ሰኞ 19 ማርች 2018

ጥያቄና መልስ

1. አዳም በምድር ላይ የኖረው የእድሜው ዘመን ስንት ነው?

መልስ፡- 930፡፡ ዘፍ.5÷1-5

2. የቅዱስ ጳውሎስን የሕይወት ታሪክ መዝግቦ የያዘ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የቱ ነው?

መልስ፡- የሐዋርያት ሥራ፡፡

3. ስለ ነቢያት በስፋት የሚተርከው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል የቱ ነው?

መልስ፡- መጽሐፈ ነገሥት 1ኛ እና 2ኛ፡፡
4. ጌታ ሲወለድ የነበሩት የእስራኤልና የኢትዮጵያ ነገሥታት እነማን ነበሩ?

መልስ፡- ሄሮድስና ንጉሥ ባዚን፡፡ ማቴ.2÷1

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

1. የወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ አባት እና እናት ስማቸው ማን እና ማን ናቸው?

መልስ፡- አባቱ ዘብዴዎስ እናቱ ማርያም ስትሆን ከ 36 ቱ ቅዱሳን አንስት አንዷ ነች፡፡
2. ቅዱስ ዮሐንስ ከዚህ ሌላ ስንት መጠሪያ ስሞች አሉት ? ዘርዝሩ፡፡

መልስ፡- 7 ስሞች አሉት፡፡ ወልደ ዘብዴዎስ  ፣ ወልደ ነጎድጓድ / ቦአኔርጌስ/ ፣ ቁጽረ ገጽ ፣ ፍቁረ እግዚእ ፣ ነባቤ መለኮት/ ታዖሎጎስ/ ፣ አቡቀለምሲስ/ ባለራዕይ/ ፣ ወንጌላዊ/ ሐዋርያ/፡፡

3. ዮሐንስ ወንጌላዊ በአጠቃላይ ስንት መጻሕፍትን ጽፏል?ዝርዝሩ

መልስ፡- 5 ፡፡ የዮሐንስ ወንጌል ፣ 1ኛ የዮሐንስ መልዕክት ፣ 2ኛ ና 3ኛ የዮሐንስ መልዕክት  እና የዮሐንስ ራዕይ፡፡

4. በዮሐንስ ወንጌል ውስጥ እኔ ነኝ ተብሎ የተጻፉ ሰባት ነገሮች አሉ ዘርዝራችሁ ጸፉ፡፡

መልስ፡- የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ ፣ የዓለም ብርሃን እኔ ነኝ ፣ የበጎች በር እኔ ነኝ ፣ መልካም እረኛ እኔ ነኝ ፣ ትንሣኤና ሕይወት እኔ ነኝ ፣ መንገድ እውነትና  ሕይወትም እኔ ነኝ  እና እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፡፡

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨♥♥

1. ቤተክርስቲያን የሚለው ቃል ሦስት ነገሮችን ያመለክታል ለመሆኑ እነዚህ 3 ነገሮች ምን ምን ናቸው?

መልስ፡- 1. ሕንጻው እራሱ ፣2. የክርስቲያኖች ህብረት፣ 3.አንድ አማኝ ብቻውን፡፡

2. ሳይወለድ የሞተው ወይም ወደመቃብር የወረደው ብቸኛው ሰው ማን ነው?

መልስ፡- አዳም፡፡ ተፈጠረ እንጂ አልተወለደም፡፡

3. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጥንተ አብሶ እንደሌለባት የሚነገረ ጥቅስ ተናገሩ፡፡

መልስ፡- ኢሳ.1÷19

4. አናንያ፣ አዛርያ፣ ሚሳኤልና ዳንኤል ከሌሎቹ የተለየ የነበራቸው የተለየ ነገር ምን ነበር?

መልስ፡- ጥበብ ፣ እውቀት፣ እና ማስተዋል ነበራቸው፡፡ ት.ዳን 1፥3


https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjA
ተጨማሪ ጥያቄና መልሶችን ለማግኘት ሊንኩን በመጫን ቤተሰብ ሁኑ👆🏻

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...