2017 ዲሴምበር 14, ሐሙስ

ውዳሴሃ ለእግዝትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ ዘይትነበብ በዕለተ ዓርብ

«ውዳሴሃ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክዘይትነበብ በእለተ ዓርብ»

ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ የማኅፅንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ያለ ርኩሰት አምላክን የወለድሽ ድንግል ማርያም ሆይ እውነተኛ ፀሐይ ከአንቺ ወጣልን /ጌታ ተወለደልን/ በክንፈ ረድኤቱም አቀረበን እርሱ ፈጥሮና ልና። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

አምላክን የወለድሽ እመቤታችን ሆይ የብርሃን እናት ነሽና አንቺን ብቻሽን በክብር በምስጋና እናገንሻለን የተባረክሽ አንቺ ከመላእክት ትበልጫለሽ ከደቂቀ አዳምም ትበልጫለሽ ከአሳቦች ሁሉ ትበልጫለሽ ገናንነትሽን መናገር የሚቻለው ማነው አንቺን የሚመስል የለምና ማርያም ሆይ መላእክት ያገኑሻል ሱራፌ ልም ያመሰግኑሻል በኪሩቤልና በሱራፌል ላይ አድሮ የሚኖር ጌታ መጥቶ በማኅጸንሽ አድርዋልና ሰውን የሚወድ ወደ እርሱ አቀረበን ክብር ምስጋና ያለው እርሱ የእኛን ሞት ተቀብሎ የእርሱን ሕይወት ለእኛ ሰጠን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

የደናግል መመኪያቸው አምላክን የወለድሽ ድንግል ማርያምሆይ የተባረክሽ ነሽ የማኅፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነው ከዓለም በፊት የነበረ እርሱ ሰው ሆኖዋልና ከአንቺ የተወለደ ሥጋችንን ነሣ/ተዋሐደ/ መንፈስ ቅዱስንም ሰጠን በቸርነቱ ብዛት መሳዮቹ አደረገን ጸጋንና ክብርን ከተቀበሉ ብዙ ሴቶች አንቺ ትበልጫለሽ አምላክን የወ ለድሽ ማርያም ሆይ ልዑል እግዚአብሔር ያደረብሽ /የከ ተመብሽ/ ረቂቅ ከተማ ነሽ በኪሩቤልና በሱራፌል ላይ የሚኖረውን ጌታንበመኻል እጅሽ ይዘሺዋልና በቸርነቱ ብዛት ስጋዊ ፍጥረትን ሁሉ የሚመግብ እርሱ ጡትሽን ይዞ ጠባ። ይኸውም ሁሉን የሚያድን አምላካችን ነው ለዘለዓለሙ ይጠብቀናል እንሰግድለትና እናመሰግነው ዘንድ እርሱ ፈጥሮናልና። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

ድንግል ማርያም የሽቱ መኖሪያና የሕይወት ውሃ ምንጭ ናት የማኅፀንዋ ፍሬ ሰውን ሁሉ አድንዋልና። ከእኛም እርግማንን አጠፋልን። በመካከላችንም ሆኖ በመስቀሉ አስታረቀን በልዩ ትንሳኤውም ሰውን ዳግ መኛ ወደ ገነት መለሰው። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

ንጽሕት ድንግል ማርያም የታመነች አምላክን የወለ ደች ናት። ለሰዎች ልጆችም የምሕረት አማላጅ ናት። ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ወደ ልጅሽ ወደ ክርስቶስ ለምኝልን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ድንግል ማርያም በቤተ መቅደስ አሰምታ ትናገር ነበርመልአኩ ቅድስት ድንግል ሆይ ሰላምታ ይገባሻል ብሎ አክብሮከነገረኝ ነገር በቀር ምንም ምን ሌላ የማውቀው ነገር እንደሌለኝእግዚአብሔር ያውቃል አለች። የማይቻለውን ቻልሽየማይወሰነውንና ምንም ምን የሚወስነው የሌለውን ወሰንሽ።በክብር ሁሉ ላይ ጸጋን የተመላሽ ሆይ ምስጋናሽ ይበዛል ክብርሽፍጹም ነው። የአብ ቃል ማደሪያ ሆነሻልና የክርስቲያን ወገኖችምዕመናንን የምትሰበስቢያቸውና ማሕ የዊ የሚያድኑን ለሆኑለሥላሴ ሰጊድን/መስገድን/ የምታስተ ምሪላቸው ሰፊ መጋረጃሙሴ ያየውን የእሳት አምድ የተሸከ ምሽ አንቺ ነሽ ይኸውምመጥቶ በማሕፀንሽ ያደረው የእግዚ አብሄር ልጅ ነው።ሰማይንና ምድርን ለፈጠረ ጌታ ማደሪያ ሆንሽ። ዘጠኝ ወርበማሕፀንሽ ተሸከምሽው ሰማይና ምድር ለማይወስኑትየታመንሽ አንቺ ነሽ። ከምድር ወደ ሰማይ ለማ ረግ መሰላልሆንሽ። ብርሃንሽ ከፀሐይ ብርሃን ይበልጣል።

ቅዱሳን በፍጹምደስታ ያዩት ኮከብ ከአንቺ የተወለደ ምስራቅ አንቺ ነሽ።ይኸውም በጻዕርና በምጥ ትወልድ ዘንድ በሔዋን የፈረደባትነው። አንቺ ማርያም ግን ጸጋን የተመላሽ ሆይ ደስ ይበልሽየሚል ቃልን ሰማሽና መጥቶ ያዳነን የፍጥረት ሁሉ ገዥ የሆነንጉሥን ወለድሽልን መሐሪ ነው ሰውንም ወዳጅ ነው።ስለዚህማርያም ሆይ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽም ፍሬ የተባረከ ነውጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ነውና ደስይበልሽ እያልን መልአኩ ገብርኤል እንዳመሰገነሽእናመሰግንሻለን።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ለዘለዓለሙ አሜን ቅድስት ሆይ ለምኝልን።saramareyama.890@gmail.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...