2017 ዲሴምበር 18, ሰኞ

ቀንቷል መንገዴ/2/

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

saramareyama.890@gmail.comቀንቷል መንገዴ።


ቀንቷል መንገዴ (2)
ክርስቶስ አንተን በመዉደዴ.ቀንቷል 
መንገዴ
      ቀንቷል ኑሮዬ  (2)
     አንድዬ አንተን ተከትዬ ቀንቷል ኑሮዬ

አርፍያለሁኝ ዛሬ በቤቴ
ጭንቄ ተጥሎ ባንተ በአባቴ
በልቤ ዙፍን ንጉሴን ሹሜ
ተደላደልኩኝ በዝቶ ሰላሜ

      ቀንቷል መንገዴ (2)
     ክርስቶስ አንተን በመዉደዴ ቀንቷል መንገዴ

ከእንግዲህ አልዘምትም ሳልታጠቅ
ጌታዬን ሳልይዝ የፍቅሩን ስንቅ
እያለቀስኩኝ የዘራሁት
በሳቅ በደስታ ስበስብኩት
       
 

   ቀንቷል ኑሮዬ (2)
     ኢየሱስ አንተን ተከትዬ ቀንቷል ኑሮዬ

እሳቱ ዉሀ ተራራዉ ሜዳ
ለምለም ሆነልኝ ያምድረ በዳ
ከቁጥር በዝቷል ያንተ ስጦታ
እወድሀለዉ ልዩ ነህ ጌታ

      ቀንቷል መንገዴ (2)
     ክርስቶስ አንተን በመዉደዴ ቀንቷል መንገዴ

የለም በስሙ ያላተረፈ
ከእርሱ ጋር ወጥቶ ማን ተሽነፈ
የቅጥሬን ቋሚ ማንም አይነካ
ጌታ ስላለኝ ልቤ ተመካ
       
        ቀንቷል መንገዴ (2)
      ክርስቶስ አንተን በመዉደዴ ቀንቷል መንገዴ

ቀንቷል ኑሮዬ (2)
ኢየሱስ አንተን ተከትዬ ቀንቷል ኑሮዬ
አንድዬ አንተን ተከትዬ ቀንቷል ኑሮዬ
 ።።።።።።፡።።።።።
     
 ። አድርገህልኛልና።

አድርገህልኛልና በቸርነትህ አመሰግንሀለሁ እልል ልልል
ለዓለም ዓለም(2)አማኑኤል እገዛልሀለሁ መድኅኔዓለም
፦፦፦፦፦፦፦፦አዝ ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ቀኑ ጨልሞብኝ ዙሪያው ገደል ሆኖ
የችግር አረንቋ  ፊቴ ተደቅኖ
ረዳት ያጣሁኝ በመሰለኝ ጊዜ
ፈፅሞ  አራቀልኝ የልቤን ትካዜ
፦፦፦፦፦፦፦፦አዝ ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አምላኬ ጉልበቴ ኃይሌ መመኪያየ
ጠላት ማሳረፊያ የእምነት ጋሻዬ
እንደማትተወኝ አሁን አውቄአለሁ
ካለኝ ነገር ሁሉ ባንተ ታምኛለው
፦፦፦፦፦፦፦፦፦አዝ ፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦
ጥቂቷን አብዝተህ ለምትመግብ ጌታ
የምመልስልህ ባላገኝ ስጦታ
በቀንም በሌሊት ሁሌ የሚያበራ
ምንከር ለባህሪሀ  እፁብ ያንተ ስራ
፦፦፦፦፦፦፦፦፦፦አዝ፦፦፦፦፦፦፦፦፦
አምላክ ሆይ ምስጋና ላንተ ይገባሃል
ለምስኪኗ ጎጆ በረከት ሰጥተሃል
ድሀ ነኝ አልልም ሐብቴ አንተ ነህና
ማሰሮዬ ሞልቷል ሳይጎል እንደገና
 ።።።።።።፡፡።።።።

ባይኖቼ እፈልግሻለዌ

ባይኖቼ እፈልግሻለው
በሥዕ ሁል ጌዜ እጽናናለው
በልቤ ማርያም እያልኩኝ (2)
ዘመኔን ከመከራዳንኩኝ

..አዝ።።።።።።።

አይሰግድም ጉልበቴ ለሀማ
ስለኔ እመቤቴ ቁማ
አልፈራም እጠፍለው ብዬ
መስቀሉን በጀርባዬ አዝዬ

..አዝ።።።።

ሎዛናት የጎኔ ማረፊያ
አልሰጋም ከደጅዋ ሰተኛ
ማርያም ማርያም እያልኩኝ
በስሟ መች ተርቤ አወኩኝ

..አዝ።።።።

አናብስት ይታዘዙላታል
መላእክት ያገለግሏታል
እኔ ግን ሥዕሏን በደረቴ
ታቅፌው ተባርኳዋል ሕይወቴ

..አዝ።፡።

ልቤ ላይ ተስሏል ያው ፍቅሯ
እኖራለው ሁሌም በምልጃዋ
ሰቶኛል አድርጓት መመኪያ
ዘመኔን አልፋለው ከእርሷጋር
።።።።።።።።።።...

ትህትናሽ ግሩም ነው ደግነትሽም(፪)
እናቱ ሆነሻል ለመድኃኔዓለም(፪)

ንጽህት ስለሆንሽ እመቤቴ(፪)
እንከን የሌለብሽ “
የፍጥረታት ጌታ “
በአንቺ ያደረብሽ “
የድንግል መመረጥ “
ዜናው አስገረመኝ “
እሳቱን ታቀፈች “
የማይቻለውን “

ምርኩዜ ልበልሽ እመቤቴ
ጥላ ከለላየ “
ጋሻዬ አንቺ ነሽ “
ለእኔ መመክያዬ “
በአለም እንዳልጠፋ “
ህይወቴ ምርሮብኝ “
እንደ ወይን አጣፍጭው “
ማርያም ድረሽልኝ “

የምስራቅ ደጃፍ ነሽ “
የሁላችን ደስታ “
እሙ ለፀሃይ ፅድቅ “
የሁሉ ጠበቃ “
ድንግል የድል አክሊል “
ድንግል የፅድቅ ሥራ “
ድንግል መሰላል ንሽ “
የተዋህዶ ተስፋ ‘’
 ።።።።።።።።።።።።።
ባማረ ቅኔ በተወደደ
ህይወት ለሠጠን እየታረደ
የእግዚአብሔር ልጅ መድኃኒታችን
ጠርቶህ አይጠግብም አደበታችን

አዝ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡//
 የተሰዋው በግ የሚፈሰው ደም
አልሆነምና ድህነት ለአለም
የፍቅር አምላክ ወደኛ መጣ
ፍጥረት በደሙ ከሲኦል የሚሰዋወጣ

አዝ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡//
ከተናገረ ይፈፅመዋል
ሀሰት አያውቅም ሁሉም ያምነዋል
ሞትን በሞቱ ሽሮ አሸነፈ
በልባችን ላይ ፍቅሩ ተፃፈ

አዝ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡//
ያሁሉ እንባ ያሁሉ ለቅሶ
ከሁላችን አይን ፍፁም ታብሶ
ፍፃሜ አግኝቶ መከራችን
የድል ሆነልን ምስጋናችን

አዝ ፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡//
በአዲሱ ስም አሮጌው አልፏል
በሁለተኛው ስም ህይወት አውጇል
ከፍከፍ ይላል ይሰዋል ገና
ባማረ ቅኔ ባዲስ ምስጋና

ዲ/ን  ወንደሰን በላይ
 ።።።።።።።።።።።።።።።

    ©ዛሬም አለሽ በልቤ
ዛሬም አለሽ በልቤ (3)
ድንግል ሆይ ውለታሽ አይጠፋም ከሃሳቤ
     . አ..ዝ.
እንደ ኃጢአቴ ብዛት እንደበደሌማ
የጥልቁ ሰንሰለት ስያንሰኝ ነው ጨላማ
ግን ያንቺ ሆንኩና ሁሉንም አለፍኩት
ያንን የሞት ባሕር በምልጃሽ ቀዘፍኩት

       ።አ...ዝ።

አርፏል ልቤ ባንቺ ባዛኝቷ ማርያም
ውስጥል እያፈሰሰፍቅር እና ሰላም
ህመሜን ቢያስረሳኝ የውዳሴሽ ቃና
እመቤቴ እላለሁ ዛሬም እንደ ገና
     ።አዝማች።

እናታችን ጽዮን ሰው ሁሉ ይልሻል
ዳዊት በበገና ያመሰግንሻል
የሴቦን ነገስታት ለክብርሽ ዘመሩ
የማትፈርሺ መቅደስ የእግዚአብሔር ሃገሩ

        ።አዝማች።

እጅግ ብዙ ነገር አድርገሽልኛል
ይቅር ባዩ ልጅሽ በፍቅር አይቶኛል
እኔስ እኖራለሁ ድንግል ባንቺ ጥላ
ጨለማን አላይም ከእንግዲህ በኋላ

      ።በዘማሪ ዳ/ን
 ልዑል-ሰግድ ጌታቸው
 ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
    ።ሐዋርያው መነኩሴ።
ሐዋርያው መነኩሴ የመረጡት ሥላሴ/2/
ዋስ ጠብቃ ሆኗል ትክልዬ ለንፈሴ

 ዳሞት ትናገረው ያንተ ሕዋርያነት
የወንጌል ገበሬ የጣኦታት ጠላት
ፀሎተኛው ቅዱስ አባ ተክለሀይማኖት
ክንፍን የተሸለምክ እንደ ሰማይ መላዕክት/2/
            ..አዝ..
ብራናው ሲገልፀ ገደል ትክለሐይማኖት
ከሰው ልጂ ልቦና ይወጣል አጋንት
የቅዳሴው እጣን ሲዎጣ ከዋሻው
ምድረን የባርካል ጸሎተ ምህላው/2/
                 ..አዝ...
የኢትዮጵያን ምድር አርስከው በመስቀል
ጭንጫው ፍራረስ የዘራኸው ወንጌል
ትላንት የዘራኸው ዛሬ ከኛ ሆኗል
አምላከ ተክልዬ ብለን ተምረናል/2/
                ..አዝ...
ከሱራፌል ተርታ ቆመህ ሰተመፀን
ቅዱስ ቅዱስ በለህ ስታመስግን
 ቸርነትን ትትናህ ስግደትህ
ፆምህ ከፍ አደርጎ ሰናይ አደርስን/2/
               ..አዝ..
ዛፉ ሲመነገል አምፀሎትላከ ተከልዬ
ሞቶሎሚም ሲያፈር ቶቅ ሰው ነኝ አለ
ትክልዬ ፀሎቱ በዙ ነው ሚስጥሩ
6ክንፍ አወጣ ቢቆረት አንደ እግሩ/2/

።።።።።።።።።።።።።።
♥ሰብህዎ♥
።።።።።።።።
ስብህዎ ለአምላክነ ሀሌሉያ ለእግዚአብሔር (2)
በሰማይ በምድር (3) 2

አዝ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ሰማይን ያለ ምሰሶ አጥብቋል በቃሉ
መሬትን በውሆች መሐልሁሉ መስርቷል እነሆ
ይታያል ያበራል ጌታ ዛሬም በስራው
ምስጉን ነው ሰራዊት  ያመሰገነው

አዝ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ምህረቱ ይቅርታው ብዙ ከወሰንታላቅ የሰፋ
አባት ነው ብርቱ መጠጊያ የሰው ልጆች ተስፋ
መጋቢ ለፍጥረት ዓለም  ባለ ጸጋ
ያብባል ይለመልማል እሱን የተጠጋ

አዝ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
ተመስገን/2/ይላል የተጎበኘ ሰው
ከጥፋት ከጉስቁልና ከሞት የመለሰውየጌታ
ይቀባል ከታች አንስቶ ከእረኝነት ቦታ
ይቅርታ ጸጋው ብዙ ነው ምህረቱ

አዝ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
መላእክት በላይ በሰማይ ይዘምሩለታል
ዳዊትም ከበገናው ጋር ለቅኔ ተነስቷል
በምድርም እኛ ልጆቹ እንበል ንሴብሆ
ይገባል ለአምላከ እስራኤል ውዳሴ አምልኮበመስቀል
።።።።።።።።።
‬: በፍቅር ተስቦ
†††††††††††
በፍቅር ተስቦ ወረደ ለኛ ሲል
የፍቅሩን ፍፃሜ ገለፀ
ለኛ ያላረገዉ ከቶ ምን አለና
አፋችን ዝም አይበል እናቅርብ ምስጋና
- - - አዝ - - -
ደስ ይበለን......... ሰማያትን ቀዶ
ደስ ይበለን......... ታላቁ አባታችን
ደስ ይበለን......... የዘመናት ንጉስ
ደስ ይበለን......... እየሱስ ጌታችን
ደስ ይበለን......... የኤፍራታዉ ህፃን
ደስ ይበለን......... በዳዊት ከተማ
ደስ ይበለን......... ተወልዶ ማደሩን
ደስ ይበለን......... ምስራች ተሰማ
- - - አዝ - - -
እንዳንተ ያለ......... በኃጢአያት ዉስጥ ወድቀን
እንዳንተ ያለ......... ስኖር ተጎሳቁለን
እንዳንተ ያለ......... አምላክ የኔ ጌታ
እንዳንተ ያለ......... ከሞት ዉስጥ አዳንከን
እንዳንተ ያለ......... ዝናዉን አዉረዉ
እንዳንተ ያለ......... ለአህዛብ ሁሉ
እንዳንተ ያለ......... እንደ እግዚአብሔር ያለ
እንዳንተ ያለ......... ማንም የለም በሉ
- - - አዝ - - -
ደስ ይበለን......... ወረደ ወምድር
ደስ ይበለን......... ሰላሙን ሊሰጠን
ደስ ይበለን......... ሰላም ለናንተ ይሁን
ደስ ይበለን......... ብሎ ሰበከልን
ደስ ይበለን......... በመሰስቀል ተሰቅሎ
ደስ ይበለን......... እኛን የተቤዘን
ደስ ይበለን......... ከሲኦል እስራት
ደስ ይበለን......... በፍቅሩ የ ፈታን
- - - አዝ - - -
ሃሌ ሉያ......... ምስጋና በሰማይ
ሃሌ ሉያ......... ምስጋና በምድር
ሃሌ ሉያ......... ሁሉን ቻይ ለሆነዉ
ሃሌ ሉያ......... ለቸሩ እግዚአብሔር
ሃሌ ሉያ......... ሃሌ ሉያ ለእርሱ
ሃሌ ሉያ......... ለነፍሳችን ጌታ
ሃሌ ሉያ......... ዝማሬን አናቅርብ
ሃሌ ሉያ......... ከጠዋት እስከ ማታ

ምንም አስተያየቶች የሉም:

አስተያየት ይለጥፉ

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...