቸው???

መልስ
1➡ትንቢተኛ አይን
2➡ሀሰተኛ ምላስ
3➡ንፁህ ደም የምታፈስ እጅ
4➡ክፉ ሀሳብን የምታፈልቅ ልብ
5➡ወደ ክፉ የምትሮት እግር
7➡በወንድም አማቾች መካከል ጠብን የሚዘራ ናቸው።
በተማርነው 30፦ 60፦ 100 ፍሬን እንድናፈራ ልዑል እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን
ወስብኃት ለእግዚአብሔር
@Teyakaenamels
@Teyakaenamels
@Teyakaenamelssara mareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 16, ሰኞ

ዘመነ ትንሳኤን አስመልክቶ የቀረቡ ጥያቄና መልሶች

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
@Teyakaenamels
ክርስቶስ ትንሳኤ እሙታን
በዐብይ ኃይል ወስልጣልን
አሰሮ ለሰይጣን
አጋዐዞ ለአዳም
ሰላም
እምይዕዜሰ
ኮነ ፍስሀ ወሰላም
////    ;///
@Teyakaenamels
ጥያቄና መልስ👇

1ኛ✅✍ፋሲካ ማለት ምን ማለት ነው? ለእኛስ ፋሲካችን ማን ነው?  ማስረጃ ጥቀሱ?
መልስ፡- ፋሲካ ማለት ማለፍ ማለት ሲሆን ለእኛ ፋሲካችን ክርስቶስ ነው፡፡ ዘፀ.12÷1 ፣ 1ኛ ቆሮ.5÷8

2ኛ✅✍ የትንሣኤ ሁለተኛ ሣምንት ዳግም ትንሣኤ የሚባልበት ምክንያት ምንድን ነው?
መልስ፡- በተዘጋ ቤት ገብቶ ለሁሉም የተገለጠበት፡፡ ዮሐ.20÷19

3ኛ✅✍ከትንሳኤ በኋላ እስከ ዳግም ትንሳኤ ያሉ የዕለታትን ስያሜ ጥቀስ/ሽ??
መልስ፦👇
ሰኞ 👉ማዕዶት
ማክሰኞ 👉ቶማስ
ረቡዕ 👉አላዛር
ሐሙስ👉አዳም ሐሙስ
ዓርብ👉ቅድስት ቤተ ክርስቲያን

ቅዳሜ 👉ቅዱሳን አንስት

እሁድ👉 ዳግሚያ ትንሳኤ

4ኛ✅✍ክብር ይግባውና ጌታችንና መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለመቅደላዊት ማርያም ስለምን አትንኪኝ አላት???

መልስ፦ስለ 3 ምክንያት አትንኪኝ ብሏታል።

1ኛ - "ሶስት መዓልት ሶስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አድሬ እነሳለው" ብሎ የተናገረውን ስለረሳች ስለ እምነቷ ማነስ ሊገስጻት ፈልጎ ነው ፡፡ ለመላእክት ስለምን ታለቅሺያለሽ ሲላት "ጌታዬን ወስደውታል" አለች እንጂ ‹‹እንደተናገረው ተነስቷል›› አላለችም ዮሐ 20፡11-13

2ኛ - በዛው ወደ ባህሪ አባቱ የሚያርግ መስሏት እግሩን ስማ ልትሰናበተው ነበር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ግን የማርግበት ጊዜ ገና ነውና ለመሰናበት ብለሽ አትንኪኝ ሲላት ነው

3ኛ -ሥርዓተ ክህነትን ሲመሰርት ሴቶች ካህን መሆን "ሥጋወ ደሙን መፈተት" እንደማይችሉ ሥርዓት ሲሰራልን ነው!

 ለዚህም ማረጋገጫ ሐዋርያው ቅዱስ ቶማስን ግን እንዲዳስሰው የፈቀደለት ሲሆን መግደላዊት ማርያምን ግን አትንኪኝ ነው አላት፦
 " ቶማስን፣ጣትህን ወደዚህ አምጣና እጆቼን እይ፤እጅህንም አምጣና በጎኔ አግባው አለው"ዮሐ 20፡27::

ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ÷ ወደ አምላኬና ወደ አምላካችሁ አርጋለሁ " ምን ማለት ነው?ክርስቶስ አምላኬ ያለው ስለምንድን ነው?

በመጀመሪያ ክርስቶስ በመለየት ወደ አባቴ እና ወደ አባታችሁ አለ እንጂ ወደ "አባታችን" አላለም እንዲሁም ወደ አምላኬና አምላካችሁ አለ እንጂ ወደ "አምላካችን" ብሎ ጠቅልሎ አልተናገረም!
 እንዲህም ለይቶ ማለቱየእርሱ የእግዚአብሔር ልጅ መባልናሕ የእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች መባል ፍጹም የተለያየ በመሆኑ ነው፡፡ እርሱ፥ «አባቴ» ቢል የባሕርይ ልጅ በመሆኑ
ነው፡፡ እነርሱ ግን የጸጋ ልጆች ናቸው፡፡ እርሱ፥ «አምላኬ» ቢል ስለተዋሐደው
ሥጋ ነው፡፡ የተዋሐደው የፈጠረውን ሥጋ ነውና ፡፡ እነርሱ ግን «አምላካችሁ»
ቢባሉ ፍጡራን ስለሆኑ ነው፡፡ በዚህም እርሱ ፈጣሪ እነርሱ

ፍጡራን መሆናቸውን አስረግጧል።

5ኛ✅✍የመጀመሪያው ፋሲካ በየት ተከበረ???

//መልስ//🖊 ግብጽ ውስጥ በችኮላ እንደተከበረ ከዘጸ 12, 1-20 እንረዳለን ነገር ግን ትክክለኛው ፋሲካ ወይም “ማለፍ” ወይ “መሻገረ” የሚለውን ትርጉም በሚያሳይ መልኩ የተከበረው ግን የግብጽን የባርነት ኑሮ አልፈው ከወጡ በኋላ እንደሆነ ከዘጸ 12, 43- 51 ላይ እንረዳለን ፡፡ በዘጸ 12, 21 በእንዲህ ዓይነት ሁኔታ እንደተከበረ እንረዳለን ፦

6ኛ✅✍ከትንሳኤ እሁድ በኋላ የሚውሉ የዕለታትን ስም ስያሜ ትርጉም አስረዱ??

✍ሰኞ ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር ማለፍ ማለት ነው በዚህ
ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን
ከሞት ወደ ሕይወት ከሲኦል ወደ ገነት ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን
እናስባለን::

✍ማክሰኞ ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ ጌታዬና
አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል ዮሐ. 20፡27-29::

✍ ረቡዕ አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው ጌታ
ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን ክርስቶስ የሞትን ስልጣን
የሻረ የሕይወት ራስ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ በድልም ያረገ ንጉሥ
መሆኑን እንመሰክራለን::

✍ሐሙስ አዳም ሐሙስ ይባላል፡ በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና
የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን::

✍አርብ ቅድስት ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን
በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ  ይሰበካል ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን
አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ጥቶ ስለመመስረቷእንዳከበራት
ይነገራል ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው ክርስቶስ
ለሕንፃ አልሞተምና::

✍ ቅዳሜ ቅዱሳት አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን
አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና
ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል::

✍ እሁድ ዳግም ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ
ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል::

ወስብኃት ለእግዚአብሔር.
https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjAsaramareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 15, እሑድ

ድንግል እመቤቴ

ድንግል እመቤቴ የአምላኬ እናት
የሰማእታት ክብር የአቤል ደግነት
የሲና ልምላሜ የያእቆብ መሰላል
የአሮን በትሩ ወላዲተ ልኡል
የሙሴ ፅላቱ የአዳም መዳን ተስፍ
የኤልሳ ማሰሮ የአይናችን ማረፊያ
አምባ መሸሸጊያ ከሞት ማምለጫችን
ስምሽ የሚያጠግብ ሲርበን ምግባችን
ሲከፍን መፅናኛ ፈጥነሽ ደራሻችን
በቃ ሁሉ ነገር የሆንሽ አለኝታችን
ዛሬ ግርም ቢለኝ መጣው ልጠይቅሽ
ያንን ክፍ ስደት እንዴት ስ እንደቻልሽ
የበረሀው ትልቀት
የአሸዋው ግለት
ድንግል እመቤቴ እንዴት ነበር ያኔ...??
የውሀ ጥም እንግልት
ደረሱብኝ ብለሽ ደግሞ ያሀ ጭንቀት
እንዴት ቻልሽው ከቶ ገና በለጋ እድሜሽ
የስደት መከራ እንዴት አለፈልሽ
ብጨንቀኝ እኮ ነው ...
ህይወት ግራ ሆና ሁሉ ቢጠምብኝ
ስድትን ቀምሸው መቋቋም ቢያቅተኝ
መቻል የሚባለው ውሉ ቢጠፋብኝ
ጠየኩሽ እናቴ.......
የስደትን ነገር  ጠንቅቀሽ ታውቂያለሽ
እስኪ መላ በይኝ ለኔ ከንቱ ልጅሽ
እባክሽ እመ አምላክ ......
የግብፅን በረሀ ሀሩር በሞላበት
ሁሉን እንደቻልሽው እንዳለፍሽ በትእግስት
እኔንም አበርቺኝ አደራ እመቤቴ
ተወሳስቦብኛል ተሳስሯል ህይወቴ
ተስፍዬ ተሟጧል
ልቤ ተረብሿል
ባዶነቴ በዝቶ ኑሮዬ ቅጥ አጥቷል
በቃ ምንበልሽ ..........
ብቻ በደፈናው እኔነቴ ሞቷል
እናም እመቤቴ ተመልከች ልጅሽን
በእጆችሽ ደባብሽኝ ደካማ ባሪያሽን
አበርችኝ እናቴ ትእግስት አድይኝ
ስደክም ምርኩዜ ብርታት ሀይሌ ሁኝኝ

2018 ኤፕሪል 4, ረቡዕ

*©መዝሙር በእንተ ስቅለቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ©* . .

*©መዝሙር በእንተ ስቅለቱ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ©*
.
.

©ጌታ ሆይ

ጌታ ሆይ አይሁድ አማጽያን ሰቀሉህ ሆይ
የዓለም መድኃኒት የዓለም ሲሳይ ሰቀሉህ ሆይ /2/
የአዳም በደል አደረሰህ አንተን ለመስቀል
የሔዋን ስህተት አበቃህ ለሞት ቸሩ አባት /2/
ንጹሕ ክርስቶስ ሆንክ ወንጀለኛ ብለህ ስለኛ
መስቀል አሸክመው አሥረው ገረፉህ እያዳፉህ /2/
እጅና እግርህ በብረት ተመታ የዓለም ጌታ
የእሾህ አክሊል ደፍተህ ጐንህም ተወጋ አልፋ ፆሜጋ /2/
ግብዞች እንደራሳቸው መስሎአቸው
ምራቅ እየተፉ በፊትህ ቀለዱ አንተን ሊጐዱ /2/
በመስቀል ላይ ተጠማው ስትል ታላቅ በደል
ሐሞትና ከርቤ ሰጡህ ቀላቅለው ጠጣ ብለው /2/
ይቅር ባይ በደላችንን ሁሉን ሳታይ
አንተ ይቅር በለን በእኛ ሳትከፋ እንዳንጠፋ /2/

//////////////////////////////////
*©ኦ ዘጥዕመ*

ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ(፫)
ሲጠማ ለኖረው በሲፆል በረሃ
ከጎኑ ሊያጠጣው የሕይወትን ውሃ
በክብር ሊመልሰው በኤዶም ለያኖረው

በመስቀል ተሰቅሎ ሊያድነው ከፍዳ
ከዙፋኑ ወርዶ ለብሶ ከለሜዳ
በሰው እጅ ተመትቶ በችንካር ተወግቶ

ግዕዛንን ለሰብክ ወደ ሲኦል ወርዶ
ምዉቱን ሊያድነው እራሱን አዋርዶ
ሊቀድስ በደሙ ሊያከብር በስሙ
////////////////


*©አልፍና ኦሜጋ*

አልፍና ኦሜጋ ፈጣሪ የሆንክ
በከሃዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ
         አዝ
ተገፍህ ተደፋህ በጥፊ ተመታህ
እየደበደቡ ክርስቶስ ሆይ አሉህ
ጽድቅን ስለሠራህ በወንጀል ከሰሱህ
ለአዳም ቤዛ ብለህ ብዙ ተንገላታህ
             አዝ
ቅዱሳን እጆችህ የፊጥኝ ታስረው
እንደበግ ጎተቱህ ልትምራቸው
የትም ቦታ ያለህ ሁሉን የምታውቅ
ፊትህን ሸፈኑህ በመመጻደቅ
      አዝ
በአውደ ምኩናን ከጲላጦስ ዘንድ
አሳልፈው ሰጡህ አጋልጠው ለፍርድ
ከሐና ቀያፋ ከመሳፍንት እጅ
ከነሄሮድስ ዘንድ አቀረቡህ በአዋጅ
         አዝ
ግርፋት ሕማሙ አልበቃም ብሎህ
በመስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ
ሳዶርና አላዶር ዳናትና አዴራ
 ተፈልገው መጡ ሮዳስ ለችንካር
         አዝ
የሰላም ባለቤት ደረትህ ተወጋ
ሊያያዝ በችንካር እጅህ ተዘረጋ
ግፈኞች አይሁድ በአንተ ላይ ቀለዱ
ምራቅን ተፋብህ እራስክን ሊጎዱ

//////////////////////


*©በጌቴ ሴማኒ*

በጌቴ ሴማኒ በአትክልቱ ቦታ (፪)
ለእኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላታ (፪)
አዳምና ሔዋን ባጠፉት ጥፋት (፪)
ለእኛም ነበረብን የዘላለም ሞት (፪)
መስቀል ተሸክሞ ሲወጣ ተራራ(፪)
ይገርፉት ነበረ ሁሉም በየተራ(፪)
ድንግል አልቻለችም ዕንባዋን ልትገታ (፪)
እያየች በመስቀል ልጇ  (፪)
በአምላክነቱ ሳይፈርድባቸው(፪)
እንዲህ ሲል ጸለየ አባት ሆይ ሲንገላታማራቸው(፪)
በረቂቅ ሥልጣኑ ሁሉን የፈጠረ/፪/
በሰዎች ተገርፎ ሞቶ ተቀበረ(፪)
ፍቅሩን የገለጸው ተወልዶ በሥጋ(፪)
ኢየሱስ ጌታ ነው አልፋና ፆሜጋ(፪)

//////////////////////////


*©በዕፀ መስቀል ላይ*

   /ዘማሪት ማርታ ኃ/ሥላሴ ፩/

በዕፀ መስቀል ላይ በዚያ አደባባይ/2/
አምላክ ሆይ  ጌታ ሆይ መከራ አየህ ወይ
አምላክ ሆይ  ጌታ ሆይ ተንገላታህ  ወይ

መስቀል አስይዘው ኪርያላይሶን
ወደ ጎልጎታ              >>
ሲገርፉህ ሲያዳፉህ          >>
ስትንገላታ              >>

አዝ…

ያንን አቀበት       ኪርያላይሶን
ያንን ዳገት               >>
ጀርባህ ተገርፎ            >>
ስትቃትት                >>

አዝ…             

መስቀል አስይዘው  ኪርያላይሶን
እንዲያ ሲያዳፉህ          >>
የቀሬናው ሰዉ             >>
ስምዖን አገዘህ             >>

//////////////////////////


*©ሕማም የማታውቀው*

    /ዘማሪት አዳነች አስፋው ቁ.፪/

   ሕማም የማታውቀው ድካም የሌለብህ
   ስለኛ ተራብህ ደከምህ በእውነት
   የደም ላብ አላበህ ብዙም አስጨነቁህ
   እጅና እግርህን አስረውት አይሁድ አንገላቱህ/፪/

በቀርክሃ በጅራፍ አምላኬ ገረፉህ
በፈጠርከው ፍጥረት መወጋት መድማትህ
ምን ይሆን ምሥጢሩ ያንተ መንገላታት/፪/

     መንፈሳዊ አርበኛ ማርያም መግደላዊት
     ያንተ ሕማም ሞት ያንተ ስቃይ ጨንቋት
      በእኩለ ሌሊት ፅልመቱን ሳትፈራ
      አመጣት ጎትቶ የፍቅርህ አሻራ/፪/

ያ ሁሉ መከራ እንዴት ይግባ ልቤ
አልበጠስ አለኝ የኃጢአት መረቤ
መቼ ይሆን ፍቅርህ ለእኔ የሚገባኝ
ሕማም ጉስቁልናህ ልቤን የሚነካኝ/፪/

     ቃሉን ተናጋሪ ምግባር የሌለኝ

     ተገርፏል ተሰቅሏል የምል ብቻ ሆንኩኝ/፫/
ተው ልቤን ስበረው ልመንህ አጥብቄ
መቼ ሕይወት ሆነኝ ሕግህን ማወቄ
እባክህ የኔ ጌታ መንፈሴን ስበረው
የመስቀሉን ፍቅር በልቤ ላይ ሳለው/፪

//////////////////////

*©ምንኛ ድንቅ ነው*

  /መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ሰ/ት/ቤት/

ምንኛ ድንቅ ነው የአምላክ ሥራው/2/   አዝ
ዙፋኑን ትቶ/2/ቀራንዮ/2/የዋለው

ፈራጅ አምላክ ሲሆን ሊፈረድበት
በአደባባይ አቆሙት ሊሳለቁበት
በጅራፍ አካሉን ሲገርፉት
ዝም ማለቱ እንደሌለው አንደበት

አዝ…
መስቀል አሸክመው እስከ ቀራንዮ
ሲስቡት ሲገርፉት ሲጮሁ ሲሉ ወዮ
ሲጥሉት ሲያዳፉት  እየገፈተሩ
ይህ ሁሉ ትዕግስት ምን ይሆን ምሥጢሩ

አዝ…
እርቃነ ሥጋውን ከመስቀል አስተኝተው
በአምስቱ ችንካሮች አካሉን ቸንክረው
ያለ ርኅራሄ ደሙን ሲያፈሱት
የእሾህ አክሊል ሰርተው እያቀዳጁት

አዝ…
የግፍ ግፍ ሲሠሩ በገዛ ግዛቱ
ኧረ ለምን ይሆን ዝም ብሎ ማየቱ
አዳምን ሊያወጣው ከባርነቱ
ሊመልሰው ወዶ ከገነት ከቤቱ

///////////////////////////


*©እስመ ለዓለም ምሕረቱ*

እስመ ለዓለም ምሕረቱ
                 እስመ ለዓለም ምሕረቱ  /4/
               አያልቅም ብዙ ነው የአምላክ ቸርነቱ

አመስግኑት ጌታን ሁላችሁ በአንድነት /2/
መሐሪ ነውና ለሰው ልጆች ሕይወት  /2/

                          አዝ
የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው /2/
ከገሃነም እሳት እኛን ሊያድን ነው /2/

                        አዝ
ከማርያም የነሣው ያ ቅዱስ ሥጋው
ቀራንዮ ሲውል የሚያሳዝን ነው 

                      አዝ
በፈጠረው ፍጥረት እጅግ ተሰቃይቶ
ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ለይቶ  /2/

/////////////////////

*©ምድረ ቀራንዮ*

ምድረ ቀራንዮ ከጠዋት እስከ ሰርክ/2/
የእሾህ አክሊል ደፍተህ በመስቀል ላይ ዋልክ 

በቀራንዮ ጎልጎታ ጌታ በችንካር ተመታህ
ለዓለም ቤዛ ልትሆን ራስህን ለሞት ሰጠህ

እንደ ወንበዴ ታስረህ ሲቸንክሩህ እጅህና እግርህን
ለጠላቶችህ ክፉ አላሰብክም ይቅር በላቸው ነው ያልህ

ይሁዳ ሞኙ ተላላ ጌታውን ሽጦ ሊበላ
ገንዘብን ብቻ በመውደድ ገመድ ሆነችው ዘመድ

በዕለተ ዓርብ ስድስት ሰዓት ጌታን በመስቀል አውለውት
በግራ በቀኝ ፈያት መካከል እሱን ሰቀሉት

በኪሩቤል ላይ የሚኖር በቀራንዮ ተሰቀለ ለአዳም ክብር
እንደ ወንበዴ ተገረፈ ሥጋው አለቀ ተገፈፈ

አገኘን ብለው ልዩ ልብስ ተከፋፍለዋል ቀሚስህን
እሱን ሲሰቅሉት ጎልጎታ ወንበዴው በርባን ተፈታ

//////////////////////////


*©ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን*

ዘጠኝ ሰዓት ሲሆን አባት ሆይ
በመስቀል ሆነህ አባት ሆይ
ድምጽህን በማሰማት አባት ሆይ
ነፍስህን ሰጠህ አባት ሆይ

ከዋክብተ ሰማይ በሙሉ ረገፉ
ጨረቃና ፀሐይ ደምን አጎረፉ
ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ
ሥጋህን በመስቀል ተገልጦ ስላዩ

ጌታችን ክርስቶስ በመስቀል ላይ ሳለ
አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ
ማርና ወተትን ለሚመግበው
ሐሞት አመጡለት ይቅመሰው ብለው

አካሉ ሲወጋ ውኃ ደም ፈሰሰ
በምድር ተረጭቶ ዓለምን ቀደሰ
የእሥራኤል ሴቶች ዋይ ዋይ ሲሉልህ
ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለአንተስ አላሰብክም

እናትህ ስታለቅስ በመስቃል ሥር ሆና
ዮሐንስን ሰጠህ ጠብቆ እንዲያፅናና
መላእክትም ታዩ አጋንንትም ሸሹ
የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

/////////////////////

*©ሕሙም ስላዳነ*

   /ዲ/ን ዳዊት ቁ.፩/

ሕሙም ስላዳነ በእጆቹ ዳስሶ
ሙትን ስላስነሣ በእጆቹ ዳስሶ
ይህም በደል ሆኖበት ለአምላክ ኖላዊ ሔር
በዕፀ መስቀሉ ላይ ዘርግቶ በፍቅር
ቀኝ እጁን በሳዶር ግራውን በአላዶር
ተቸነከረልን ጌታ በሁለት ችንካር

*አምንስቲቲ ሙኬርያ አንቲ ፋሲልያሱ*

ቤተ መቅደስ ምኩራብ በተመላለሱ
ባሕር ላይ በሔዱ ልክ እንደ በየብሱ
ለአምላክ ቤዛ ኵሉ ይህ ወንጀል ሆኖበት
በዕፀ መስቀሉ ላይ ተላልፎ ለመሞት
ሁለቱን በአንድ ላይ እግሮቹን በዳናት
ተቸነከረልን አምላክ የእኛ ሕይወት

*አምንስቲቲ ሙዓግያ አንቲ ፋሲልያሱ*

በልቡ አስቦ ድኅነት የሚያመጣ
ከበጎ ልቦናው በጎ የሚያወጣ
ይህ ወንጀል ሆኖበት ለአምላክ መድኅን ዓለም
በዕፀ መስቀሉ ላይ ተዘርግቶ ለዓለም
ልቡን በአዴራ ደረቱን በሮዳስ
ተቸነከረልን ወልደ አምላክ ክርስቶስ

*አምንስቲቲ ሙዳሱጣ አንቲ ፋሲልያሱ*

///////////////////

*©ድንግል የዚያን ጊዜ*

   /ዘማሪት ማርታ ኃ/ሥላሴ ቁ.፩/

ድንግል የዚያን ጊዜ/2/ ሐዘንሽ በረታ /2/
በመስቀል ላይ ሆኖ ልጅሽ ሲንገላታ/2/

አዝ…

ሴቶች ሲያባርሩት የዚያን ጊዜ ራርቶ ሆድሽ
ለፍጡር በማዘን ውሃ ያጠጣሽ/2/

አዝ…

ተጠማሁ እያለ የዚያን ጊዜ ሲናገር ልጅሽ
ታድያ እንደምን ቻለ ድንግል አንጀትሽ/2/

አዝ…

እንደዚያ ስታለቅሽ የዚያን ጊዜ ሐዘን ሲውጥሽ
እነማን ነበሩ ያስተዛዘኑሽ/2/

አዝ…

ስታለቅሽ በማየት የዚያን ጊዜ ራርቶ ልጅሽ
ዮሐንስን አጽናኝ እንደ ልጅ ሰጠሽ/2/

አዝ…

///////////////////

*©ግሩም ነው* 

   /ዘማሪት ማርታ ኃ/ሥላሴ ቁ.፫/

ግሩም ነው ግሩም /2/ የአምላክ ሥራ ግሩም ነው         
ዕፁብ ድንቅ አዳምን ለማዳን ያደረገው እርቅ/2/


ለጊዜያዊ ጥቅም ልቡ ስለሳሳ
ይሁዳ ሕይወቱን ሸጠው በሠላሳ
ጠላትህን ውደድ ብሎ እንዳስተማረው
ያስያዘውን ይሁዳ ወዳጄ ሆይ አለው

አዝ…..
እውነተኛ ፍቅር ነውና እስከ ሞት
መስቀል ተሸክሞ ሄደ ወደ ስቅለት
አንቺ ቀራንዮ የመስቀል ተራራ
ለዓለም መስክሪ የወልድን መከራ

አዝ…
የመድኃኔዓለም ደም የፈሰሰበት
መስቀል ኃይላችን ነው ከሞት የዳንበት
አምላክ ከሠራቸው ድንቅ ዕፁብ ሥራዎች
ይበልጣል ያሳየው ፍቅርን ለሰው ልጆች

አዝ…
ቀድሞ የገባለት ቃል ኪዳን ስላለ
ዐርብ ለፈጠረው ዐርብ ተሰቀለ.

//////////////////

*©ሙታንን ያድን ዘንድ*

ሙታንን ያድን ዘንድ የሞት ሞትን ሽሮ /2/
ወልደ አምላክ ሄደ ወደ ኋላ ታሥሮ/2/
ግርማን ለኪሩቤል ያጐናጸፋቸው
ዘውድን ለሱራፌል የሚያቀዳጃቸው
ከለሜዳ ለብሶ ዋለ ከፊታቸው

ቅዱሳን እጆቹ አዳምን የሠሩት
ቅዱሳን እግሮቹ በገነት የዞሩት
ተቸንክረው ዋሉ በጠንካራው ብረት

በምን በበደለ ነው ምን ባደረገ ነው/2/
ወልድ እንደ ቀማኛ ሲገረፍ የዋለው

አዳም በበደለ የግፍ ግፍ በሠራ
ቸሩ ወልደ አምላክ ዋለ በመከራ

ሁሉንም ታገሰ ሁሉን ቻለ ሆድህ
ትልቁም ትንሹም ሲዘባበትብህ

//////////////////////


*© ሞት ስለእኛ*

     ሞተ ስለእኛ /2/ የነገስታት ንጉስ
     የኃያላን ዳኛ ሞተ ስለኛ /2/

     ጐለጐታ እስኪደርስ ሰቃይ ተቀበለ
     ሥጋው ተዳከመች በመከራ ዛለ
     በጅራፍ ተገርፎ ደም ነጠበ ገላው ሞተ ስለእኛ /2/
   
     የሚካኤል ዝም አለ ተገርሞ አስተዋለ
     ገብርኤል ሰይፉን ወደ ምድር ጣለ
     ከዋክብት ደንግጠው ረገፉ ዛሬ
     መላእክት አለቀሱ ቀረና  ዝማሬ
     ሞተ ስለእኛ /2/

     ዑራኤል አምላኩን በመስቀል ላይ አየ
     በብርሃን ጽዋ ደሙን ተቀበለ
     ዕንባው አላቆሙም ጌታው ሲንገላታ
     ተገርሞ አስተዋለ በጥፊ ሲመታ
     ሞተ ስለእኛ /2/saramareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 3, ማክሰኞ

የሰሞነ ሕማማት ጥያቄና መልሶች

https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjA
https:


https://youtu.be/lwfQaXDUk58
✝➡የሰሞነ ሕማማት ጥያቄና መልስ እንደ ሚከተለው ነው፦👇👇👇👇👇

✍ጥ.ተራ.ቁ.1⃣➡በዕለተ አርብ  ስግደት ከሰገድን በኋላ ለምንድ ነው ካህናቱ ጀርባችን በወይራ ዘንጣፌ ቸብ ቸብ የሚያደርጉት??

✝መልስ✝🖊 ወይራ በባህሪው  ጠንካራ  ነው 
እናተም ጠንካራ እሙን የሆነ ክርስቲያን ሁኑ ሲል አንድም  በኖህ ዘመን የጥፋት ውሃ ጎደለ ስትል እርግብ የወይራ ዝንጣፌ ይዛ መጥታለች  እኛም በወይራ ዘንጣፌ ጀርባችን መመታቱ የኃጢአት ቀንበር ተወገደላችሁ ሲል በእርሱ ቸብቸብ እንደረጋለን አንድም የሚወደኝ ቢኖር መስቀሌን ተሸክሞ ይከተለኝ እንዳለው እኛም  በጀርባችን መስቀሉን ተሸክመናል ስንል አንድም መከራው በሚመስል መከራውን ከመሰልን ትንሳኤውን በሚመስል ትንሳኤውን እንመስላለን ስንል።

✍ጥ.ተራ.ቁ.2⃣በሰሞነ ሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም ? ??


✝መልስ✝🖊የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀለ ከተሰቀለ በኋላ ነው በሰሞነ ሕማማት ከሰኞ እስከ አርብ ያሉት ቀናት የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው በነዚህ ዘመናት ሰዎች የመስቀልን አገልገሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት በሰሞነ ሕማማት በቤተክርስተያን ሥርዓት መሠረት መስቀል መሳለምም ሆነ የማማተብ ሥርዓት የለም።


✍ጥ.ተራ.ቁ 3⃣➡በሰሞነ ሕማማት ለምን አንንሳሳምም???


✝መልስ✝🖊

✍ይሁዳ በመሳም ጌታውን  አሳልፎ ሰጥቶአል እኛም እንደ ይሁዳ ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችችንን ለማሰረዳት ከዚሀ በተጨማሪም ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ ለማሳየት በሰሞነ ሕማማት እሰከ ምሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሠላምታ የለም።

✍ጥ.ተራ.ቁ.4⃣➡ኪርያላይሶን ማለት ምን ማለት ነው ቃሉስ የምን ቃል ነው??


 ✝መልስ✝👇🖊ቃሉ የግሪክ(ጽርዕ) ሲሆን አጠራሩ "ኪርዬ  ኤሌይሶን"ቃሉዉ፡፡ "ኪርያ" ማለት "እግዝእትነ / እመቤታችን" ማለት ሲሆን "ኪርዬ" ማለት ደግሞ "እግዚኦ / ጌታ ሆይ / አቤቱ" ማለት ነዉ፡፡ "ኤሌይሶን" ማለት ደግሞ "ማረን / ይቅር በለን" ማለት ነዉ ፡፡ ሲጠራም "ኪርዬ ኤሌይሶን" መባል አለበት፡፡ ትርጉሙም "አቤቱ ማረን" ማለት ነዉ፡፡ "ኪራላይሶን" የምንለዉ በተለምዶ ነዉ፡፡ ይኸዉም "ኪርዬ" ከሚለዉ "ዬ" ኤሌይሶን" ከሚለዉ ደግሞ "ኤ" በመሳሳባቸዉ በአማርኛ "ያ"ን ፈጥረዉ ነዉ፡፡


✍ጥ.ተራ.ቁ.5⃣➡አክፍሎት፡ ምንድን ነው?? እስኪ ስለ አክፍሎት አብራ/ሪ


✝መልስ✝🖊በሰሙነ ሕማማት ዕለተ ዓርብ ከስግደት በኋላ ምእመናን በየቤታቸው ጥቂት ነገር ለቁመተ ሥጋ ቀምሰው እስከ እሁድ /የትንሳኤ / ይሰነብታሉ፡፡ ይህ አክፍሎት ይባላል፡፡ ከአርብ እስከ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ብዙዎች ያከፍላሉ፡፡ አንዳንዶች ግን ከሐሙስ ጀምረው ያከፍላሉ፡፡ ይህም እመቤታችን፤ ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታን ትንሳኤ ሳናይ እህል ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤ መቆየታቸውን ተከትሎ የመጣ ትውፊት ነው፡፡
ይህንን ትውፊት አስመልክቶ ሄሬኔዎስ፤ አውሳብዮስ የተባሉ ጸሐፍት፤ ሐዋርያት በሰሙነ ሕማማት ከደረቅ ዳቦ እና ከትንሽ  በቀር እንደማይመገቡ፤ ከሐሙስ ጀምረው እንደሚያከፍሉም ጽፈዋል፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ሐዋርያት ሌሎቹንም እንዲያከፍሉ እንዳሳሰቡና ውኃ ከሐሙስ ጀምሮ ያልተቻለው ቢያንስ ከዓርብ ጀምሮ እንዲያከፍል ማዘዛቸውን ጽፈዋል፡፡ የእኛ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትም ይኸው ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.6⃣➡ ስለ ጉልባን ትውፊት አስረዳ/ጅ??


 ✝መልስ✝🖊ጉልባን ከባቄላ ክክ፤ ከስንዴ ወይም ከተፈተገ ገብስ ጋር አንድ ላይ ተቀቅሎ የሚዘጋጅና የጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ነው፡፡ የጉልባን ትውፊት እስራኤላውያን ከግብፅ ተሰደው በሚወጡበት ጊዜ በችኮላ ስለነበር አቡክተው ጋግረው መብላት ያለመቻላቸውን ሁኔታ ያመለክታል፡፡ ያን ጊዜ ያልቦካውን ሊጥ እየጋገሩ ቂጣ መብላት፤ ንፍሮም ቀቅለው ስንቅ መያዝ ተግባራቸው ነበር፡፡ ይህን ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ቂጣና ጉልባን በማዘጋጀት በዓሉ ይታወሳል።

✍ጥ.ተራ.ቁ.7⃣➡ክብር ይግባውና ጌታችና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶ በጸሎተ  ሐሙስ ምን ምን ነገሮችን  ያከናወነበት ዕለተ ነው?? 

✝መልስ✝👇🖊

በዚች ዕለት ጌታ በፍጹም ትሕትና የደቀመዛሙርቱን እግር ያጠበበት፤ ከሐዋርያት ጋር ግብር የገባበትና የክርስትና ሕይወት ማሕተም የሆነውን ምስጢረ ቁርባን ያከናወነበት ዕለት ነው፡፡
አንድም ሕጽበተ እግር ጌታችን እናንተ ለወንድማችሁ እንዲህ አድርጉ በማለት የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት የተሰጠ ምሳሌ ነው፡፡ ይህም የሚያሳየው እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና፤ እውነት እውነትኽ እላችኋለሁ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም፤ መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም፤ ይህን ብታውቁ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ 《  ዮሐ.13፡16-17 》በማለት ትሕትናውን አሳይቷል፡፡

✍ጥ.ተራ.ቁ8⃣➡ቄጤማ የምን ምሳሌ ነው?? በቀዳም ስዑርስ ለምን በግንባራችን ላይ እናስራለን??

✝መልስ✝👇🖊
✍በቀዳም ስዑር ቀሳውስቱና ዲያቆናቱ ቃጭል 《 ቃለ ዓዋዲ 》እየመቱ ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሳኤሁ አግሃደ የሚለውን ያሬዳዊ ዜማ በመዘመር ጌታ በመስቀሉ ሰላም እንደሰጠን እና ትንሳኤውንም እንደገለጠልን በማብሰር ቄጤማውን ለምእመናን ይሰጣሉ፡፡ ምእመናኑም ገጸ በረከት ያቀርባሉ፤ ቄጤማውንም በራሳቸው ያስራሉ፡፡ ይህም አይሁድ ጌታችንን እያሰቃዩ ሊሰቅሉት ባሉ ጊዜ የእሾህ አክሊል ጭንቅላቱ ላይ ያሰሩበትን ድርጊት የሚያስታውስ ነው፡፡
በዚህ ዕለት ልብሰ ተክህኖ የለበሱ ካህናትና ዲያቆናት ቄጤማ ተሸክመው፤ ቃጭል ሲያቃጭሉ መታየታቸው ዕለተ ትንሳኤውን ለሚናፍቁ ምእመናን ትልቅ ብስራት ነው፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 2, ሰኞ

ከፊያታዊ/ጥጦስ/ የተላከ ጦማር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን✝


ከፊያታዊ ዘይማን (ጥጦስ) የተላከ ጦማር
==========================
 ከሁሉ አስቀድሜ ታናሽነት ያልቀደመህ ታላቅ ዘመን የሌለህ ቀዳማዊ ድህነት የማይስማማህ  ባለጠጋ ለሆንከው ለንጽሀ ባህርይ ለድንግል ማርያም ልጅ ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና ከባህርይ አባትህ ከአብ ከባህርይ ህይወትህ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ይሁን አሜን

ቀኑ ሽብር የነገሰበት ሙታን በሞት  የተዋጠ ዝምታቸዉን  ሰብረዉ የተናገሩበት አንዳንዶቹ የዘላለም ሞትን አንዳንዶቹ ደግሞ የዘላለም ህይወትን የወረሱበት እለት ነዉ። በእለቱ ብዙ እስረኞች አመለጡ ከእነዚያ መካከል በዉንብድና ወንጀሌ ተይዤ የሞት ፍርድ የተላለፈብኝ አንዱ ነበርኩ።
ታድያ፦ ከስድስት ሰዓት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ለሶስት ሰዓታት እኔ ከነብስ አባቴ ከክርስቶስ ጋር ተነጋግሬ ቀኖና ተሰጦኝ ስለሀጢአቴ የቀኖና ሰዓት እንጂ የቅጣት ሰዓት አልነበረችም ለሶስት ሰዓት የተሰጠኝን ቀኖና ጨርሼ የደም ማህተም ያረፈበት የነጻነት ደብዳቤ ከንጉሱ ተቀብየ በነፋሳት ጀርባ ተጭኜ እየበረርሁ የምስራቹን ለማዳረስ በምድር የተደረገዉን ድንቅ ነገር ገነትን ይጠብቁ ለነበሩ መላዕክት ለማድረስ ገሰገስሁ
እናም ከገነት ቅጥር  እስክደርስ ማንም  አልተናገረኝም  የእሳት  ባህሩ አላገደኝም  የሞት  ስልጣንም  አላገደኝም  የያዝሁት  ደብዳቤ  ከንጉሱ  ነበርና  ወደ  ገነት  እየተጠጋሁ  ስመጣ ግን አይኖቼ ያዩትን ማየት  ተሳናቸዉ።

ቁመቱ  ከምድር እስከ  ሰማይ  ይደርሳል  የክንፎቹ  ርዝመት  ሰዉ  አይመጥናቸዉም አይኖቹ  እንደ እሳት  ነበልባል  ይንቀለቀላሉ  የምትገለባበጥ የእሳት ሰይፍን  በእጁ  ጨብጧል በዚያች  የመከራ  ቀን  በአዳም ፈንታ  ገነትን  ይጠብቅ ዘንድ  የተሰየመዉ  ኪሩብ መላዕክ ነበር።መካከል
በዚህ ጊዜ  ከፊት ለፊቴ  የቆመዉ መላዕክ  በመገረም  ተዋጠ   ። የሰዉ  ልጆች  ወደዚህ  ክልል መግባት  ካቆሙ 5534 ዘመናት  ተቆጥረዋል  በገነትና በሰዉ  ልጆች  የእሳት ባህር  ተዘርግቷል  በዚህም  ምክንያት  ተሻግሮ መምጣት  የቻለ  የሰዉ  ዘር እንዴት አልነበረም   እኔ  ግን ይህን  ባህር  ተሻግሬ  ከገነት በር  ስደርስ  ጠባቂዉ መለዓክ  መኑ  አንተ ማነህ  አንተ  የእሳቱንስ  ባህር   አለፍኸዉ  አለኝ።
ከዚች  ሶስት  ሰዓት  በቀር  በጎ  ስራ  ያልሰራሁ እኔ  የትኛዉ  ስራየን  ልንገረዉ   እጀን  በሰዉ  ደም ነክሬ  የምኖር  ወንበዴ    ወይስ  ነብሰ ገዳይ  ሌባና  ቀጣፊ ወይስ  መላ  ዘመኔን በሀጢዓት  የጨረስሁ ክፉ  ሰዉ  ነኝ  ልበል  የቱን  ስራየን  ልንገረዉ? መላዕኩም በመፅሀፍ  ስማቸዉ  በበጎ ስራቸዉ  የተፃፉ  ቅዱሳንን እያነሳ  መረመረኝ ጠየቀኝ እኔም  ዝም  አልሁ  ከብዙ ዝምታ  በሃላ   ትንሽም  ብትሆን  ያለችኝን ስራየን ነገርሁት  ዓለም  በጨለማ  ስትወረር  ደቀመዛሙርቱ  ርቀዉ ሲመለከቱ መላዕክቱም  ከፍርሃት  የተነሳ  ዝም  ሲሉ  አይሁድም  ልብሱን  ሲካፈሉ  አቤቱ  በመንግስትህ በመጣህ  ጊዜ  አስበኝ  ብየ  አምላክነቱን የመሰከርሁ ነኝ።
ታድያ  ጩኸቴን ሰምቶ  ዝም  አላለኝም  ብየ የተሰጠኝን የነፃነት ደብዳቤ  አሳየሁት  እሱም  በሁኔታው  በመገረም  ወደተላኩበት  ቦታ  አስገባኝ  አምላኬ  ሆይ ይህን  ያደርግህ  እኔ  ማን ነኝ  ዘመኔን  በሙሉ  በሀጢአት  ያሳለፍሁ  ከልጅ  እስከ  አዋቂ  ሳልል  ሁሉንም  የገደልሁ  ቀማኛና  ወንበዴ  አይደለሁምን? ታድያ  ከኔ  ሀጢአት  ያንተ ምህረት  በዝቶ  ለዚህ  አበቃኸኘ ስለሆነዉም እየሆነስላለዉም  ወደፊት ለሚሆነዉም  አመሰግንሀለሁ  ክብር  ምስጋና  ጌትነት ከባህርይ  አባትህ  ከአብ  ከባህርይ  ህይወትህ  ከመንፈስ  ቅዱስ  ጋር ይሁን  ዛሬም  ዘወትርም  ለዘላለሙ  አሜን ።

///////////////////////////
ፊያታዊ ዜይማ ወይንም ደግሞ ጢጦስ
የነበርሁ እኔ ነኝ የሰው ደም የማፈስ፣
ድሃን የምቀማ ደም ማፍሰስ የምሮጥ
እኔ ነበርሁ ጢጦስ ድሃን የማፋጥጥ፣
ወንበዴ የምባል ሐጢአተኛ እኔ ነኝ
በሙሉ ዘመኔ ስቀማ የኖርሁኝ
እኔ ዕብራዊ ነኝ ከቅዱሳን ወገን
 ግና አልታደልሁም እነርሱን ለመሆነ፣
ድሃን በመበደል ዘመኔም አለቀች
ጌታዋን በመፍራት ነፍሴም ተጨነቀች፣
በሀጢአቴ ምክኒያት በሰዎች እጅ ተያዝሁ
ፍርድን ፈርደውብኝ በመስቀል ተሰቀልሁ፣
በግራየ በኩል አየሁት አምላኬን
ስለ ሰው ልጅ ሀጢአት ሰማሁት ሲማፀን፣
እኔስ በስራየ እርሱ ምን አጠፋ
ብየ በልቤ አሰብሁ ወይ የእርሱ ሥራ፣
የእኔ ውንብድና በእርሱ ላይ ተጣለ
የቀድሞው ሐጢአቴ በእርሱ ተነቀለ፣
በመንግስትህ ጌታ አስበኝ በማለት
እርሱን ተማፀንሁት በመጨረሻው ስዓት፣
ወደኔ አየና አዲት ቃል ነገረኝ
ከነት ለመግባት እኔን አስቀደመኝ፣
በዘመኔ ስኖር መልካም ስራ የለኝ
ታዲያ እዴት ወዶኝ ነው እርስቱን የሰጠኝ፣
አዳምን የቀደምሁ ወነበዴው ጢጦ ነኝ
ወደ ገነት መግባት መጀመሪያው ሆንሁኝ፣

ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

2018 ኤፕሪል 1, እሑድ

ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው? ጥያቄና መልስ

sara mariyam:
https://youtu.be/yTY62za_Dww

sara mariyam:
https://youtu.be/yTY62za_Dww


✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን አላችሁ ውድ የክርስቶስ ቤተሰቦች ሰላማችሁ ይብዛልን!!
🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿

🌿እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና በሰላም በጤና አደረሳችሁ አደረሰን እያልን፦ ዛሬ ስለ ሆሳዕና 8 ጥያቄዎችን እንጠያየቃለን...🌿🌿🌿🌿


1ኛ, 🌿ሆሳዕና ማለት ምን ማለት ነው??

🌿መልስ🌿🌿✍ሆሳዕና ማለት፦ የዕብራይስጥ ቃል ሲሆን ትርጉሙ ‹‹እባክህ አሁን አድን አሁን ባርከን›› ማለት ነው፡፡በሰሙነ ሕማማት ጸሎተ ፍትሃት ጸሎተ አስተስርዮ ስለማይፈጸም ጸሎተ ፍትሃትና አስተስርዮ የሚደረገው በዚሁ ዕለት ነው::

2ኛ, 🌿 በሆሣዕና ዕለት በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው??

🌿መልስ🌿1.ጌታ ለአዳም የሰጠው ቃል ኪዳን ለማስታወስ፡-ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድነሃለሁ ያለውን የተስፋ ቃል ለማስታወስ፡፡
2.ጌታ ለእመቤታችን የገባላትን ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
3.ጌታ ለእስራኤላውያን የሰጣቸው ቃል ኪዳን ተምሳሌት ነው
4.ጌታ ለአዳም ከሰይጣን ግዛት ነጻ እንዳወጣው ሁሉ እኛም ከሰይጣን ግዛት ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ ከክፋት ከኃጢአት አውጣን ማረን ለንስኃ ሞት አብቃን ከቤትህ አትለየን እንደ ቸርነትህ ይቅር በለን ስንል ለጌታ ዳግም ላናጠፋ ቃል የምንገባበት ነው፡፡

3ኛ,🌿 ጌታችን በዕለተ ሆሳዕና ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም??

🌿መልስ🌿ትንቢቱንና ምሳሌውን ለመፈጸም ነው፡፡ " አንቺ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ፤ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እልል በዪ፤ እነሆ፥ ንጉሥሽ ጻድቅና አዳኝ ነው፤ ትሑትም ሆኖ በአህያም፥ በአህያይቱ ግልገል በውርጫይቱ ላይ ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል። "
             (ትንቢተ ዘካርያስ 9:9)
🌿በአህያ መቀመጡ፦
•ትህትናን ለማስተማር
•የሰላም ዘመን ነው ሲል
•ለፈለጉኝ ሁሉ የቅርብ አምላክ ነኝ ሲል በንጽህና በየዋህነት ለሚኖሩ ምዕመናን  አድሬባቸው እኖራለሁ ሲል፡፡
•አህያዎች ትሁታን ናቸው ረጋ ብለው ነው የሚሄዱት፤በቀላሉ ትወጣበታለህ፤በቀላሉ ትይዘዋለህ፤እንደፈለክም ታዝዋለህ፤.

4ኛ, 🌿ጌታችን ወደ ኢየሩሳሌም ሲገባ ዘባባ የመነጠፉ ሚስጢር የምን ምሳሌ ነው???

🌿መልስ🌿🌿✍ዝንባባ
1.ዝንባባ፡- ይስሃቅ በተወለደ ጊዜ ደስ ብሎት አብርሃምን ዘንባባ ይዞ እግዚአብሔር አመስግነዋል፡፡
2.ዝንባባ ደርቆ እንደገና ሂይወት ይዘራል፡- የደረቀ  የምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
3.ዝንባባ የሰላም ምልክት ነው፡- የሰላም አምላክ ነህ ሲሉ ነው
4.ዝንባባ የደስታ መግለጫ ነው፡- አንተ ደስ የምታሰኝ ሃዘናችንም የምታርቅልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
5.ዝንባባ እሾሃማ ነው፡- አንተ ህያው አሸናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው፡፡
6.ዝንባባ እሳት አይበላውም ለብልቦ ይተወዋል እንጂ፡፡ ጌታም አንተ ባህሪህን የማይመረመር ነው ሲሉ ነው፡፡


5ኛ,🌿 ህዝቡ ከልብሳቸው ሌላ ስንት አይነት ቅጠንል አነጠፉለት ምን ምን??

🌿መልስ🌿🌿🖊 ልብሳቸውን ማንጠፋቸው፡- ለክብሩ መግለጫ ነው፡፡
ሌሎችም ሦስት አይነት ቅጠል አነጠፉለት ዘንባባ፤የቴመር ዛፍ፤የወይራ ዛፍ አነጠፉለት፡፡


6ኛ, 🌿 ትልቅዋ አህያ በምን ትመሳለለች ውርንጭለዋስ???


🌿መልስ🌿🌿✍ትልቅዋ አህያ የኦሪት ምሳሌ ነው
1.ትልቅዋ አህያ ሸክም የለመደች ናት ህገ ኦሪትም የተለመደች ህግ ናትና፡፡
2.የእስራኤል ምሳሌ ነው፡-ትልቅዋ አህያ ሸክም እንደለመደች ሁሉ እስራኤልም ህግ ለመፈጸም በህግ ለመራመድ የለመዱ ናቸው፡፡
3.የአዳም ምሳሌ ነው፡- አዳም ሸክም የበዛበት ነበርና

🌿✍ውርጭላዋ
1.በህገ ወንጌል ትመሰላለች፡-ምክንያቱም ወንጌል ኢየሱስ ክርስቶስ የመሰረታት የሰራት አዲስዋ ህግ ናትና፡፡
2.በአህዛብ ትመሰላለች፡-ትንሽዋ አህያ ሸክም የለመደች አይደለችም እንዲሁም አህዛብም ህግህን የመቀበል የለመደ አይደሉም፡፡ ለህግህ አዲስ ናቸውና፡፡
3.የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡- የዓለም ሸክም አቅልላለችና በእመቤታችን ትመሰለላለች፡፡ እመቤታችን ድህነተ ምክንያታችን ጌታን የተሸከመች ንጽህት እንከን የሌላት እናት ናትና፡፡


7ኛ,🌿 አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ፥ እጅግ ደስ ይበልሽ አንቺ የኢየሩሳሌም ልጅ ሆይ እልል በይ ንጉሥሽ በአህያ ግልገል ተቀምጦ ወደ አንቺ ይመጣል የሚለው ሃይለ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይገኛል???

🌿መልስ🌿🌿✍ት/ ዘካርያስ.ም 9፥9

8ኛ, 🌿 ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ብዙ ያልታሰሩ አህዮች እያሉ ለምን የታሰሩትን መረጠ???

🌿መልስ🌿🌿✍አህዮቹ የታሰሩት ሌባ ሰርቆ ነው ያሰራቸው፡፡ ወንበዴ ሰርቆ ነው ያሰራቸው አህዮቹ ለጌታ ውለታ ሰርተዋል፡፡ ጌታ ሲወለድ አሙቀውታልና  ለጌታ ውለታ ልንመልስ ያልቻልነው እኛ ሰዎች ብቻ ነን፡፡
        የታሰሩት እዲፈቱ የመረጠበት ሚስጥር፡-እኔ ከሃጥአታችሁ ልፈታችሁ የመጣሁ ነኝ ሲል ነው፡፡ወንበዴው አህዮቹን ሰርቆ በመንደር እንዳሰራቸው ዲያብሎስም ለሰው ልጅ በሃጥአት ሰንሰለት ከሲኦል መንደር አስሯቸው ነበርና፡፡
ሐዋርያቱ ሲልካቸው ምን ታደርጋላችሁ የሚላችሁ ሰው ቢኖር ጌታቸው ይሻቸዋል በልዋቸው አላቸው፡፡ የፈጠራቸው እሱ ነውና፡፡

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿መልካም የሆሳዕና በዓል ይሁንልን ወስብሐት እግዚአብሔር 🌿🌿🌿🌿🌿🌿saramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...