2018 ጃንዋሪ 7, እሑድ

ልዩ የገና መልእክቶቻችሁ መረሀ ግብር

✞ በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን ✞

በወንጌሉ ያመናቹ
እንኩዋን ለብርሃነ ልደቱ አደረሳቹ !

✞♥✞♥✞ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወልደ+ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወል+ቤዛ ኩሉ አለም ዮም ተወል✞♥✞♥✞

✞♥✞እንኩዋን ለጌታችን ለመድሐኒታች ለኢየሱስ ክርስቶስ ለብርሃነ ልደቱ በሰላም በጤና አደረሳቹ አደረሰን!!! ✞♥✞

«ህፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፥ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል»ኢሳ 9፥6 የተባለው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወሰነና በቤተልሔም ተወለደ።
የወረብ መዝሙር
✞✞✞ሃሌ ሉያ በጎል ሰከበ በአጽርህት ተጠብለለ ውስተ ማህፀነ ድንግል ኃደረ ዬም ተወልደ ✞✞✞
የወረብ መዝሙር
✞✞✞ተወልደ ኢየሱስ በቤተልሔም [2] ✞✞✞
✞✞✞በቤተልሔም ዘይሁዳ በቤተልሔም [2] ✞✞✞
«የይሁዳ ምድር አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ ከይሁዳ ገዥዎች ከቶ አታንሽም ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና»ሚክ 5፥2 የሚል ትንቢት ተነግሮ ነበር። እነሆ ይህ ትንቢት እውን ሆነና የነገስታት ንጉሥ፥ የጌቶች ጌታ፥ የአማልክት ሁሉ አምላክ እንደ ቃል ኪዳኑ ተወለደ። ቅዱስ ኤፍሬም የነቢያት አገራቸው ቤተልሔም ሆይ ደስ ይበልሽ ባንቺ ክርስቶስ ተወልዷልና ያለው ለዚህ ነው።«ህፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፥ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል፤ ስሙም ድንቅ መካር፥ ኃያል አምላክ፥ የዘላለም አባት፥ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል»ኢሳ 9፥6 የተባለው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ ሰማይና ምድር የማይችሉት አምላክ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወሰነና በቤተልሔም ተወለደ። «የይሁዳ ምድር አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ ከይሁዳ ገዥዎች ከቶ አታንሽም ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና»ሚክ 5፥2 የሚል ትንቢት ተነግሮ ነበር። እነሆ ይህ ትንቢት እውን ሆነና የነገስታት ንጉሥ፥ የጌቶች ጌታ፥ የአማልክት ሁሉ አምላክ እንደ ቃል ኪዳኑ ተወለደ። ቅዱስ ኤፍሬም የነቢያት አገራቸው ቤተልሔም ሆይ ደስ ይበልሽ ባንቺ ክርስቶስ ተወልዷልና ያለው ለዚህ ነው።

+ይህው ተወለደ ‘ያለም መዳኒት’[3]
+እሰይ ተወለደ ‘ያለም መዳኒት’[3]
አዝ...
ሰባሰገል መጡ ‘ሊሰግዱ በሙሉ’[3]
አምላክ ቀዳማዊ ‘ተወልዶአል እያሉ’[3]
አዝ...
ሰባ ሰገል መጡ ‘እጅ መንሻይዘው’[3]
ወርቅ እጣን ከርቤውን ‘ገበሩለት ሰግደው’[3]
አዝ...
ህፃናት እንሂደ ‘ከመቅደሱ ቤት’[3]
ውሃው ሆኖአልና ‘ማርና ወተት’[3]

ማቴ:2÷1-12
"ኢየሱስም በይሁዳ ቤተ ልሔም በንጉሡ በሄሮድስ ዘመን በተወለደ ጊዜ፥ እነሆ፥ ሰብአ ሰገል፡- የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው? ኮከቡን በምሥራቅ አይተን ልንሰግድለት መጥተናልና እያሉ ከምሥራቅ ወደ ኢየሩሳሌም መጡ። ንጉሡ ሄሮድስም ሰምቶ ደነገጠ፥ ኢየሩሳሌምም ሁሉ ከእርሱ ጋር፤ የካህናትንም አለቆች የሕዝቡንም ጻፎች ሁሉ ሰብስቦ ክርስቶስ ወዴት እንዲወለድ ጠየቃቸው። እነርሱም፡-አንቺ ቤተ ልሔም፥ የይሁዳ ምድር፥ ከይሁዳ ገዢዎች ከቶ አታንሽም፤ ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና ተብሎ በነቢይ እንዲህ ተጽፎአልና በይሁዳ ቤተ ልሔም ነው አሉት። ከዚህ በኋላ ሄሮድስ ሰብአ ሰገልን በስውር ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከእነርሱ በጥንቃቄ ተረዳ፥ ወደ ቤተ ልሔምም እነርሱን ሰድዶ፡- ሂዱ፥ ስለ ሕፃኑ በጥንቃቄ መርምሩ ባገኛችሁትም ጊዜ እኔ ደግሞ መጥቼ እንድሰግድለት ንገሩኝ አላቸው። እነርሱም ንጉሡን ሰምተው ሄዱ እነሆም፥ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ሕፃኑ ባለበት ላይ መጥቶ እስኪቆም ድረስ ይመራቸው ነበር። ኮከቡንም ባዩ ጊዜ በታላቅ ደስታ እጅግ ደስ አላቸው። ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፥ ወድቀውም ሰገዱለት፥ ሣጥኖቻቸውንም ከፍተው እጅ መንሻ ወርቅና ዕጣን ከርቤም አቀረቡለት። ወደ ሄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ።"
የበአሉ እረዴትነና በረከት በሁላችን ይደርብን

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክብር አሜን።ይቆየን

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...