2017 ዲሴምበር 11, ሰኞ

ውዳሴሃ ለእግዝትነ ማርያም ድንግል ዘይትነበብ በዕለተ#ሰሉስ#

የማክሰኞ ውዳሴ ማርያም
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።saramareyama.890@gmail.com
የመመኪያችን ዘውድ የድኅነታችን መጀመሪያ የንጽሕናችንም
መሠረት እኛን ስለማዳን ሰው የሆነ የእግዚአብሔር ቃል
በወለደችልን በድንግል ማርያም ተገኘልን ሰው ከሆነ በኋላም
ፍጹም አምላክ ነው
ስለዚህም በድንግልና ወልደችው። ድንቅ የሆነ የመወለድዋ
ችሎታ የማይመረመር ሊነገር የማይችል ነው። ቅድስት ሆይ
ለምኝልን።
በእርሱ ፈቃድ ከአባቱ ፈቃድ በመንፈስ ቅዱስ መጥቶ አዳነን።
በድንግልና ፍጽምት የሆንሽ ማርያም ሆይ የድንግልናሽ
ምሥጋናና ክብር ታላቅ ነው እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ቢሆን
ከምድር እስከ ሰማይ ደርሳ የእግዚአብሔር መላእክት
ሲወጡባት ሲወርዱናት ያያት መሰላል አንቺ ነሽ። ቅድስት ሆይ
ለምኝልን።
ሙሴ በነደ እሳት ሳትቃጠል ያያት ዕፅ አንቺ ንሽ ይኸውም
መጥቶ በማኅፀንሽ ያደረው የእግዚአብ
ሔር ልጅ ነው የመለኮቱ እሳትነት ሥጋሽን አላቃጠለውም።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ዘር ያልተዘራባት እርሻ አንቺነሽ የሕይወት ፍሬ ከአንቺ ወጣ።
ዮሴፍ የዋጃትና የከበረ ዕንቁን ያገኘባት ሣጥን አንቺ ነሽ
ይኸውም መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው በማኅፀንሽ አደረ
በዚህ ዓልምም ወለድሸው ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የመላእክት ደስታቸው የሆነ ጌታን የወለድሽ ሆይ ደስ ይበልሽ።
የነቢያት ዜናቸው ንጽሕት ሆይ ደስ ይበልሽ እግዚአብሔር
ከአንቺ ጋር ቢሆን ባለሟልነትን አግኝተሻልና ደስ ይበልሽ።
የዓለም የሰው ሁሉ ደስታ የሆነ የመልአኩን ቃል ተቀብለሻልና
ደስ ይበልሽ። ዓለምን ሁሉ የፈጠረ ጌታን የወለድሽ ሆይ ደስ
ይበልሽ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
በሚገባ የአምላክ እናት ተብለሻልና ደስ ይበልሽ። የሔዋን
መድኃኒት ሆይ ደስ ይበልሽ። ፍጥረቱን ሁሉ የሚመግበውን
እሱን ጡትሽን አጥብተሽዋልና ደስ ይበልሽ። የሕያዋን
(የጻድቃን) ሁሉ እናታቸው ህይ ደስ ይበልሽ። ትለምኝልን ዘንድ
ወደ አንቺ እናንጋጥጣለን።ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ድንግል ሆይ ቅድስት ሆይ ጌታን የወለድሽ ሆይ እኛን ለማዳን
ድንቅ ምሥጢር (ተዋህዶ) በአንቺ ቢደረግ ንጉሥን
ወልደሽልናልና ፍጥረታትን በልዩ ልዩ መልክ የፈጠረ የርሱን
የገናንነቱን ነገር ፈጽመን መናገር አይቻለምና ዝም እንበል።
ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ወደ ደብረሲና የወረደ ለሙሴ ሕግን የሰጠ የተራራውን እራስ
በጽጋግ በጢስ በጨለማና በነፋስ የሸፈነ ፈርተው የቆሙትንም
በነጋሪዎሽ ድምጽ የገሠፀ የአብ አካልዊ ቃል ነው። ቅድስት
ሆይ ለምኝልን።
በትሕትና የተጋገርሽ ተራራ ሆይ ይኸውም ወደ አንቺ የወረደው
ነው ሰውን የወደደ እርሱ ያለመለወጥ ባንቺ ሰው ሆነ እንደ እኛ
በሚናገር ሥጋ ፍጹም ሆኖ አምላክ በመንፈስ ቅዱስ በማህፅኗ
አደረና ፍጹም ሰው ሆነ አዳምን ያድነው ዘንድ ኅጢአቱንም
ያስተሠርይለት ዘንድ በሰማያት (በሰማያዊ መዓረግ) ያኖረው
ዘንድ በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ወደ ቀድሞው ቦታው
ይመልሰው ዘንድ ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የድንግልን ገናነቷን ሊናገሩት አይቻልም። ጌታ መርጧታልና
የሚቀርበው በሌል ብርሃን ውስጥ የሚኖር እርሱ መጥቶ
አደረባት ዘጥኝ ወር በማኅፀንቃ አደረ የማይታይና
የማይመረመር (ታይቶ የማይታወቅ) እርሱን በድንግልና
ወለደችው ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
ነብዩ ዳንኤል ያየው ያለ እጅ ከረጅም ተራራ የተፈነቀለው ያ
የደጊያ ከአብ ዘንድ የወጣው ቃል ነውና መጥቶ ያለ ወንድ ዘር
ከድንግል አዳነን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
እንደ ንጽሕ ጫፍ ሆነሽ የሃይማኖት መገኛ ነሽ የቀናች የቅዱሳን
አባቶቻችን ሃይማኖታቸው ነሽ። አምላክን የወለድሽና
በድንግልና የታተምሽ ንጽሕት ሆይ የአብን ቃል ወለድሽልን
ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን መጣ ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የከበርሽ ጌታን የወለድሽ ሆይ የማይታይ ቃልን የተሸከምሸው
የብርሃን እናቱ አንቺ ነሽ እሱን ከወለደሽው በኋላ በድንግልና
ኖረሻልና በፍጹም ምስጋና ያገኑሻል ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
የአብ ቃል እናቱ ንጽሕት ድንግል ሆይ ስለአንቺ የሚነገረውን
ነገር መናገር የሚቻለው ምን አንደበት ነው ኪሩቤል
ለሚሸከሙት ንጉሥ ዙፋኑ (ማደሪያው) ሆንሽ የተከበርሽ ሆይ
እናመሰግንሻልን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ መልካሟ
እርግብ ሆይ ስምሽን እንጠራለን። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።
እናትና ገረድ ማርያም ሆይ ደስ ይበልሽ። የታቀፍሽውን
መላእክት ያመሰግኑታል ኪሩቤልም በፍርሃት ይሰግዱለታልና
ሱራፌልም ያለማቋረጥ ንጉሥ (የክብር ባለቤት) ይህ ነው
በይቅርታው ብዛት የዓለምን ኃጥያት ያሰተሰርይ ዘንድ የመጣው
ይህ ነው ይላሉ። ቅድስት ሆይ ለምኝልን።

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...