2018 ጃንዋሪ 11, ሐሙስ

የምዕራፍ ሦስት/የ21ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን!! ይህ የምዕራፍ ሦስት/የ21ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር ነው።!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

✍ጥ.ተራ ቁ👉1⃣ልደት ማለት ምን ማለት ነው??

//መልስ//✍🏻ልደት ማለት =ግኝት ወደ መኖር መምጣት ማለት ነው ። ኦ.ዘ.ፍ ማለትም ወደ ግኝት መምጣት ማለት እንደሆነ ​አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ በመዝገበ ቃላቸው ላይ *ገፅ 325​ ላይ ተገልጿል።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉2⃣ዘመነ ብረሀን የሚባለው  ከምን እስከ ማንትወልድ ያለው ነው??

//መልስ//✍🏻ዘመነ ብረሃን የሚባለው ከልደተ ዳዊት እስከ ፍልሰት ባቢሎስን"14"ቱ ትውልድ ነው። ብርሀን የተባለው ጌታችን ኢየሲስ ክርስቶስ ነው ።

✍ጥ.ተራ ቁ..3⃣ዘመነ ሀጋይ ማለት ምን ማለት ነው ??

//መልስ//✍🏻ዘመነ 'ሀጋይ'  ማለት 'ከታህሳስ 26-መጋቢት 25"  ያለው ሲሆን የቃሉ ትርጎሜ ሀጋይ ፡ደርቅ,ጸሀይ፡ሀገር፡በጋ፡፡ሲሆን ከ4ቱ ክፍለ ዘመነ አንዱ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉4⃣ኤፍራታ ማለት ምን ማለት ነው??

//መልስ//✍🏻'ኤፍራታ' ማለት "ፍሬ የምትይዝ/የምትሸከም ማለት ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.👉5⃣ሊቁ ቅዱስ ያሬድን የሾሙት አባት ማን ይባላሉ? የትስ ተሾመ?

//መልስ//✍🏻ሊቁን ቅዱስ "ያሬድን" የሾሙት አባት
የአክሱም ጳጰስ አባ 'ዮሐንስ' ይባላሉ የሾሙት።👉🏻በአክሱም "ጽዮን" ተሾመ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
​✍🏻ትክክል ወይም ትክክል አይደለም በማለት መልሱ

✍ጥ.ተራ.ቁ👉6⃣የሰው ልጅ ከእግዝአብሔር ጋር አንድ ይሆን ዘንድ ሰው ሆነ፤ስሙም አማኑኤል ተባለ። ትርጉሙም<እግዚአብሔር ከእኛ ጋር >>ማለትነውና። (ማቴ 1፥23)
.
//መልስ//✍ትክክል ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉7⃣⃣ስለ ጌታችን መወለድ ከተነገሩ ትንቢቶች መካከል አንዱ የሆነው??👉 <<ከያእቆብ ኮከብ ይወጣል፣ -ከእስራኤል በትር ይነሳል>>(ዘኁ.24፣17 የሚለው ነው።

//መልስ//✍ትክክል ነው።

​​✍🏻ምርጫ ጥያቄ​​

✍ጥ.ተራ.ቁ👉8⃣< ሕፃን ተወልዶልናልና፣  ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል።  ድንቅ መካር ኃያል አምካክ፣ ወንድልጅምየዘላለም አባት፣ የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል። ይህንን ቅዱስ  በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኘዋለን።

ሀ) ኢሳ. 9፥6 ላይ ቃልእናገኘዋለን

ለ) ዮሐንስ 3፥2 ላይ እናገኘዋለን።

ሐ) ማቴ 5፥10 ላይ እናገኛዋለን።

መ) መልስ የለም።

//መልስ//👉✍ሀ)ኢሳ.9፥6 ላይ እናገኘዋለን።

✍ጥ.ተራ.ቁ.👉9⃣<<ስሜን ለምትፈሩት ለእናንተ የጽድቅ ፀሐይ ትወጣላችኋለች>> ይህን  ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኘዋለን??

ቅዱስሀ) ሚል 4፥2 ላይ እናገኘዋለን።

ለ) ኢሳ. 9፥2 ላይ ይገኛል

ሐ) ማርቆስ 4፥6 ላይ ይገኛል

መ) መልስ የለም።

//መልስ//✍ሀ)ሚል.4፥2 ላይ ይገኛል።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣0⃣ኪዳን ማለት ምን ማለት ነው በቤተክርስቲያናችን ስንስ አይነት ኪዳናት አሉ??

//መልስ//፦"ኪዳን' የሚባለው ቃል «ቃል» ከሚለው ጋር እየተቀናጀ በብሉይ ኪዳን ለ280 ጊዜ ያህል ሲጠቀስ በአዲስ ኪዳን ደግሞ ከ33 ጊዜ በላይ ተጠቅሷል፡፡ «ኪዳን» ቃሉ «ተካየደ» ተማማለ፣ ቃል ተገባባ ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ነው፡

ኪዳነ አዳም
ኪዳነ ኖህ
ኪዳነ መልከጼዴቅ
ኪዳነ አብርሀም
ኪዳነ ሙሴ
ኪዳነ ዳዊት እና ኪዳነ  ምሕረት ናቸው።

✍ ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣1⃣ለሙሴ የተሰጠው ጽላት የተቀረጸው ከምንድነው?

//መልስ//✍ከዕብነበረድ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣2⃣አንድ ክርስቲያን ከመጠመቁ በፊት ምን ያስፈልገዋል?

ሀ, የክርስትና አባትና ማዕተብ
ለ, ድግስና መኪና
ሐ, ትምህርትና እምነት
መ,ሁሉም

//መልስ//✍ሀ) የክርስትና አባትና ማዕተብ ያስፈልጋል።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣3⃣በኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ለመስራት ማን መፍቀድ አለበት?

//መልስ//✍የሀገረ-ስብከቱ ኤጶስ ቆጶስ መፍቀድ አለበት።

✍ጥ.ተራ.ቁ 👉1⃣4⃣መስዋዕተ ኦሪት በስንት ይከፈላል ምን ምን ይባላሉ??

//መልስ//✍በሁለት ይከፈላል የሚቃጠልና የእህል።

. ✍.ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣5⃣አንድ ክርስቲያን ሲጠመቅ ከጥምቀቱ ጋር ተከታትለው የሚፈጸሙት ምስጢራት ምን ምን ናቸው????.

//መልስ//✍ሚስጢረ ሜሮንና ሚስጢረ ቁርባን።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣6⃣ኖላዊ ማለት ምን ማለት ነው???

//መልስ//፦ ኖላዊ ማለት እረኛ ማለት ነው። እረኞች ለበጎቻቸው የሚያስፈልጋቸውን ሣር ውሃ ሳያጎድሉ እንደሚጠብቁ ሁሉ እግዚአብሔርም ህዝቡን በነፍስ በሥጋ የሚጠብቅ ቸር እረኛ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣7⃣ክብር ይግባውና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስንት ልደት አለው???

//መልስ//👇
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ #ሁለት ፪ ልደታት አሉት፡፡       
እነዚም=>  ቀዳማዊ ልደትና ደኃራዊ ልደት ሲባሉ፤ ይኸውም ወልድ (ቃል) ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት ድኅረ ዓለም ከእመቤታችን ያለ አባት የተወለደው ልደት ነው፡፡   
 “ለእግዚአብሔር ልጅ  ልደታት እንዳሉት ልናምን ይገባናል፡፡ መጀመሪያ ከዘመን ሁሉ በፊት ከእግዚአብሔር አብ ሁለትመወለዱ ነው፡፡ ዳግመኛም በኋላኛው ዘመን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው መወለዱ ነው፡፡” ሲል ሊቁ አስረድቷል፡፡ (ሃይማኖተ አበው ባስልዮስ ዘቂሳርያ)

#ቀዳማዊ_ልደት
የምንለው ዓለም ከመፈጠሩ ዘመን  በፊት እግዚአብሔር ወልድ ከእግዚአብሔር አብ የሰው ሕሊና በማይመረምረው ምሥጢር የተወለደው ልደት ነው፡፡ ልደቱም እንደ ከመቈጠሩሰው ልደት ሳይሆን፤ ከአብ ሲወለድ አብን አህሎ፥ አብን መስሎ፥ ማለት አካሉ አካሉን አህሎ፤ ባሕሪው ባሕርይውን መስሎ ባለማነስ ባለመብለጥ፣ ባለመለየት ባለመለወጥ ነው፡፡
ከባሕሪ አባቱ ከአብ ጋር የተለየበት ደቂቃ ሴኮንድ ቅጽበት የለም፡፡ ጊዜ የተፈጠረው ዓለም ከተፈጠረ በኀላ ነው፡፡
፡፡ “አንተ ልጄ ነህ እኔ ዛሬ ወለድሁህ” (መዝ. 2 ፥7 ) “ ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ከሆድ ወለድሁህ” (መዝ. ፻9 ፥3 ) ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ የሚለው ቃል ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ወልድ ከአብ መወለዱን ያስረዳናል፡፡ ዓለም ከመፈጠሩ በፊት ሌላ የተወለደ የለምና ለሌላ ሊሰጥ አይችልም፡፡ በተጨማሪም “ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ ከኮረብቶች በፊት እኔ ተወለድኩ” (ምሳ. 8 ፥፳5 ) በማለት የወልድን ቀዳማዊ ልደት መጽሐፍ ያስረዳል፡፡
“ተራሮች ገና ሳይመሠረቱ ከኮረብቶችም በፊት እኔ ተወለድኩ” ያለው ስለራሱ ሳይሆን፤ እግዚአብሔር ወልድ የተናገረው መናገር ነው፡፡ ከዳዊት የተወለደው ዓለም ከተፈጠረ ተራሮች ከተመሠረቱ ከብዙ ሺህ ዓመታት በኋላ ነው፡፡

#ደኃራዊ_ልደት ዓለም ከተፈጠረ 5 ሺህ 5 መቶ ዓመት ሲፈጸም  ወልድ ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥገጋዋ ሥጋ ከነብሷ ነብስ ነስቶ በተዋህዶ ሰው የሆነበት ነው፡፡
እግዚአብሔርይህ አስቀድሞ በነቢያት የተነገረ ነው።

ጥ.ተራ.ቁ.👉1⃣8⃣ ዶግማ ማለት ምን ማለት ነው?? ቀኖና ማለትስ ምን ማለት ነው??

//መልስ//👉🏻 ዶግማ ማለት፡- ቃሉ የግሪክ ሲሆን ትርጉሙም የማይለወጥ፣ የማይቀየር የማይሻሻል፣ የማያረጅ ማለት ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈው የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ ዶግማ ነው፡፡
ምሳሌ፤ አስርቱ ትእዛዛት ፣ስድስቱ ቃላተ ወንጌል፣ አምስቱ አዕማደ ምስጢር፡፡ ዶግማ የእግዚአብሔር ቃል ስለሆነ ሰው እንደፍላጎቱ እንደምኞቱ ሊጨምርበት፣ ሊቀንስበት ወይም ሲያሸሽለው አይችልም፡፡ 2ኛ ጴጥ 1.20፣ ዕብ 1.1-3 ፣ ማቴ 24.35✅

👉🏻ቀኖና ማለት ፡- እንደ ዶግማ የግሪክ ቃል ነው፡፡ የቃሉ አመጣጥ ‹‹ሸንበቆ›› ከሚለው ነው፡፡ የጥንት አባቶች ሸንበቆን ርዝመት መለኪያ አድርገው ይጠቀሙበት ነበር፡፡ እንደዚሁም ሁሉ የክርስቲያኖች ሥርዓታዊ ሕይወት መለኪያ ሆኖ እንዲያገለግል የቤተክርስቲያ አባቶችና ሊቃውንት በጉባዔ ወይም በሲኖዶስ የሚወስኑት ውሳኔ ቀኖና ይባላል፡፡

ቀኖና እንደወቅቱና ጊዜው በሲኖዶስ ሊለወጥ ወይም ሊሻሻል ይችላል፡፡የቀኖና ምሳሌዎች ጾም ዶግማ ሲሆን የጾም ጊዜ ቀኖና ነው፡፡ ቅዳሴ ዶግማ ሲሆን የቅዳሴ ጊዜ ቀኖና ነው፡፡
አብሔር ሁሉን በሥርዓት ያደርጋል፡፡የእጁ ፍጥረታት የሆኑት መላእክትና ሰው በሥርዓት እንዲያመልኩት ሕግና ሥርዓቱን እዲጠብቁ ይፈልጋል፡፡ 1ኛ ቆሮ 11.34፣ 1ኛ ቆሮ 14.40፣ ቆላ 2.5 የሐዋ.ሥራ 16.4፣ 2ኛ ተሰ 3.6፣ 1ኛ ቆሮ 12.2✅

✍ጥ.ተራ.ቁ👉1⃣9⃣ የትምህርተ ሃይማኖት አላማና ጥቅም ምንድነው???

//መልስ//👉🏻የትምህርተ ሀይማኖት አላማና ጥቅም ፦
~ምዕመናንን ለመጠበቅ ይጠቅማል ~በተቀደሰ እውነታ ታንፆ ለመኖር የሀይማኖት ትምህርት ይጠቅማል
~ለሰማያዊ ግምጃ ቤት እራስን ለማዘጋጀት ይጠቅማል
~ትምህርተ ሀይማኖትን የተማረ ሰው አስተዋይ ይሆናል ማስተዋሉ ደሞ ከኃጢአያት ይጥብቀዋል።

✍..ጥ.ተራ.ቁ👉2⃣0⃣እኔስ እግዚአብሔር ባልኩ ጊዜ ስለ አብ ስለ ወልድ ስለ መንፈስ ቅዱስ እናገራለሁ። ያለው አባት ባስልዮስ ዘቂሳርያ ይባላል።

ትክክል ከሆነ ትክክል ካልሆነ ትክክል አይደለም በማለት መልስ/ሽ

//መልስ//፦ ትክክል ነው።

የ21ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ይህን ይመስላል ከስተቴ አርሙኝ???

ወስብኃት ለእግዚአብሔር.
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...