2017 ዲሴምበር 22, ዓርብ

ብሒለ አበው

ብሒለ አበው

*ጾም በአባቶች አንደበት*
❖ጾም የጤንነት እናት ፥ የፍቅር እኅት ፥ የትሕትና ወዳጅ ናት፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

❖መመጽወትና መጾም ለነፍስ ሕይወትን ለሥጋ ጤንነትን ይሰጣል፡፡
አንጋረ ፈላስፋ

❖ያለ ጸሎት መንፈሳዊ ነኝ የሚል ሰው እሳት መካከል ገብቶ የሚጫወትን የእሳት እራትን ይመስላል፡፡
ማር ይስሐቅ

❖ጾም ጸሎት ከሥግደት ጋር ከሆነ የጦር ዕቃ ነው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

❖በወንድሙ ውድቀት የሚደሰት ሰው ተመሳሳይ ውድቀት ይጠብቀዋል፡፡
ቅዱስ ኤፍሬም

❖በእግዚአብሔር ዘንድ ባለሟልነትን ታገኝ ዘንድ ታገስ
ማር ይስሐቅ

❖ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው ፥ መላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኮልንም ከመናገር ይከልክል ፤
የሐዋርያት አለቃ የመጀመሪያይቱ የቅዱስ ጴጥሮስ መልዕክት ፫፥፲

❖አሁንስ ይላል እግዚአብሔር ፥ በፍጹም ልባችሁ ፥ በጾምም ፥ በለቅሶና በዋይታ ወደ እኔ ተመለሱ፡፡
ነቢዩ ኢዩኤል ፪፥፲፪

❖ልብህ ይጫወት ዘንድ አፍህን ዝም አሰኘው ከእግዚአብሔር ጋር ይነጋገር ዘንድ ደግሞ ልብህን ዝም አሰኘው፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ ሳባ

<<<ጾምን ቀድሱ ፥ ጉባኤውንም አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ ፥ ወደ እግዚአብሔርም ጩኹ>>> ኢዩ• ፩፥፲፬saramareyama.890@gmail.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...