saramareyama.890@gmail.com
#ቅኔ
ሰሙን ወርቁን በማውጣት ይሞክሩ፡፡
#ቅኔ
፩. ከዚያ ታች ያለችው ድውይ፤
ከቶ ምን ቀመሽ አልሻት ወይ
ኋላ ፀፀቱ ባንቺ ይሆናል
ተይ ሥጋ ብላሽ ይሆናል፡፡
#ቅኔ
፪.የቀድሞ ዘመን ስህተት
የፆም ቀን አሳ መብላት
የአሁን ዘመን ሰው አያውቅ መላ
በጦም ሽሮ ነው የሚበላ፡፡
✝ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንዴት ዋላችሁ እንዴትስ ቆያችሁ???
ለተሳተፋችሁ ሁሉ ቃለ ሕይወትን ያሰማልን ተስፋ ዕርሰተ መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን አሜን፫
☞ የቅኔ ፩ መልስ
ሕብረ ቃሉ => ተይ ሥጋ ብላሽ
ሰሙ => #ሥጋው #ብላሽ (#የተበላሸ) ሊሆን ስለሚችል እንዳይፀፅትሽ ምንም አትበያት። ወይም ቅመሽው አትበያት ነው።
ወርቁ => 1ኛው ፍቺ #ሥጋ(የሰው ደካማው ሥጋ) ብላሽ መሆኑ አይቀርም። አፈር መግባቱ ወይም መበላሸቱ አይቀርም።
2ኛው የወርቁ ፍቺ ደግሞ => ነብስሽ ለሥጋሽ "ተይ ሥጋ" ብላሽ(ተናግራሽ)ይሆናልና፣ ይህን እያለችሽ(እንፁም )እያለችሽ) እንብላ(እንቅመስ) አትበያት። ኋላ እንዳይፀፅትሽ። ማለት ነው።
☞ የቅኔ ፪ መልስ
ሕብረ ቃሉ => በጦም ሽሮ
ሰሙ => የጦም ቀን ሽሮ የሚባል ወጥ ነው የሚበላው። ወይም የጦም ምግብ ነው የሚበላው።
ወርቁ => #ጦምን #ሽሮ ወይም #አፍርሶ ነው የሚበላው። የቀድሞዎቹ #በስህተት(#ባለማወቅ) ነበር የሚበሉት፣ የአሁኖቹ ግን #እያወቁ #ጦምን #ሽረው(#አፍርሰው) ነው አሳ የሚበሉት ማለት ነው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፫
#ቅኔ
ሰሙን ወርቁን በማውጣት ይሞክሩ፡፡
#ቅኔ
፩. ከዚያ ታች ያለችው ድውይ፤
ከቶ ምን ቀመሽ አልሻት ወይ
ኋላ ፀፀቱ ባንቺ ይሆናል
ተይ ሥጋ ብላሽ ይሆናል፡፡
#ቅኔ
፪.የቀድሞ ዘመን ስህተት
የፆም ቀን አሳ መብላት
የአሁን ዘመን ሰው አያውቅ መላ
በጦም ሽሮ ነው የሚበላ፡፡
✝ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንዴት ዋላችሁ እንዴትስ ቆያችሁ???
ለተሳተፋችሁ ሁሉ ቃለ ሕይወትን ያሰማልን ተስፋ ዕርሰተ መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን አሜን፫
☞ የቅኔ ፩ መልስ
ሕብረ ቃሉ => ተይ ሥጋ ብላሽ
ሰሙ => #ሥጋው #ብላሽ (#የተበላሸ) ሊሆን ስለሚችል እንዳይፀፅትሽ ምንም አትበያት። ወይም ቅመሽው አትበያት ነው።
ወርቁ => 1ኛው ፍቺ #ሥጋ(የሰው ደካማው ሥጋ) ብላሽ መሆኑ አይቀርም። አፈር መግባቱ ወይም መበላሸቱ አይቀርም።
2ኛው የወርቁ ፍቺ ደግሞ => ነብስሽ ለሥጋሽ "ተይ ሥጋ" ብላሽ(ተናግራሽ)ይሆናልና፣ ይህን እያለችሽ(እንፁም )እያለችሽ) እንብላ(እንቅመስ) አትበያት። ኋላ እንዳይፀፅትሽ። ማለት ነው።
☞ የቅኔ ፪ መልስ
ሕብረ ቃሉ => በጦም ሽሮ
ሰሙ => የጦም ቀን ሽሮ የሚባል ወጥ ነው የሚበላው። ወይም የጦም ምግብ ነው የሚበላው።
ወርቁ => #ጦምን #ሽሮ ወይም #አፍርሶ ነው የሚበላው። የቀድሞዎቹ #በስህተት(#ባለማወቅ) ነበር የሚበሉት፣ የአሁኖቹ ግን #እያወቁ #ጦምን #ሽረው(#አፍርሰው) ነው አሳ የሚበሉት ማለት ነው።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፫
ምንም አስተያየቶች የሉም:
አስተያየት ይለጥፉ