2018 ጃንዋሪ 2, ማክሰኞ

የአባታችን አቡነ ተክለ ሃይማኖት መዝሙሮች

ለተክለሃይማኖት
=============
ለተክለሃይማኖት ጻድቅ መጠነ ብዝኃ ህማሙ /2/
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ /4/
እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሠተ ሥጋሁ ወአጽሙ /2/
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ /4/
እምነ አድባራት ኵሎን ዘተለአለት በስሙ /2/
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ /4/
ኢየሱስ ክርስቶስ እንተ ቀደሰ በደሙ/2/
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ /4/
ትርጉም- ጻድቁ ተክለሃይማኖት ብዙ ህማም የተቀበለባት ቅዱስ አጽሙ ያረፈባት በስሙ ከታነጹት አድባራት ሁሉ ከፍ ያለች ኢየሱስ ክርስቶስ በደሙ የቀደሳት ደብረ ሊባኖስ ታመሰግነዋለች።

/////////////////////////////

ኢትዮጲያዊው ፃድቅ ማነው ብዬ ጠየኩ
በረከት ፈልጌ ልሳለመው ናፈኩ
ክብሩን ልመሰክር ተፈታ ምላሴ
በደጁ ደርሸ ፍቅሩን በመቅመሴ

በኢትሳ ምድር ዘር ሆነህ በቅለህ
ተለየህ ለአምልክ አለምን ጥለህ
ደብረ ሌባኖስ ህያው ምስክር
ስላንተ ዝና ስላንተ ክብር
ተክለ ሀይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል ባንተ ጓዳ ደጄ

..አ..ዝ....

አክባሪው አምላክ ስላከበረክ
ዛሬም ከኛ ጋር በመንፈስ አለህ
ደጅ እንጠናለን በትህትና
የፃዲቅ ጸሎት ሀይል አላትና
ተክለ ሀይማኖት ፀሐይ
ጸጋህ ይውጣልኝ ከሠማይ

....አ.ዝ......

ወደ ለምለም መስክ ሠብከህ መራኸን
የቃሉን ወተት አጠጥተኸን
ያቀጣጠልከው የወንጌል ችቦ
የአምላክ አድርገኅል ትውልዱን ስቦ
ተክለ ሀይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል ባንተ ጎዳ ደጄ

.....አ...ዝ..

ሠላሳ ስልሳ መቶ ያፈራህ
በደብረ አፅሙ ቆመህ ባንድ እግርህ
የመቶሎሜ መሻት ቀረና
የጌታ መንገድ ጥርጊውም ቀና
ተክለ ሀይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል ባንተ ጓዳ ደጄ
...አ...ዝ.....

በኢትሳ ምድር ዘር ሆነህ በቅለህ
ተለየክ ለአምላን አላምን ጥለህ
ደብረ ሊባኖስ ህያው ምስክር
ስላንት ዝና ስላንተ ክብር
ተክለ ሀይማኖት ወዳጄ
ተባርኳል ባንተ ጓዳ ደጄ

/////////////////////////////

#ገድሉ ተአምራቱ እጅግ ብዙ ነው
ጣኦትን አዋርዶ የተሸለመው
የተዋሕዶ ኮከብ ተክለሐዋርያ
አባ ተክለ ሃይማኖት ዘኢትዮጵያ
አዝ ------------------
ዳግማዊ ዮሐንስ ጠፈር የታጠቀ
ንጹሕ ባህታዊ ጠላት ያስጨነቀ
የጸጋ ዘአብ ፍሬ ዛፍ ሆኖ በቀለ
በደብረ ሊባኖስ መናኝ አስከተለ
አዝ ---------------------
ደካማ መስሏቸው በአንድ እግሩ ቢያዩት
ባላስድስት ክንፉ ጻድቁ የእኔ አባት
እርሱስ አንበሳ ነው ትናገር ደብረ አስቦ
ሌጌዎን ሲዋረድ እፍረት ተከናንቦ
አዝ -----------
ከካህናት መካከል ኅሩይ ነው አቡዬ
መጣው ከገዳምህ ልሳለለምህ ብዬ
ኢትዮጵያዊው ቅዱስ አባ ተክለሃይማኖት
ወልድ ዋሕድ ብለህ ምድሪቱን ቀደስካት
አዝ -----------------
የባረከው ውኃ የረገጥከው መሬት
ጥላህ ያረፈበት ሁኗል ጸበል እምነት
ኑና ተመልከቱ ድውያን ሲፈቱ
ይሰብካል ተክለአብ ዛሬም እንደጥንቱ
አዝ ------------------ገድሉ


/////////////////////////////
የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ
አናፍርም ትምኪታችን ነው መስቀሉ (2)

የእኛ ነው የእኛ
የሦስት ሽ አመት ታሪክ ያላት

ታቦተ ጽዮን ያለችበት የጸሎት ስፍራ
የኪዳን ሀገር ኢትዮጵያ እናቴ
ሃገር እግዚአብሔር

የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ አናፍርም
ትምክታችን ነው መስቀሉ

የእኛ ነው የእኛ

በአድስ ድንጋይ የተወቀር የላሊበላ
ድንቅ ስራ ነው ጋርው ክፍት ሆኖ
ዝናብ ማይገባው አቡነ ሀሮን
ምንኛ ውብ ነው

የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ አናፍርም
ትምክታችን ነው መስቀሉ

የእኛ ነው የእኛ

ኢትዮጵያ ሃገሬ ልጅሽ ባኮስ
ተጠምቆልሻል በፊሊጶስ
የአምላክ ስው መሆን ምስጥርን አውቆ
በእየሱስ አምኖ መጣ ተጠምቆ

የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ

አናፍርም ትምክታችን ነው መስቀሉ

የእኛ ነው የእኛ.. .

ትምክህታችን ነው የጌታ መስቀል
አምነን ድነናል በእምነት በጸበል

መለያንች ነው አጥማችን
ተዋህዶ ናት እምነታችን

የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ

አናፍርም ትምክህታችን ነው መስቀሉ

የእኛነው የእኛ...

ጻድቃኔ ሂዱ ሽንኮራ ሂዱ

ግሽንም ውጡ አክሱም ውርዱ

ሽባው ተፍቶ እውሩ በርቶ
ጎባጣው ቀንቶ ዴንቆሮው ስምቶ

ፍጹም አምነናል አይናችን አይቶ
ጸንተን ቁመናል ጆሯችን ስምቶ

የእኛ ነው ዋሻው እምነቱ ጸበሉ

አናፍርም ትምክህታችን ነው መስቀሉ

የእኛ ነው የእኛ.. .

//////////////////////////

ገድል_በገድልህ_ቤት_ውስጥ

ገድል በገድልህ ቤት ውስጥ ሲነበብ ሲሰማ
ልቤ ተማረከበት በተክልዬ ግርማ
ደብረ ሊባኖስ ነው ያየሁት እርሱን
ሊባርክ ሲመጣ ሌተ ቀን ገዳሙን

...አ..ዝ..

እየባረከ ይባርከናል እየቀደሰ ይቀድሰናል
ጸጋው በዝቶለት በአምላካችን
በክንፉ ይበራል ሊያማልደን
አቤት የተክለ ሃይማኖት ክብሩ
ሱራፌል ሆነ በሰማይ ሀገሩ
ጽንአ ይዞ እያጠነ ዙፋኑን
ያስታርቀናል ሌሊትና ቀን
ያማልደናል ሌሊት እና ቀን

....አ....ዝ..

እንግዶች ሆነን ዋሻው ስንሄድ
ያሳድረናል ትሁት ነው ውድ
የአምላክ ምስሌ ሆኖልናልና
ልጆቹ ሁሉ ወጡ ምነና
አቤት የተክለሃይማኖት ክብሩ
ሱራፌል ሆነ በሰማይ ሀገሩ
ጸንአ ይዞ እያጠነ ዙፋኑን
ያስታርቀናል ሌሊት እና ቀን… የማልደናል ሌሊትና ቀን

....አ...ዝ..

በንፋስ አውታር ዘውትር ይሄዳል
በወንጌል መረብ ብዙውን ያጠምዳል
የታመመውን እየፈወሰ
ሙታን ያስነሳል እየቀደሰ
አቤት የተክለሃይማኖት ክብሩ
ሱራፌል ሆነ በሰማይ ሀገሩ
ጽንአ ይዞ እያጠነ ዙፋኑን
ያስታርቀናል ሌሊትና ቀን…ያማልደናል ሌሊትና ቀን
....አ..ዝ...

ድካም የለለበት ዘወትር ብርቱ
ግዳጅ ፈጻሚ ስውር ጸሎቱ
ተዘከረኒ በባህር ወየብስ ድረስ
ተክለሃይማኖት ስልህ
.....አ....ዝ...

አቤት የተክለሃይማኖት ክብሩ
ሱራፌል ሆነ በሰማይ ሀገሩ
ጸንአ ይዞ እያጠነ ዙፋኑን
ያስታርቀናል ሌሊት እና ቀን
ያማልደናል ሌሊት እና ቀን
/////////////////////////////

ገና በሦስት ቀንህ ለምስጋና የተጋህ
ከሱራፌል ተርታ ተዋህዳ ፅናህ
የሥላሴን መንበር አብረሃቸው ያጠንህ
አባ ተክለሃይማኖት ምድራዊ መልአክ ነህ
አባ ተክለሃይማኖት ምድራዊ መልአክ ነህ/2/

አዝ===

ገድልና ታምርህ አያልቅም ተነቦ
የተጋደልክባት ትናገር ደብረ አስቦ
ከፀሎትህ ብዛት አንድ እግርህ ቢቆረጥ
ስድስት ክንፍ ተሰጠህ ክብርህን የሚገልጥ

አዝ===

ቀዝቃዛን ውሃ እንኳን በስምህ የሰጠ
ዋጋ ያግኛልና እጅግ የበለጠ
ዝክርህን መዘከር ስምህን መጥራቴ
ምስክር ይሁነኝ በላይኛው ቤቴ

አዝ====.

ከኃጢአት ወጥቼ ጽድቅን እንድሰራ
ልብ እንዲኖረኝ ቃሉም እንድዘራ
ለሕይወት የሚሆን ፍሬም እንዳፈራ
በረዴኤት ጎብኘኝ ገፅህ ለእኔ ይብራ

አዝ===

አባ ተክለሃይማኖት የወንጌል ገበሬ
ኢትዮጵያን የመገብክ የኅይማኖት ፍሬ
በነፍሴ ተርቤ ሕይወት እንዳላጣ
በጸሎትህ ኅይል እርዳኝ ነፃ ልውጣ

አዝ====


//////////////////////////

አለምን የረታ በእምነት ፪
ፃድቁ አባት ነው ተክለሃይማኖት

አክብሮሀል ጌታ፡፡፡፡፡፡አለምን የረታ
ከፍ አድርጎሀል፡፡፡፡፡፡፡አለምን የርታ
ጸሎትህ ተሰምቶ፡፡፡፡፡፡፡፡አለምን የረታ
ኢትዮጵያ ምሯል ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡አለምን የርታ
በክንፎችህ ጥላ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡አለምን የረታ
ከልለን ተክለ አብ።።።።አለምን የርታ
ልጆችህ እንዳንጠፋ።።።።አለምን የረታ
ከቤትህ ኩብልለን።።።።።አለምን የረታ

አለምን የረታ በፀሎት ፪
ፃዱቁ አባት ነው ተክለሃይማኖት

♦እያበሩ ፋና ዘለቁ፪
ገብረ መንፈስ ቅዱስ አቡዪ
ፃድቁ
የንሂሳዉ ሕፃን ።።።።እያበሩ ፋና
ዋስ ሆናት ለነፍሴ፡፡፡፡፡፡፡እያበሩ ፋና
በማህፀን ሳለህ፡፡፡፡፡፡፡ እያበሩ ፋና
መረጡህ ስላሴ።።፡፡፡፡እያበሩ ፋና
ቁምልን በፊቱ።።።።።።እያበሩ ፋና
በሀጢአት ወድቀናል፡፡፡፡፡፡እያበሩ ፋና
ለምንልን ለእኛ።።።።።። እያበሩ ፋና
ፀሎትህ ያበርታን።።።።።እያበሩ ፋና

♦ማልጄ መጣሁኝ ደጅህ፪
አቡነ ሀብተማርያም ልጅህ

ፈዋሹ ሉሚህን ።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
በእምነት በልቸ።።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
እራቀ ደዌየ።።።።።።።።ማልጅ መጣሁኝ
ፀበልክን ጠጥቸ።።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
ፅኑ ነው ኪዳኑ።።።።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
የማይናወጥ ።።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
ከልብ የለመጣሁብህ።።።።።ማልጀ መጣሁኝ
የወጣል ከማጥ።።።።።።።ማልጀ መጣሁኝ

♦የሊዳዉ ኮከብ  ነህ የቤይሩት ፪
ሰማዕቱ ጊዮርጊስ ነዓ በምህረት
በነጭ ፈረሱ።።።።።።። የሊዳዉ ኮከብ ነህ
ቀድሞ ከፊታቸው ።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ
ኢትዮጵያውያንን።።።።። የሊዳዉ ኮከብ ነህ
በድል ያቆማቸው ።።።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ
ፅኑ ነው ጊዮርጊስ ።።።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ
ገድሉ የሚያስደንቅ።።።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ
ተፈትኖ ያለፈ።።።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ
አንደ ነጠረ ወርቅ ።።።።።የሊዳዉ ኮከብ ነህ

♦የሲሪንቃዋ እናት አርሴማ ፪
ከደጅሽ መጥቸ ፀሎቴ ተሰማ
የስጨንቀኝ ነበር ።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
ለብዙ ዘመን ።።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
የልቤን ስነግራት።።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
ቀለለኝ አሁን ።።።።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
ይርዳል አጋንንት ።።።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
ሲጠራ ስምሽ።።።።የሲሪንቀዋ እናት 
ገድልሽ ግሩም ነው ።።።።።።።።የሲሪንቃዋ እናት
ዘንባባሽ ፈዋሽ።።።።።።። የሲሪቃዋ እናት

እልልልልልልልልልልልል

ስለ መዝሙሩ የዝማሬው በአለቤት ልዑል አምላካችን የተመሰገነ ይሁን አሜን፫
♥♥♥♥♥
ወስብኃት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል.
ወለ መስቀሉ ክቡርsaramareyama.890@gmail.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...