2017 ዲሴምበር 28, ሐሙስ

የምዕራፍ ሁለት/የ20ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃል መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን አላችሁልኝ??
......ሰላማችሁ ይብዛ እያልኩ እነሆ የምዕራፍ ሁለትን የ20ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ መረሀ ግብር እንዲህ ይቀርባል....
።።።።።።።።።።።።።።።።

✍✅ጥ ተራ ቁ.↪1⃣ ሰብአ ሰገል ማለት ምን ማለት ነው??? ሰባ ሰገል ወርቅ፤ ዕጣን፤ ከርቤ፤ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የመገበራቸው ምስጢር ምንድነው??  አንደምታውን በዝርዝር አስረዳ???

//መልስ//👉ሰብአ ሰገል ማለት፦ በአጭሩ የጥበብ ሰዋች ማለት ነው።
👉ሰብአ ሰገል ወርቅ ዕጣን ከርቤ መገበራቸው #ወርቅ ለንግስናው አንድም በፊት ይህንን የምንገብርላቸው ቀድሞ ፍጡራን ኋላም ሀላፊያን ናቸው አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርክ ኋላም የማታልፍ ነህ ሲሉ አንድም ወርቅ ፅሩይ ነው አንተም ፅሩይ ባህሪ ነህ ሲሉ #ዕጣን ለዘላለማዊ ክህነቱ አንድም በፊት ይህንን  ቀድሞ ፍጡራን ኋላም ሀላፊያን ናቸው አንተ ግን ቀድሞም ያልተፈጠርክ ኋላም የማታልፍ ነህ ሲሉ አንድም ዕጣን ምዑዝ ነው የምንገብርላቸውአንተም ምዑዘ ባህሪ ነህ ሲሉ #ከርቤ ለሞቱ አንድም ምንም እንኳን ቀድሞም ያልተፈጠርክ ኋላም የማታልፍ ብትሆን በለበስከው ሥጋ  ሲሉ አንድም ከርቤ የተሰበረውን ይጠግናል የተለያየውን አንድ ያደርጋል አንተም ከመላእክት የተለየውን አዳምን አንድ ትሞታለህታደርጋለህ ሲሉ ገብረውለታል

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪2⃣ ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የጌታችን ልደት የተረዳባቸው ምክንያቶች  ምን ምን ናቸው???

//መልስ//👉ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ የጌታን ልደት ያወቀበት ወይም የተረዳበት ምልክቶች  (1ኛ)ፍርሀተ ኖሎት ወይም የእረኞች ፍርሀት (2ኛ)የመላእክትን ምስጋና በሰማ ጊዜ (3ኛ)የሰብአ ሰገል መምጣትና መገበር (4ኛ)ደማቅ ኮከብ መታየት (5ኛ)የጌትነቱ ወይም የአምላክነቱ ብርሃን ናቸው።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪3⃣ አስቀድሞ ካህን የነበረ ነገር ግን የሰማዕታትን መከራ በማየት የእምነታቸውን ጥናትና ጌታችንም እነርሱን ሲፈውሳቸው ተመልእክቶ ልቦናውን ወደቀናች እምነት መልሶ በጌታችን ያመነ በኋላም እንደ ጌታችን በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሰማዕትነትን የተቀበለ ቅዱስ አባት ማን ይባላል??

//መልስ//👉ሉኪያኖስ ይባላል።


✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪4⃣ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን መላአኩ ስንት  ጊዜ አበሰራት ??

//መልስ//👉3 ጊዜ አበሰራት
👉ውሃ ስትቀዳ፤ ወደ ቤተ መቅደስ ስትገባ እና ወደ ዮሴፍ ቤት ስትገባ

👉አንቺ ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ ( ሉቃ ፩  ÷፳፮ _፴፰

👉 እግዚአብሔር ከአንችቺ ጋር ነውና ደስ ይበልሽ ( ማቴ ፩÷፲፰ _፳፭) 1÷18-25)

✍✅ጥ.ተራ.ቁ. ↪5⃣ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለ ሥላሴ አንድነት የሚያስረዱን ምዕራፍና  ቁጥሮች ጥቀስ/ሽ??

//መልስ//👉እግዚአብሔር አለ፤ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር (ዘፍ 1፥26)

👉 አዳም ከእኛ እንደ አንዱ ሆነ ( ዘፍ 3፥23)

👉 ኑ እንውረድ አንዱ የአንዱን ነገር እንዳይሰማው ቋንቋቸውን በዚህ እንደባልቀው (ዘፍ 11፥7)

👉ዮሐንስ 10፥30 እኔና አብ አንድነንይልላል ሌሌችንም ጥቅሶች መትቀስ ይላልቻ።

✍✅ ጥ.ተራ.ቁ.↪6⃣አንደበታችን የድንግልን ስራ ያመሰግናል ያለው ቅዱስ አባት ማን ይባላል???

//መልስ//👉ቅዱስ ኤፍሬም ነው።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪7⃣እግዚአብሔር አምላክህን በፍፁም ልብህ በፍፁም ነፍስህ በፍፁም ኃይልህ ውደድ።
 ይህ ኃይለ ቃል በየትኛው  የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል  ይገኛል ?  ምዕራፍና ቁጥሩስ??

//መልስ//👉ዘዳግም (6፥4-6)
👉ማር (12፥30)
👉ሉቃስ(10፥27)

✍✅ ጥ.ተራ.ቁ.↪8⃣ገድል ማለት ምን ማለት ነው ?


//መልስ//👉ገድል ማለት፦ ተጋደለ ከሚል የግዕዝ ቃል የወጣ ሲሆን ተጋደል፣ ተዋጋ ፣ታገለ፣ ስለ ክርስቶስ ፍቅር ከዓለም ጋር በሥጋ ከዓለማውያን ነገስታት ጋር.. ከዲያብሎስ ጋር  መዋጋት ወዘ..ተ ማለት ነው ።

✍✅ጥ. ተራ.ቁ.↪9⃣የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን አማላጅነት ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በማስረጃ ጥቀስ/ሽ???
//መልስ//👉ዮሐንስ (2 ፥3)
ሉቃስ (1፥28--1፥48)
መዝሙር (45፥9)
ኢሳያስ (62 ፣2)

ወ.ዘተ..

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪1⃣0⃣ እስራኤላውያን ከግብጽ ሲወጡ  በግብፅ ላይ  የተከሰተውን መቅሰፍትን  ዘርዝሩ ???

መልስ 👉ውሃው ወደ ደም ተለወጠ
👉እንቆራሪቶች
👉ቅማል
👉 የእንስሳት እልቂት
👉 በረዶ
👉 የአንበጣ መንጋ
👉 ጨለማ
👉በቁስል መመታት።
👉የግብፃውያ  የበኩር ልጆች እልቂት ወ.ዘተ የመሳሰሉት።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ↪1⃣1⃣በአዲስ ኪዳን ታቦትና ፅላት በማን ይመሰላል???

//መልስ// 👉 ታቦት፦ እመቤታችን ድንግል ማርያም የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ማደርያ ሆናለችና  በታቦት እንመስላታለን።
ፅላት፣ በአምላካችን በመድኃኔታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ይመሰላል።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪1⃣2⃣ በዕለተ ምጽአት ሰዎች ለፍርድ በሚቆሙ ጊዜ ጻድቃን በምን ፣ ኃጥአን ደግሞ በምን ይመሰላሉ? ምዕራፍና ቁጥሩስ?

//መልስ//👉 ጻድቃን በበግ ኃጥአን በፍየል ይመሰላሉ፡፡ ማቲ(.27÷34)


✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪1⃣3⃣ በሥርዓተ ቅዳሴ ጊዜ ዲያቆኑ ምስባክ ይሰብካል ለመሆኑ ምስባኩ ከየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው?

//መልስ//፡- ከመዝሙረ  ዳዊት ነው።

✍✅ጥ.ተራ.ቁ↪1⃣4⃣አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በጸሎት ብዛት እግራቸው ተቆርጦ ሰባት ዓመት በአንድ እግራቸው ቆመው የጸለዩበት ቦታ የት ነው?

//መልስ//፡- ደብረ አስቦ/ ደብረ ሊባኖስ አካባቢ/

✍✅ጥ.ተራ.ቀ.↪1⃣5⃣ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የምሕረት ቃል ኪዳን የተቀበለችበት እና የጸለየችበት ቦታ የት ነው??

//መልስ//፡-በጎለጎታ በጌታ መቃብር ላይ ነው፡፡ / የካቲት 16/

✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪1⃣6⃣በ 80 አሀዱ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት መጽሐፈ ሶስናና ተረፈ ዳንኤል ከየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል  ጋር ቆጠራሉ?

//መልስ//👉ከትንቢተ ዳንኤል ጋር በአንድ ይቆጠራል።


✍✅ጥ.ተራቁ.↪1⃣7⃣ የሰው ልጅ ዕድሜ 70 ቢበዛ 80 ከዚያ ያለፈ ድካምና መከራ ነው ብሎ የተናገረው ማን ነው??

//መልስ//👉ነቢዩ ዳዊት/የሰውመዝሙረ 89፥9-10)


✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪1⃣8⃣ እግዚአብሔር ለአዳም ፣ ለአብርሃም ፣ ለኖህ የገባላቸው ቃል ኪዳን ምን ነበር??

//መልስ//፡- 👉ለአዳም፦ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለው፡፡
👉ለአብርሃም፡- የሚባርኩህን እባርካለው ……
👉ለኖህ፦ ከአሁን በኋላ በንፍር ውሃ አላጠፋችሁም፡፡

✍✅ጥ.ተራ.ቁ..↪1⃣9⃣ኢየሱስ ፣ አማኑኤል ፣ ክርስቶስ እና መድኃኔዓለም የስማአቸውን ትርጉም አስረዳ/ጂ/.??

//መልስ//👉፦-

#ኢየሱስ፡- ኢየሱስ ማለት አዳኝ  ማለት ነው፡፡ ይህ ስሙ ቅድመ ዓለም በአብ ኅሊና ታስቦ ይኖር እንደነበር
መልክአ ኢየሱስ ይመሰክራል፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል መድኃኒትእመቤታችንን ሲያበሥራት “ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ”
ብሏታል፡፡ ሉቃ. 1÷"1፡፡ እመቤታችንና ዮሴፍ ጌታ በስምንት ቀኑ ወደ ቤተ ግዝረት ሲገባ በመልአኩ እንደ ተነገራቸው ኢየሱስ ብለው ጠሩት፡፡ ሉቃ. 2÷21፡፡ ከአምልኮ ጸሎት ፈውስና አገልግሎት የሚከናወነው በዚህ በስሙ ነው፡፡ ይህ ስም የባሕታዊያን የተመስጦ ማዕከል የማኅሌታዊያን የዜማቸው ጣዕም የሰባክያን የአትሮንሳቸው ግርማ ሞገስ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ከዚህ ስም ውጭ ውበት ደምግባት የላትም፡
 #ክርስቶስ፡- ክርስቶስ ማለት የተቀባ መሲህ ማለት ነው፡፡ አይሁድ የጠበቁት መሲህ ነቢያትና ጻድቃን ሊያዩት የናፈቁትጌታ የነፍስ ነጻ አውጪ ስለሆነ ክርስቶስ አሉት፡፡ ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ከእግዚአብሔር ተወልዷል፡፡ 1ዮሐ. 5÷1፡፡
 #አማኑኤል፡- አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ ማለት ነው፡፡ ኢሳ. 7÷14፡፡የተዋረደውን አዳምን ለማክበር ጌታ ኢየሱስ ወደ ዓለም መጥቷል፡፡እርሱ አምላካችን የእኛን ሥጋና ደም ስለተካፈለ ከእኛ ጋራ ሆነ“አማኑኤል” ተብሏል፡፡ ማቴ. 1÷23፡፡
#መድኃኔአለም፡- መድኃኔዓለም ማለት የዓለም መድኃኒት ማለት ነው፡፡ አብ ልጁን የላከው የዓለም መድኃኒት እንዲሆንነው፡፡ 1ዮሐ. 4÷14፡፡ ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ዓለምን አዳነ፡፡ እኛም እንደ ሰማርያ ሰዎች መድኃኔዓለም አልነው የሁላችንም መድኃኒት ነውና፡፡ ዮሐ. 4÷42፡፡

 #የሰው_ልጅ፡- የሰውን ልጆች የእግዚአብሔር ልጆች ለማድረግ ሰው ስለሆነ፡፡ ዮሐ. 6÷63፡፡
 #የእግዚአብሔር_ልጅ፡- የአብ የባሕርይ ልጅ ስለሆነ አባቱን በመልክ ስለሚመስልና በክብር ስለሚተካከል በዚህ ስምተጠራ፡፡ 1ዮሐ. 5÷5፡፡



✍✅ጥ.ተራ.ቁ.↪2⃣0⃣ሚከተሉትን የስም ትርጉሞችን አስረዳ/ጂ/?? ዘሩባቤል ፣ ቤቴል ፣ እና መሪባ፡፡??

//መልስ//መልስ፡- 👉ዘሩባቤል ማለት የባቢሎን ዘር ማለት ነው።
 👉ቤቴል ማለት የእግዚአክርክርብሔር ቤት ማለት ነው።
👉መሪባ ማለት፦ ክርክር፣ጥላቻ ማለት ነው፡፡1ኛ.ዜና 3÷16-19 ፣ ዘፍ.28÷19 ፣ ዘጸ.17÷1-7 እናገኘልለን።

የ20ኛው ዙር ጥቄና መልስ ይህን ይመስላል ከስተቴ ታርሙኝ ዘንድም በትህትና እጠይቃለሁ?..

ወስብሐት  ለእግዚአብሔርsaramareyama.890gmail.com

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...