ቅዳሜ 27 ኦክቶበር 2018

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን!

↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️

1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር
  ሀ. ድጓ፣ጾመ-ድጓ እና መዋስዕት
  ለ. ቅኔ፣አቋቋም እና ዕጣነ-
  ሐ. ዋዜማ፣ስብሐተ-ነግህ እና አርያም
  መ.ግእዝ፣ዕዝል እና አራራይ


✅መ

2⃣ በሥርዓተ ክርስትና ወቅት፡በተጠማቂው ተገብቶ ጸሎተ ሃይማኖትን የሚያደርሰው ማን ነው?
  ሀ. ወላጅ አባት ወይም እናት
  ለ. ክርስትና አባት ወይም እናት
 ሐ. መምህረ-ንስሐ
 መ. በክርስትናው ጸሎት የተሰበሰበው ምዕመን

✅ለ

3⃣ «ክርስቶስ ተንሥአ እምሙታን/እሙታን» ለሚለው ሰላምታ ምላሽ የሚሆነው፡
  ሀ. አሠሮ ለሰይጣን
  ለ. በአማን
  ሐ. በዐብይ ኃይል ወሥልጣን
  መ. አግአዞ ለአዳም

✅ሐ

4⃣ የዐብይ ጾም የመጀመሪያው እሁድ ምን በመባል ይታወቃል?
  ሀ.ቅድስት
  ለ. ብርሃን
  ሐ. ዘወረደ
  መ.ምኩራብ

✅ሐ

5⃣ በቤተክርስቲያን ሻማ ምሳሌነቱ ምንድን ነው?
  ሀ. ለመንግስተ-ሰማያት ብርሃን
  ለ. ለእግዚአብሔር ብርሃን መሆን
  ሐ. ለቅዱሳን ሕይወት
  መ. ሁሉም መልስ ይሆናሉ
.
✅መ

6⃣ ኢየሱስ የሚለው ስም ትርጓሜው ምንድን ነው?
  ሀ. መሲሕ
  ለ. ንጉሥ
  ሐ.ጌታ
  መ. መድኃኒት
.
✅መ

7⃣ ዐራቱ ወንጌላውያን ከአርባዕቱ (ዐራቱ) እንስሳት በተጨማሪ በዐራቱ ወቅቶች ይመሰላሉ።ከነዚህ መካከል በበጋ ወቅት የሚመሰለው ማን ነው?
  ሀ. ቅዱስ ማቴዎስ
  ለ. ቅዱስ ማርቆስ
  ሐ. ቅዱስ ሉቃስ
  መ. ቅዱስ ዮሐንስ

✅ሀ መቅድመ ወንጌል

8⃣ ከሚከተሉት ውስጥ የመንፈስ ቅዱስ ምሳሌ ያልሆነው የትኛው ነው?
  ሀ. ርግብ
  ለ. ነፋስ
  ሐ. እሳት
  መ. በግ

✅መ

9⃣ ወንጌል የሚለው ቃል ሲተረጎም፡
  ሀ. ቃለ እግዚአብሔር ማለት ነው።
  ለ. የክርስቶስ ሕይወት ማለት ነው።
  ሐ. ግብረ ሐዋርያት ማለት ነው።
  መ. የምሥራች/መልካም ዜና ማለት ነው።

✅መ

1⃣0⃣ ዕጣን በቤተክርስቲያን ያለው ምሳሌነት፡
  ሀ. የቅዱሳን ጸሎት መዓዛ ነው
  ለ. የእመቤታችን ምሳሌ ነው
  ሐ. የተስፋ መንግሥተ ሰማያት ምሳሌ ነው
  መ. ሁሉም መልስ ይሆናሉ።

✅መ

1⃣1⃣ ኦርቶዶክሳዊ የቤተክርስቲያን ሕንፃ አሠራር የትኛውን ቅርጽ ሊይዝ ይችላል?
  ሀ. ክብ
  ለ. ሰቀላማ/መርከብ ቅርጽ
  ሐ. መስቀል
  መ. ሁሉም መልስ ይሆናሉ።

✅መ

1⃣2⃣ በግእዝ «መምህር« ካለ በዕብራይስጥ ----------------- ይላል።
  ሀ. ቦአኔርጌስ
  ለ. ረቢ
  ሐ. ጣቢታ
  መ. ኤፍታህ

✅ለ

1⃣3⃣ በቅዳሴ ሰዓት ንፍቅ ዲያቆኑ የቅዱስ ጳውሎስን መልዕክት ሲያነብ ፊቱን ወደየት አዙሮ ነው?
  ሀ. ወደ ምሥራቅ
  ለ. ወደ ምዕራብ
  ሐ. ወደ ሰሜን
  መ. ወደ ደቡብ

✅ሐ

1⃣4⃣ ቅዳሴውን ሲጀምር«ልቤ መልካም ነገር አፈለቀ»በማለት ከዳዊት መዝሙር የጠቀሰው ማን ነው?
  ሀ. ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ
  ለ. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
  ሐ. ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
  መ. አባ ሕርያቆስ

✅መ

1⃣5⃣ ጸሎተ ፍትሐት ሰው በሞተ በሦስተኛው ቀን የሚደረገው ለምንድን ነው?
  ሀ. የእግዚአብሔርን ሦስትነት ለማጠየቅ
  ለ. መጽሐፍ «ነገር በሦስት ይጸናል» ስለሚል
  ሐ. ክርስቶስ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ መነሳቱን ለማጠየቅ
  መ. መልስ የለም

✅ሐ

1⃣6⃣ ርዕሰ መነኮሳት በመባል የሚታወቀው አባት ማን ነው?
  ሀ. አባ መቃርዮስ
  ለ. አባ ጳውሊ
  ሐ. አባ እንጦንስ
  መ. አባ ጳኩሚስ

✅ሐ

1⃣7⃣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በሰዓታት ድርሰቱ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ምን በማለት ጠርቷታል?
  ሀ. የመላዕክት እኅት
  ለ. የሰማዕታት እናት
  ሐ. የጻድቃን እመቤት
  መ. ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣8⃣ የቤተክርስቲያን ዶግማ ስንል፡
  ሀ. የሚሻሻል የሚለወጥ ሥርዓት ማለት ነው።
  ለ. የማይሻሻል የማይለወጥ ትምህርተ ሃይማኖት ማለታችን ነው።
  ሐ. ቀኖና ማለታችን ነው።
  መ. ትውፊት ማለታችን ነው።

✅ለ

1⃣9⃣ ሰብአ ሰገል ( የጥበብ ሰዎች) ለጌታችን ካመጧቸው ስጦታዎች መካከል በፍቅር የሚመሰል የትኛው ነው?
  ሀ. ወርቅ
  ለ. ዕጣን
  ሐ. ከርቤ
  መ. መልስ የለም

✅ሐ

2⃣0⃣ በሥርዓተ ቅዳሴ ወቅት ካህኑ የማቴዎስን ወንጌል ካነበበ በኋላ «ሰማይ እና ምድር ያልፋሉ፥ ቃሌ ግን አያልፍም አለ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ» ይላል።የማርቆስ ወንጌል ከተነበበ በኋላ የሚባለው የቱ ነው?
  ሀ. ኦሪት እና ነብያት ከተናገሩት አንዲት ከምታልፍ ሰማይ እና ምድር ቢያልፉ ይቀላል
  ለ. ሰሚ ጆሮ ያለው ይስማ
  ሐ. በወልድ ያመነ የዘላለም ሕይወት አለው
  መ. መልስ አልተሰጠም

✅ለ

🖊ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል💐
ቻናላችን ለመቀላቀል
saramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ 5 የ45ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

Watch "የምዕራፍ አምስት (፭) የ45ኛዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃል ጥያቄና መልስ ውድድርhttps://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8V" on YouTube
https://youtu.be/Lrf4stF7NSE

https://youtu.be/Lrf4stF7NSE
✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን!

↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 45ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️

1⃣.መጠመቅ ያለብን በማን ስም ነው?
ሀ/ በኢየሱስ
ለ/ በእግዚአብሔር አብ ስም
ሐ/ በመንፈስ ቅዱስ ስም
መ/ በአብ ፡በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም

✅መ

2⃣.ከጌታችን መድኃኂታችን ኢየሱስ ከርስቶስ ልደት አስቀድሞ የሚመጡ ሦስት እሑዶች ስያሜያቸው ምንድን ነው?
ሀ/  ስብከት ፡ኒቆዲሞስ ደብረ-ዘይት
ለ/  ቅድስት፡ ዘወረደ፡ መፃጉዕ
ሐ/ ስብከት፡ ብርሃን ፡ኖላዊ
መ/ ምኩራብ ፡ገብርሔር፡ ብርሃን

✅ሐ

3⃣.የሰው ልጅ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ መፈጠሩ ግልጽ ሲሆን ዕድሜውም እንዲሁ በዐራት ደረጃዎች የተከፈለ ነው።በዚህም መሠረት ከሃያ እስከ ዐርባ ዓመት ያለው ጌዜ የትኛውን ባሕርይ ያመለክታል?
ሀ/ የነፋስ
ለ/ የእሳት
ሐ/ የውኃ
መ/ የመሬት

✅ለ

4⃣.ስለስንበተ-ክርስቲያንና ስለ ዕለተ ምጽአት የሚናገረው ቅዳሴ?
ሀ/ ቅዳሴ ጎርጎርዮስ
ለ/ ቅዳሴ ማርያም
ሐ/ ቅዳሴ አትናቴዎስ
መ/ ቅዳሴ ባስልዮስ

✅ሐ

5⃣.ቅዱስ ቅባት በመቀባት ከሥጋም ከነፍስም ደዌ የምንድንብት ምሥጢር የትኛው ነው?
ሀ/ ምሥጢረ ሜሮን
ለ/ ምሥጢረ ቀንዲል
ሐ/ ምሥጢረ ተክሊል
መ/ ምሥጢረ ቁርባን

✅ለ

6⃣.የሥርዓተ ቅዳሴ ዋነኛው ዓላማ፣
ሀ/ በኅብረት መጸለይ
ለ/ ወንጌል  መማር
ሐ/ ቅዱስ ቁርባን
መ/ ሁሉም

✅መ

7⃣.በላሕም/ላም/ የሚመስለው ወንጌላዊ ማነው?
ሀ/ ቅዱስ ማቴዎስ
ለ/ ቅዱስ ማርቆስ
ሐ/ ቅዱስ ሉቃስ
መ/ ቅዱስ ዮሐንስ

✅ሐ

8⃣.የቤተክርስቲያን የውስጥ ክፍሎች ምን ምን ተብለው ይታወቃሉ?
ሀ/መቅደስ ፡ቅደስትና ቅኔ ማኅሌት
ለ/ ደጀ ስላም ፡ቤተልሔምና መቅደስ
ሐ/ ቅድስተ- ቅዱሳን መቅደስና ቤተልሔም
መ/ መልሱ አልተስጠም

✅ሀ

9⃣.ከሚከተሉት በቅዳሴ ሰዓት የማይነበብ ምንባብ የትኛው ነው?
ሀ/ ወንጌል
ለ/ ትንቢተ ኢሳይያስ
ሐ/ ከሐዋርያት ሥራ
መ/ ከቅዱስ ጳውሎስ መልዕክታት

✅ለ

🔟.ምሥጢረ ቁርባን
ሀ/ ኀብስቱ ወደ ሥጋ መለኮት ወይኑ ወደ ደመ መለኮት የሚለወጥበት ምሥጢር
ለ/ ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢራት የሚመደብ ነው
ሐ/ እያንዳንዱ ክርስቲያን ሊሳተፍበት የሚገባ ምጢር ነው
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣1⃣.ከሚከተሉት በዕለቱ የተጋደሉትን ቅዱሳን ታረክ የምናነብበት መጽሐፍ የትኛው ነው?
ሀ/ መጽሐፍ ስንክሣር
ለ/ ገድለ ሐዋርያት
ሐ/ ድርሳነ ስንበት
መ/ ዜና አበው

✅ሀ

1⃣2⃣.በሥርዓተ ቅዳሴ ሊደረግ የማይገባው ድርጊት የትኛው ነው?
ሀ/ የግል ጸሎት መጸለይ
ለ/ ወሬ ማውራት
ሐ/ መሳቅ
መ/ ሁሉም መልስ ናቸው

✅መ

1⃣3⃣.ከሚከተሉት ስለ ንስሐ ትክክል እና ገላጭ የሆነው የትኛው ነው?
ሀ/ ኃጢታትን ይቅር የሚልና የሚያስተስርይ እግዚአብሔር ብቻ ነው።
ለ/ የሠሩትን ኃጢያት ማመን ለመምህረ- ንስሐ መንገር እና ዳግም ላለመስራት መወስን ፡ንስሐ መግባትነው።
ሐ/ ንስሐ መግባት ያለብን በየጊዜው  ነው
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣4⃣.ከትንሣኤ ጀምሮ ለሃምሳ ቀናት የሚቀደስው የትኛው ቅዳሴ ነው?
ሀ/ ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ
ለ/ ቅዳሴ ሐዋርያት
ሐ/ ቅዳሴ ዘሠለስቱ ምዕት
መ/ ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ

✅መ

1⃣5⃣.ምሥጢረ ጥምቀትን የሚፈጽመው ማነው?
ሀ/ ዲያቆን
ለ/ ቄስ
ሐ/ ጳጳስ
መ/ ለእናሐ መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣6⃣.ከዐቢይ ጾም እሑድ ስያሜዎች የማይመደበው የትኛው ነው?
ሀ/ ዘወረደ
ለ/ ምኲራብ
ሐ/ ኖላዊ
መ/ ገብርሔር

✅ሐ.

1⃣7⃣.አንቀጸ አባግዕ/የበጎች አንቀጽ/በመባል የሚታውቀው ክፍል የትኛው ነው?
ሀ/ ማቴ.5
ለ/ ማር.1
ሐ/ ሉቃ.18
መ/ ዮሐ.10

✅መ

1⃣8⃣.ከአሥራ ዐራቱ ቅዳሴያት ጸሐፊዎች መካክል ያልሆነው የትኛው ነው?
ሀ/ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ለ/ ቅዱስ ባስልዮስ
ሐ/ ቅዱስ ኤፍሬም
መ/ ቅዱስ ጎርጎርዮስ

✅ሐ

1⃣9⃣.ምሥጢረ ክህነትን የሚፈጽመው ማን ነው?
ሀ/ ዲያቆን
ለ/ ቄስ
ሐ/ ጳጳስ
መ/ ማንኛውም ክርስቲያን

✅ሐ

2⃣0⃣.ዲያቆኑ ክቡር ደሙን ለምዕመናን የሚያቀብልበት ንዋየ-ቅዱስ ምን ተብሎ ይጠራል?
ሀ/ ጻሕል
ለ/ አጎበር
ሐ/ እርፈ መስቀል
መ/ ማኀፈድ

✅ሐ

ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላለ ከስተቴ እረሙኝ
saramareyama.890@gmail.com

ማክሰኞ 2 ኦክቶበር 2018

የምዕራፍ አምስት(፭)የ44ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

https://youtu.be/ceehMHSXFek

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
@Teyakaenamels
የ2011 ዓ.ም የምዕራፍ አምስት(፭) የ44ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ
💛💛💛💛💛💛💛
@ምንጭ 👉420 ጥያቄዎችthanks  እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ
💛💛💛💛💛💛💛

1⃣✏ከሚከተሉት  የእመቤታችን ምሳሌ የሆነው የትኛው ነው❓
ሀ// የታተመ ፈሳሽ
ለ// ዕፀ ሳቤቅ
ሐ// ታቦት
መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

2⃣✏የቤተ ክርስቲያን የጸሎት መፅሐፍ በመባል የሚታወቀው የትኛው የመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው❓
ሀ// ትንቢተ ኢሳያስ
ለ// መዝሙረ ዳዊት
ሐ// የሉቃስ ወንጌል
መ// የዮሐንስ ራእይ

✅ለ

3⃣✏አንድ ሰው ሞቶ  በሚቀበርበት ጊዜ ፊቱን ወዴት አዙሮ ነው❓

ሀ// ወደ ምስራቅ
ለ// ወደ ምዕራብ
ሐ// ወደ ሰሜን
መ// ወደ ደቡብ

✅ሀ

4⃣✏ከሚከተሉት የመንፈስ ቅዱስ መጠሪያ ያልሆነው የትኛው ነው ❓
ሀ// ጰራቅሊጦስ
ለ// አፅናኝ
ሐ// የእግዚአብሔር እስትንፋስ
መ//ጰንጤ ቆስጤ

✅ሐ

5⃣✏ምስጢረ ሥጋዌ ምንድን ነው ❓
ሀ// የእግዚአብሔርን አንድነት እና ሦስትነት የምናይበት ምስጢር ነው
ለ// አምላክ ሰው የሆነበት ምስጢር ነው
ሐ// የቁርባን ምስጢር ነው
መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅ለ

6⃣✏ከጌታችን ዐበይት በአላት የማይመደበው የትኛው ነው ❓
ሀ// ቃና ዘገሊላ
ለ// ብስራት
ሐ// ልደት
መ// ጥምቀት

✅ሀ

7⃣✏የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ የሆነው የትኛው ነው ❓
ሀ// በእርሻው መካከል ዘር የዘራው ሰው
ለ// እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ሐ// መልካምን ዕንቁ የሚሻ ነጋዴ
መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

8⃣✏ክርስቶስ በተሰቀለጊዜ ግራ ጎኑን የወጋው ወታደር ማን ነበር❓
ሀ// በርባን
ለ// ጥጦስ
ሐ// ዳክርስ
መ// ለንጊኖስ

✅መ

9⃣✏ክርስቲያን ስንት ልደቶች አሉት❓
ሀ// አንድ
ለ// ሁለት
ሐ// ሦስት
መ// አራት

✅ለ

🔟✏ስግደት በምን አይነት ይከፋፈላል❓
ሀ// የአምልኮ እና የጸጋ
ለ// የጸጋ እና የአክብሮት
ሐ// የአክብሮት የጸጋና የአምልኮ
መ// መልሱ አልተሰጠም

✅ሐ

1⃣1⃣✏በቤተ ክርስቲያናችን ቀኖና መሠረት ስንት አፅዋማት አሉ❓
ሀ// 3
ለ// 5
ሐ// 7
መ// 9

✅ሐ

1⃣2⃣ከመንፈስ ፍሬዎች መካከል ቀዳሚነትን የሚይዘው የትኛው ነው❓
ሀ// ትዕግስት
ለ// እምነት
ሐ// ደስታ
መ// ፍቅር

✅መ

1⃣3⃣ቤተ ክርስቲያን ስንል ምን ማለታችን ነው❓
ሀ// የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ የሚፈተትባት ቦታ
ለ// የክርስቲያኖች ኅብረት
ሐ// እያንዳንዱ ክርስቲያን የተባለ ወገን
መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣4⃣✏ ጌታችን አምላክነቱን በደብረ ታቦር በገለጠ ወቅት ሙሴ እና ኤልያስ ያነጋግሩት ነበር ሙሴና ኤልያስ በምድር ላይ በነበሩበት ወቅት ሁለቱም ከእግዚአብሔር ጋር የተነጋገሩበት ተራራ የትኛው ነበር❓
ሀ// የታቦር ተራራ
ለ// የሞርያ
ሐ// ኮሬብ(የሲና ተራራ)
መ// የአራራ ተራራ

✅ሐ

1⃣5⃣✏ከሚከተሉት የመዝሙር ንዋያተ ቅዱሳት የእመቤታችን ምሳሌ የሚሆነው የትኛው ነው ❓
ሀ// ጸናጽል
ለ// በገና
ሐ// መሰንቆ
መ// ከበሮ

✅ሐ

1⃣6⃣✏ከዐራቱ ወንጌላውያን በስዕሉ ላይ አንበሳ ከጎኑ ሆኖ የሚሳለው ማን ነው❓
ሀ// ቅዱስ ማቴዎስ
ለ// ቅዱስ ማርቆስ
ሐ// ቅዱስ ሉቃስ
መ// ቅዱስ ዮሐንስ

✅ለ

1⃣7⃣✏ቤተ ክርስቲያንን የትኛው ይገልጻታል❓
ሀ// የድህነት መርከብ
ለ// የክርስቶስ ሙሽራ
ሐ// የክርስቶስ አካል
መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅መ

1⃣8⃣✏ተመሳሳይ (ሲኖፕቲክ) ወንጌል በመባል የሚታወቁት የትኞቹ ናቸው ❓
ሀ// የማቴዎስ ፣ማርቆስ እና ዮሐንስ ወንጌል
ለ// የማቴዎስ ፣ማርቆስ እና ሉቃስ ወንጌል
ሐ// የማርቆስ ፣ ሉቃስ እና ዮሐንስ ወንጌል
መ// የማቴዎስ እና የዮሐንስ ወንጌል

✅ለ

1⃣9⃣✏ሚስጢረ ሜሮን .....❓
ሀ// ድህነት ያገኘንበት ምስጢር ነው
ለ// ይቅርታ ነው
ሐ// የመንፈስ ቅዱስ ማህተም ነው
መ// ከሥጋ ደዌ የምንድንበት ሚስጢር

✅ሐ

2⃣0⃣የፍጥረት መጀመሪያ ዕለት ማን ናት❓
ሀ// ሰኞ
ለ// ማክሰኞ
ሐ// ዓርብ
መ// እሁድ

saramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት የ43ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ውድድር

https://youtu.be/jY1O9jzyS_I
✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
@Teyakaenamels
የ2011 ዓ.ም የምዕራፍ አምስት(፭) የ43ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻
@ምንጭ 👉420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ
🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻🌻

1⃣🖊ከሚከተሉት ውስጥ ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢራት የማይመደበው የትኛው ነው?

ሀ/ምሥጢረ ሥላሴ
ለ/ምሥጢረ ጥምቀት
ሐ/ምሥጢረ ሜሮን
መ/ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን

✅ሐ
2⃣🖊ስናማትብ ምን ማመላከታችን ነው??

ሀ/በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ማመናችን
ለ/አጋንንትን ማራቃችን
ሐ/ መስቀል አርማችን መሆኑን
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

3⃣🖊ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማይስማማ አገላለፅ የቱ ነው??

ሀ/የእግዚአብሔር አብ አንድያ ልጅ
ለ/ የሰው ልጅ
ሐ/የእግዚአብሔር ቃል
መ/ፍጡር

✅መ
4⃣🖊ከሐዋርያት መካከል "እንደ አምላኬ ሳይሆን ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ"  በማለት በሰማዕትነት ያለፈው ማን ነው?

ሀ/ቅዱስ ጳውሎስ
ለ/ቅዱስ ቶማስ
ሐ/ቅዱስ ጴጥሮስ
መ/ ቅዱስ ጢሞቴዎስ

✅ሐ
5⃣🖊ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ትክክል ያልሆነው አገላለፅ የቱ ነው?

ሀ/ሥላሴ በአካል ሦስት መሆናቸው
ለ/በአገዛዝ አንድ መሆናቸው
ሐ/ሥላሴ-በሕልውና ሦስት መሆናቸው
መ/በከዊን፦አብ ልብ፣ ወልድ ቃል፣ መንፈስ ቅዱስ እስትንፋስ መሆናቸው

✅ሐ
6⃣🖊ከሚከተሉት ውስጥ የማይደገመው የቤተ ክርስቲያን ምሥጢር የቱ ነው??

ሀ/ ጥምቀት
ለ/ሜሮን
ሐ/ተክሊል
መ/ሁሉም

✅መ

7⃣🖊የጌታችን ዐበይት በዓላት ስንት ናቸው?

ሀ/ 7
ለ/8
ሐ/9
መ/10

✅ሐ

8⃣🖊ከሚከተሉት ውስጥ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ያልሆነው የትኛው ነው?

ሀ/ፊትን ወደ ምሥራቅ አዙሮ መጸለይ
ለ/የቅዱሳንን አማላጅነት ማመን
ሐ/መንፈሳዊት በዓላትን ማክበር
መ/መልስ አልተሰጠም

✅መ

9⃣🖊መዳንና ጽድቅ የሚገኘው .?

ሀ/በእምነት ብቻ ነው
ለ/በበጎ ተግባር ብቻ ነው
ሐ/በእምነትና በበጎ ተግባር ነው
መ/መልስ የለም

✅ሐ

🔟🖊የቤተክርስቲያንናችን ትምህርት የሆነው የትኛው ነው?

ሀ/እግዚአብሔር አንድም ሦስትም ነው
ለ/መንፈስ ቅዱስ የሰረጸ ከአብ ብቻ ነው
ሐ/እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአምላክ እናት ናት
መ/ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

1⃣1⃣🖊ሦስቱ የክህነት ደረጃዎች የትኞቹ ናቸው??

ሀ/ኤጲስ ቆጶስ፣ቄስ፣ዲያቆን
ለ/ፓትርያርክ፣ሊቀ ጳጳስ፣ቆሞስ
ሐ/የነፍስ አባት፣የንስሀ አባት፣ ቄስ ገበዝ
መ/መልስ የለም

✅ሀ
1⃣2⃣🖊ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት "ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሒድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ የሚለን ለምንድን ነው??

ሀ/ የማያውቁንና የምናውቃቸው ሰዎች ቤተክርስቲያን መሔዳችንን አውቀው እንዲያመሰግኑ
ለ/ የጠፉ ዘመዶቻችን ስለምናገኝ
ሐ/አብሮ መዘመሩ ስለሚያስደስተንና የመዝሙር ፍላጎታችን ስለምናረካ
መ/በዐይን በሚታይና በጀሮ በሚሰማ የአምልኮት እግዚአብሔር አገልግሎት አማካይነት በዐይን የማይታይና በእጅ የማይዳሰስ የእግዚአብሔርን ጸጋ ስለምናገኝ

✅መ

1⃣3⃣🖊በቤተክርስቲያን ላይ በሚተከለው መስቀል ላይ የሚቀመጠው ምንድን ነው??

ሀ/የዓሳ ምልክት
ለ/የሰጎን እንቁላል
ሐ/የጦር ምልክት
መ/ምንም አይቀመጥም

✅ለ

1⃣4⃣🖊መንበረ መንግስት ስንት ስም አሏት

ሀ/1
ለ/ 2
ሐ/4
መ/3

✅መ

1⃣5⃣🖊ቅዱሳን መላእክ____?

ሀ/ይራዱናል
ለ/ይጠብቁናል
ሐ/ያማልዱናል
መ/ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ
1⃣6⃣🖊በቀን ውስጥ የታወቁት የጸሎት ጊዚያት ስንት ናቸው??

ሀ/1
ለ/3
ሐ/5
መ/7
✅መ
1⃣7⃣🖊የቤተ ክርስቲያን የታሪክ ምንጮች የሆኑት የትኞቹ ናቸው??

ሀ/የብሉይ ኪዳንና የሐዲስክ ኪዳን መጽሐፍት
ለ/በየጊዜው የተደረጉ የቤተክርስቲያን ጉባኤዎችና ውሳኔዎች
ሐ/የቤተ ክርስቲያን አባቶች የጻፏቸው የታሪክ መጽሐፍት
መ/ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

1⃣8⃣🖊ስለ ቤተ ክርስቲያን ትክክል ያልሆነው አባባል የትኛው ነው?

ሀ/ቤተ ክርስቲያን አንዲት፣ቅድስት፣ዓለም አቀፋዊትና ሐዋርያዊት ናት።
ለ/የቤተ ክርስቲያን መሪ መንፈስ ቅዱስ ነው
ሐ/የክርስቲያኖች ህብረት ቤተ ክርስቲያን ይባላል
መ/መልስ አልተሰጠም
✅መ
1⃣9⃣🖊ከሰባቱ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን የማይመደበው የቱ ነው??

ሀ/ ጥምቀት
ለ/ተክሊል
ሐ/ቀንዲል
መ/ትንሳዔ ሙታን

✅መ

2⃣0⃣🖊ከሚከተሉት የቅዱሳት ሥዕላት ጥቅም የትኛው ነው?

ሀ/ለትምህርት
ለ/ለጸሎት
ሐ/ለተግሣጽ
መ/ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

saramareyama.890@gmail.com

ማክሰኞ 25 ሴፕቴምበር 2018

እንኳን ለብርሀነ መስቀሉ አደረሳችሁ አደረሰን

#መስቀሉ_አበራ

እዮሐ አበባዬ    መስከረም ጠባዬ (2)
መስከረም ሲጠባ ተተክሎ ደመራ
ህዝበ ኢትዮጵያን እዩት ችቦውን ሲያበራ
በታላቁ ብርሃን በመስቀል ደመራ (2)

#በኃጢአት_ጨለማ  አበራ መስቀሉ  ለእኛ አበራ
#ተውጠን_ሳለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የክርስቶስ_መስቀል  አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ብርሃን_ሆነልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ትምህርተ_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሆኖን_ላመንነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በቃሉ_ለምንድን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የእግዚአብሔር_ኃይል_ነው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል ባንዲራችን
   የነጻነት አርማችን (2)

#በኢየሩሳሌም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አይሁድ_አብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ያዳናቸውን_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አናውቅም_ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የድሉን_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ከመሬት_ቀብረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስሏቸው_ነበር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ውጦ_የሚያስቀረው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በቀራንዮ ጎልጎታ
   ጠላታችን ድል ተመታ (2)

#ንግሥቲቷ_እሌኒ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በጣም_የታደለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ደመራን_አቁማ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ፍለጋ_ጀመረች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀለ_ክርስቶስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ወዴት_ነው_እያለች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በጣን_ጢስ_ተመርታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀሉን_አገኘች አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል መከታ
   ቆስጠንጢኖስ ድል ተመታ (2)

#ነገር_ግን_መስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተቀብሮ_አልቀረም አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተራራ_አፍርሶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጠላት_አሳፈረ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል_ሲወጣ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ታላቅ_ሁካታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ድውይ_ሲፈወስ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አንካሳው_ዳነ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሙታን_ተነሱ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይመስገን_ጌታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ
    ክርስቲያኖች እልል በሉ (2)

#መስቀል_መከታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይሁን_ጋሻችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እንዳይደፈር_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ዳር_ድንበራችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኢትዮጵያ_ኑሪ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእምነት_ፀንተሽ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጌታ_በመስቀል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የባረከሽ_አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀሉ አበራ
    እንደ ፀሀይ ጮራ (2)

#መስቀሉን_አምነን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተሳልመነዋል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ከክብሩ_ዙፋን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእርሱ_ባርኮናል አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እንሰግድለታለን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የፀጋ_ስግደት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በእርሱ_ላይ_ስላለ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኃይለ_መለኮት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል የእኛ ጋሻ
    የዲያብሎስ ድል መንሻ (2)

#የኢትዮጵያን መኩሪያ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኑ_ተመልከቱልን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የመስቀሉን_ብርሃን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ነፀብራቁን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#እፀ_መስቀሉ _ው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የእኛ_መከታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የተሰጠን_ለእኛ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ምልክታችን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

በመስቀል እንመካለን
    እንድንበታለን (2)

#የዳዊት ልጅ ያዕቆብ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የሀገራችን ኩራት አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የኢትዮጵያ ንጉሥ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጌታን የሚፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሀገሪቱን ሲዞር አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ድካሙን ሳይፈራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል ተሸክሞ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ብርሐን እያበራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ፍቅር
   በእኛ ላይ ይደር (2)

#መናገሻ_እንጦጦ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የረር አምባ አመራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ሲፈለግ_ሰንብቶ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የመስቀል_ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ጊሸን ላይ አገኘ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የአምባሰል_ተራራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ግማደ_መስቀሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አርፏል_ከዚያ_ስፍራ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

መስቀል መስቀላችን
   የክርስቲያን ኃይላችን (2)

#የመስቀል_ለታ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#የደመራው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ኢትዮጵያውያን አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተደስተው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በሀገር_ልብሳቸው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#አምረው_ደምቀው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#በአደባባዩ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ተሰብስበው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#ይዘምራሉ አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ
#መስቀል_ብለው አበራ መስቀሉ ለእኛ አበራ

የመስቀሉ ደመራ
    በኢትዮጵያ ሲያበራ (2)
Watch "የመስቀል ኮሌክሽን መዝሙሮች" on YouTube
https://youtu.be/_YnPAwv1sZE

እሑድ 23 ሴፕቴምበር 2018

መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
@Teyakaenamels
@Teyakaenamels

1ኛ) አምሥቱ(5) አዕማደ ምስጢር የሚባሉት ምን ምን ናቸው?  መልስ፦  ሚስጥረ ሥላሴ
ሚስጥረ ስጋዌ
ሚስጥረ ጥምቀት
ሚስጥረ ቁርባን
ሚስጥረ ትንሳኤ ሙታን ናቸው።
2ኛ) ቤተ ክርስቲያን ስንት ባህሪ አሏት? መልስ፦ቤተ ክርስቲያን  4 ባህሪ አሏት እነሱም 1ኛ፦ በመጀመርያ ቤተ ክርስቲያን አንዲት ነች።
2ኛ፦ ቤተ ክርስቲያን ቅድስት ነች።
3ኛ፦ቤተክርስቲያን ኩሉውይት ነች።
4ኛ፦ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያት ነች ማለት ነው።
3ኛ) እናታችን ቅድስት አርሴማ  ሰይፍ  ከአረፈባተ በኋላ ለስንት ስዓት ቆመች? የናታችን የአርሴማ ሃገርስ የት ነው? መልስ፦ እናታችን ቅድስት አርሴማ ሰይፍ ከአረፈባት በኋላ ለ3 ስዓት ቁማለች ሃገሯ ደግሞ አርመንያ ነው።
4ኛ)  የእመቤታችን በዓላት ስንት ናቸው? መልስ፦  33 ናቸው።
5ኛ) ማርያም ፊደል የሚለውን ቃል የተናገሩት አባት ማን ናቸው (ማን) ይባላሉ? መልስ፦ አባታችን አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ናቸው።
6ኛ) ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ክርስትና የተመለሰው ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እርገት በኋላ በስንተኛው አመት ነው?  መልስ፦በ8ኛ አመቱ ነው።
7ኛ) መጽሐፍ ነገስት በስንት ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል? መልስ፦በ3 ዋና ዋና ክፍሎች ይከፈላል።
8ኛ) ዜና መዋል ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦ የእለት ዜና ማለት ነው።
9ኛ) ምናሴ ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  ማስረሻ ማለት ነው።
10ኛ)መስፍን ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  ፈራጅ፤ አስተዳዳሪ ማለት ነው።
11ኛ) ቅዱስ ጊዮርጊስ ከዘንዶ አፍ ያዳናት ልጅ ስማ ማን ትባላለች? መልስ፦ ብሩክታይት ትባላለች።
12ኛ) አኬልዳማ ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦  የደም መሬት ማለት ነው።
13ኛ) ፃዲቁ አባታችን አቡነ አረጋዊ በስንት አመተ ምህረት ወደ ኢትዮጵያ ገቡ? መልስ፦  በ480 ዓ.ም ነው።
14ኛ ከነአን የምን ምሳሌ ናት?መልስ፦የመንግስተ ሰማያት ምሳሌ ናት።
15ኛ) ላንች የማይገዛ ህዝብና መንግስት ይጠፋል። ይህን ሃይለ ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኛዋለን? ምዕራፍና ቁጥሩን? መልስ፦ኢ.ሳ 60፥12 ላይ ነው።
16ኛ)በጨረቃ በከዋክብት ላይ ስልጣን የተሰጠው መላክ ማን ነው? መልስ፦ ቅዱስ ሩፋኤል ነው።
17ኛ) ቁርባን ማለት ምን ማለት ነው? መልስ፦ በሱርስት ቋንቋ መባ፤ስጦታ ማለት ነው።
18ኛ) ደስታ በስንት ይከፈላል? መልስ፦ ደስታ በሁለት(2) ይከፈላል መንፈሳዊ ደስታ እና ሥጋዊ ደስታ ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyama.890@gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭) የ42ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፫

የምዕራፍ (፭)/የ42ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃልና የጹህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር⤵

@ምንጭ ማኅበረ ቅዱሳን 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ⤵

ማጠቃለያ መልስ🖊
➡1⃣ዮሴፍ የሚባል አንድ ሌዋዌ በሐዋርያት አጠራር ትርጉሙ "የመጽናናት ልጅ" የሚሆን ስም ተሰጠው። የዚህ ሐዋርያ ስም ማን ነው?

ሀ. ፋሮስ
ለ.እስክንድሮስ
ሐ.አጵሎስ
መ. በርናባስ

✅መ

➡2⃣"ጌታ ሆይ በኢየሩሳሌም በቅዱሳንህ ላይ ስንት ክፉ ነገር እንዳደረገ ስለዚህ ሰው ከብዙዎቹ ሰምቻለሁ። በዚህም ስምህን የሚጠሩትን ሁሉ ለማሰር ከካህናት አለቆች ሥልጣን አለው።" ተብሎ የተነገረው ስለ ማን ነው?

ሀ. ሐናንያ
ለ.ስምዖን
ሐ.ሳውል
መ.በርስያስን

✅ሐ

➡3⃣የሞት አያት ማን ነው?

ሀ. ኃጢአት
ለ.ተንኮል
ሐ.ምኞት
መ.ቁጣ

✅ለ

➡4⃣አጋቦስ ይባል የነበረው ነቢይ ከኢየሩሳሌም ወደ አንጾኪያ በመውረድ ምን ተነበየ?

ሀ. ቅዱስ ጳውሎስ እንደሚታሰር
ለ. በምድር ላይ ራብ እንደሚመጣ
ሐ. ኢየሩሳሌም በሮማውያን ወታደሮች ፈጽማ እንደምትጠፋ
መ.ክርስትና በዓለም እንደሚሰበክ

✅ለ

➡5⃣አይሁድን ደስ ያሰኝ ዘንድ በክርስቲያኖች ዘንድ መከራን ያጸናው ንጉሥ ማን ነው?

ሀ. ሄሮድስ አንቲጳስ
ለ. ሄሮድስ ቀዳማዊ አግሪጳ
ሐ.ሄሮድስ ዳግማዊ አግሪጳ
መ.ጲላጦስ

✅ሐ

➡6⃣ከናዝሬት መልካም ነገር ሊወጣ ይችላልን?" ያለው ሐዋርያ ማን ነው?

ሀ.ፊሊጶስ
ለ.ታዴዎስ
ሐ.ቶማስ
መ.ናትናኤል

✅መ

➡7⃣ከሐዋርያት መካከል  አስቀድሞ "አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ነህ" ብሎ የተናገረው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ. ቅዱስ ቶማስ
ሐ.ቅዱስ ናትናኤል
መ. ቅዱስ ፊልጶስ

✅ሀ

➡8⃣በሁለተኛው የቅዱስ ጳውሎስ ሐዋርያዊ ጉዞ ላይ አብሮ የነበረው ማን ነው?

ሀ.አቂላስ
ለ.ሲላስ
ሐ.ጵርስቅላ
መ.በርናባስ

✅ሐ

➡9⃣በሕልሙ የመቄዶንያ ሰው ለእርዳታ ሲጠራው ያየው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጳውሎስ
ለ.ቅዱስ ቲቶ
ሐ.ቅዱስ ሉቃስ
መ.ቅዱስ ጋይዮስ

✅ሀ

➡🔟ቅዱስ ጳውሎስ በአንድ ከተማ በሚመላለስበት ወቅት ሰዎች "ለማይታወቅ አምላክ" ብለው ጽፈው በመመልከቱ በማዘን ትምህርት አስተምሯቸዋል።
ከተማው የትኛው ነበር?

ሀ. ተሰሎንቄ
ለ.ቆሮንቶስ
ሐ.ኤፌሶን
መ.አቴና

✅መ

➡1⃣1⃣ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር አብረው ድንኳን ይሰፉ የነበሩት ማንና ማን ናቸው?

ሀ.ሲላስ እና ጢሞቴዎስ
ለ.አጵሎስ እና በርናባስ
ሐ. አቂላ እና ጵርስቅላ
መ.ማርቆስ እና ሉቃስ

✅ለ

➡1⃣2⃣ቅዱስ ጳውሎስ ለፊልሞና በጻፈው መልእክቱ ማንን ይቅር እንዲል መክሮታል?

ሀ. አገልጋዩ ግያዝን
ለ.ውሸተኞች ወንድምችን
ሐ. አገልጋዩ አናሲሞስን
መ.መልስ የለም

✅ሐ

➡1⃣3⃣የክፋት ሁሉ ሥር ምንድን ነው?

ሀ. ትዕቢት
ለ.ቁጣ
ሐ.ዝሙት
መ.ገንዘብን መውደድ

✅መ

➡1⃣4⃣የልስጥራን ሰዎች ሁለት ሐዋርያትን ድያ እና ሄርሜን በማለት በአማልክቶቻቸው ስም ሰይመዋቸዋል። ሐዋርያቱ እነማን ነበሩ?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ዮሐንስ
ለ.ቅዱስ ጢሞቴዎስ እና ቅዱስ ቲቶ
ሐ. ቅዱስ እንድርያስ እና ቅዱስ ታዴዎስ
መ.ቅዱስ በርናባስ እና ቅዱስ ጳውሎስ

✅መ

➡1⃣5⃣ከሐዋ መካከል በሰማዕትነት ያላለፈው ማን ነው?

ሀ. ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ.ቅዱስ ያዕቆብ
ሐ. ቅዱስ እንድርያስ
መ.ቅዱስ ዮሐንስ

✅መ

➡1⃣6⃣ቅዱስ ጳውሎስ "የእግዚአብሔር ጦር ዕቃ ብሎ የሰየመው የትኛውን ነው?

ሀ. የእውነትን ቀበቶ
ለ.ለእግዚአብሔር ቃል
ሐ.የእምነት ጋሻ
መ. ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

➡1⃣7⃣በሐዋርያት ስም ዝርዝር የመጀመሪያውን ቦታ ይዞ የሚገኘው ማን?

ሀ. ቅዱስ እንድርያስ
ለ.ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐ. ቅዱስ ጳውሎስ
መ. ቅዱስ ፊልጶስ

✅ለ

➡1⃣8⃣ዐበይት ነቢያት የሚባሉት ማን ማን ናቸው?

✅ኢሳያስ፣ ኤርምያስ፣ሕዝቅኤልና ዳንኤል  ናቸው።

➡1⃣9⃣ የተራራው ሥብከት ዐሥሩ ዐበይት ክፍሎች ማን ማን ናቸው??

✅ክፍል አንድ፦ ስለ አንቀጸ ብፁዓን/ማቴ 5፥3-12/

ክፍል ሁለት፦ስለ አንቀጸ ምግባር/ማቴ 5፥13-16

ክፍል ሦስት፦አጽንኦተ ሕግ/ማቴ 5፥17-48

ክፍል አራት፦ ሦስቱ አናቅጸ ምግባራት/ ማቴ 6፥1-8

ክፍል አምስት፦እግዚአብሔርን ማስቀደም እንዲገባ/ማቴ 6፥19-34

ክፍል ስድስት፦ አትፍረዱ/ማቴ.7፥1-6

ክፍል ሰባት፦ እንድንጸልይ መታዘዛችን/ ማቴ.7፥7-12

ክፍል ስምንት፦ቀጭን መንገድ በጠባቡ በር/ማቴ. 7፥13-14

ክፍል ዘጠኝ፦ መልካም ፍሬ ከመልካም ዛፍ/ ማቴ.7፥15-20

ክፍል አስር፦ ጽድቅ በተአምራት ሳይሆን በሥራ ስለመሆኑ/ማቴ 7፥21-29

➡2⃣0⃣በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ በገና፣ዋሽን፣ጸናጽል፣ከበሮ፣እምቢልታ፣ ነጋሪት፣መለከት፣ መሰንቆ ተጽፎ የምናገኘው በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው?

✅በገና፣መሰንቆ፣ነጋሪት፣ጽናጽል 2ኛ.ሳሙ 6፥5
ዋሽንት፣ክራር ት.ዳ. 3፥5/ ዘፍ.4፥21/ከበሮ፣እንቢልታ/ኢሳ.5፥12/ዘዳ.15፥20/መለከት/1ኛ.ነገስት 1፥40/

ወስብሀት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን!saramareyama.890@gmail.com

የመስቀል መዝሙሮች !

ያሬዳዊ መዝሙሮች:
©✝መዝሙር በእንተ መስቀሉ ለእግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ©⤵️

©ይቤሎሙ ኢየሱስ

ይቤሎሙ ኢየሱስ/፪/ለአይሁድ/፪/
እመኑ ብየ ወእመኑ በአቡየ አበርህ በመስቀልየ ለእሊአ /፪/
#ወረብ


©ያሬድ ካህን
ያሬድ ካህን /፪/ ፀሐያ ለቤተክርስቲያን/፪/
አሰርገዋ ለኢትዮጵያ በስብሐት ወበሃሌ  ሉያ/፪/

#ዮምሰ
ዮምሰ ለእሊአየ /፪/
አበርህ በመስቀልየ/፬/

      #ወረብ

©ቤተ ክርስቲያን ርእየቶ

ቤተ ክርስቲያን ርእየቶ ቅንወ ለዘበጎልጎታ ደሙ ተክዕወ/፪/
ከመ እግረ ፀሐይ ሥኑ ኀተወ በዓለ መስቀል ዘዮም ትገብር ህልወ/፪/
ትርጉም:- በጎልጎታ ደሙ የፈሰሰውን አምላክ ቤተ ክርሲያን አየችው ደም ግባቱም እንደ ፀሐይ አውታር(ጮራ) አበራ የዛሬው የመስቀል በዓልም ለዘለዓለም ታበራለች

©መስቀሉሰ

መስቀሉሰ ለክርስቶሰ ብርሃን ነአምን ትብሌ ቤቴ ክርስቲያን/፪/
ዛህኑ ለባሕር ወመርሶ ለአሕማር ዝንቱ ውእቱ መስቀል/፪/
ትርጉም:-የክርስቶስ መስቀል ለመናምን ሰዎች ብርሃን ነው መስቀል የባሕር ፀጥታው የመርከቦች ወደብ ነው ትላለች ቤተ ክርስቲያን

©መርሕ ለፍኖት

ሃሌ ሉያ መርሕ ለፍኖት ሞገሶሙ ለጻድቃን ሞገስ/2/
ዝንቱ መስቀል ለአዳም ዘአግብኦ ውስተ ገነት/2/
ሃሌ ሉያ መሪ ነው በመንገድ ሞገሳቸው ለጻድቃን ሞገስ/2/
ይኸ መስቀል ነው አዳምን የመለሰው ወደ ገነት/2/

©ብከ ንወግዖሙ

ብከ ንወግዖሙ ለኵሎሙ ፀርነ/፪/ ይቤ ዳዊት በመንፈሰ ትንቢት/፪/
በእንተ ዝንቱ  ዕፀ መስቀል ዘተሰቅለ ዲቤሁ ቃለ አብ /፪/

ትርጉም፡- ቅዱስ ዳዊት በትንቢት መንፈስ እንዲህ አለ፣ በአንተ
ጠላቶቻችንን እንወጋቸዋለን፤ በዚህ የእግዚአብሔር ቃል/ኢየሱስ ክርስቶስ/ በተሰቀለበት፡፡
©ትቤሎ እሌኒ

ትቤሎ እሌኒ ለኪራኮስ ንግረኒ አፍጥን /፪/
ኀበ ሀሎ መስቀሉ ለኢየሱስ/፪/ ክርስቶስ /፬/

ትርጉም፡- ዕሌኒ ኪራኮስን የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል
የት እንዳለ ፈጥነህ  ንገረኝ አለችው፡፡

©መስቀል አብርሃ

መስቀል አብርሃ በከዋክብት አሰርገወ ኢትዮጵያ/፪/
እምኩሉሰ ፀሐየ አርአየ ዕፀ መስቀል/፪/

ትርጉም፡- መስቀል አበራ ኢትዮጵያንም  በከዋክብት ሸለመ
 ከሁሉ ይልቅ መስቀል እንደ ፀሐይ ደምቆ/በርቶ/ ታየ፡፡

©ለዕፀ መስቀል

ርእዩ ዕበዮ ለዕፀ መስቀል /፪/
ዘመጠነዝ/፪/ትርሢተ ክብር ትህትና ወፍቅር /፪/

ትርጉም፡-የዕፀ መስቀሉን ክብሩን ትህትናውን ፍቅሩን ሽልማቱን     
ምን ህል እንደሆነ እዩና አድንቁ ወይም ከፍ ከፍ አድርጉት፡፡

  ©ርእዩ ዕበዮ
ርእዩ ዕበዮ ለቅዱስ ዕፀ መስቀል /፪/
ዕውራን ይሬእዩ ወጽሙማን ይሰምዑ እለ ለምጽ 
ይነጽሑ እለ መጽኡ ኀቤሁ /፪/

ኑ እዩ የመስቀሉን ተአምራት /፪/
እውሮች ያያሉ ደንቆሮዎች
ይሰማሉ ለምጻሞችም           
ይነጻሉ ወደ እርሱ የመጡ ሁሉ /፪/

©ዮም መስቀል

ዮም መስቀል አስተርአየ እለ ማሰነ ፍጥረተ አሠነየ/፪/
ዮም መስቀል ተኬነወ ወዘተጼወወ ሕዝበ በደሙ ቤዘወ/፪/

ትርጉም፡-ዛሬ መስቀል ተገለጠ የጠፉትን ሰዎች አዳነ ዛሬ
መስቀልብልሃተኛ ሆነ ምርኮኞች ወገኖቹንም
በክርስቶስ ደም አዳነ፡፡

©ወበእንተዝ

ወበእንተዝ አዘዙነ መምህራነ ቅዱስ ወንጌል/፪/
ንስግድ ለመስቀል ወለማርያም ድንግል/፬/

ትርጉም፡- ቅዱስ ወንጌልን የሚያስተምሩ መምህራን
ለመስቀልና  ለድንግል ማርያም እንድንሰግድ ያዝዙናል፡፡

©ሀብሩ ቃለ

ሀብሩ ቃለ ነቢያተ/፪/
ወይቤሉ መስቀል ብርሃን/፪/ ለኵሉ ዓለም /፪/

ትርጉም፡-ነቢያት መስቀል ለዓለም ሁሉ ብርሃን ነው
ብለው በአንድ ቃል  ሆነው  ተናገሩ፡፡

© ኀበ ቀራንዮ

ኅበ ቀራንዮ ደብረ መድኃኒት/2/
ቀራንዮ/2/ ኀበ ቀራንዮ/2/
የመስቀሉ ቃል ለእኛ የእግዚአብሔር ኃይል ነው/4/
ለማያምኑት ሞኝነት ነው ለእኛ ግን ሕይወት ነው/2/
እንመሰክራለን ፈጣሪያችን አለ/4/
እንመነው አንካደው ፈጣሪያችን ቸር ነው/2/
እንመሰክራለን ድንግል አማላጅ ናት/2/
እንመሰክራለን ማርያም  አማላጅ ናት/4/
እንመናት አንካዳት የአምላክ እናት ናት/2/
ኅበ ጥበባት ኀበ ልሳናት/4/
ዮሐንስ/2/ ወንጌለ ስብከት/2/

#በመስቀሉ #ቤዘወነ

በመስቀሉ ቤዘወነ ወበደሙ ተሰሃለነ/2/
አምላከ ምሕረት ውእቱ መድኃኒነ
አምላከ ምሕረት ውእቱ
በመስቀሉ ቤዛ ሆነን ሞትን ሽሮ ከሞት አዳነን/2/
የምሕረት ጌታ ነውና ይቅር አለን
የምሕረት ጌታ ነውና

#ብርሃን ወጣ

ብርሃን ወጣ ከመስቀሉ የሚያንጸባርቅ
የአምላክ እና የሰው ልጆች እውነተኛ እርቅ
ደስ ይበለን በመስቀሉ ብርሃን
እልል እንበል በአንድነት ሆነን
ተነሳልን መድኃኒታችን

ከፊት ለፊት በመሳሉ የመስቀሉ ነገር
የሚወደው ሐዋርያ የወንጌል መምህር
ዮሐንስም ስቅለቱን በማየቱ
ሲያዝን ኖረ በምድራዊ ሕይወቱ
ቢያሰቅቀው ሞቱ ግርፋቱ

ሞኝነት ነው ለሚጠፉት መሰናከያቸው
በዓለም ጥበብ ለሚኖሩት እውነት ተሰኗቸው
ለጠቢብ ሰው በመንፈስ ለሚኖረው
የመዳን ቀን እውነተኛ ዓርማ ነው
ከገሀነም እሳት የሚያድን ነው

እስከመስቀል ላልተለየው ቅዱስ ሐዋርያ
ለዮሐንስ ለወንጌል ሰው የፍቅር ባለሞያ
ምስጋናችን በምድር ይድረሰው
እንድናለን በሰጠው ምሳሌው
ሰዎች ሁሉ

#ኧኸ #በመስቀልከ

ኧኸ በመስቀልከ ኧኸ ጽልመተ አብራህከ
ኧኸ በመስቀልከ ኧኸ ሙታነ  አንሣእከ/፪/
ኧኸ ወዘተዓጉለ ረዳእከ በመስቀልከ/፪/
ትርጉም:-በመስቀልህ ጨለማን አበራህ ሙታንንም አነሣህ የጠፋውንም በመስቀልህ ረዳኸው/አዳንኸው/።

#በኃይለ #መስቀሉ

 በኃይለ  መስቀሉ/2/ይዕቀበነ
በኃይለ መስቀሉ /3/  ይዕቀበነ/2/


      #©መስቀል #ብርሃነ
መስቀል ብርሃነ ለኲሉ ዓለም
መሠረተ ለቤተክርስቲያን/2/

ወሀቤ ሰላም መድኃኔዓለም መስቀል
መድኅን ለእለ ነአምን/2/

መስቀል ብርሃን ነው ለመላው  ዓለም
መሠረተ ነው ለቤተክርስቲያን/2/
ሰላምን ሰጪ ነው መድኃኔዓለም መስቀል
አዳኝ ነው ለኛ ለምናምን /2/

        #©አለው #ሞገስ
አለው አለው ሞገስ  ኧኸ  አለው ሞገስ
የመስቀል በአል ሲደርስ ኧኸ  አለው ሞገስ
አለው አለው አበባ  ኧኸ  አለው አበባ
የመስቀል በዓል ሲገባ  ኧኸ አለው አበባ
አለው አለው ደስታ  ኧኸ አለው ደስታ
መስቀል ሲከብር በእልልታ  ኧኸ አለው ደስታ
አለው አለው ሰላም ኧኸ አለዉ ሰላም
መስቀል ሲታይ በአለም  ኧኸ አለው ሰላም
አለው አለው አለኝታ  ኧኸ አለን አለኝታ
እፀመስቀል መከታ  ኧኧ አለን አለኝታ
እዩት እዩት ሲያበራ  ኧኸ እዪት ሲያምር
የመስቀል በዓል ደመራ  ኧኸ እዪት ሲያበራ
እዪት እዩት ሲያምር  ኧኸ እዩት ሲያም
መስቀል በዓለም ሲከብር  ኧኸ እዪት ሲያምር


   #©አየኸው #ደመራ
አየኸው ደመራ መስቀል ሲያበራ/2/
መስቀል አለ ወይ ቆሟል ወይ
አለእንጂ ለምጽ ያነጻል እንጂ
ያው ቆሟል ድውይ ይፈውሳል
      አምነዋለሁ የት አገኘዋለሁ
አለልሽ እሰሪው በአንገትሽ
ከልብሽ ተሳለሚው አምነሽ
      እኮራለሁ በእፀ መስቀል
ይፈውሳል ሙታንን ያስነሳል
ድል ያደርገል ድውይ ይፈውሳል


#©ዕሌኒ #ንግስት
እሌኒ ንግሥት ሐሠሠት መስቀሉ/2/ኧኸ
ዕንባቆም ነቢይ ዘአንከረ ክብሩ/4/
ትርጉም=ዕሌኒ ንግሰት መስቀሉን ፈለገች
ነቢይ እንባቆም የጌታችንን ሥራ አደነቀ።


    #©እንተ ተሐንፀት
እንተ ተሐንፀት በስሙ ወተቀደሰት
በደሙ ቤተክርስቲያን/2/
ወተአትበት/2/ በዕፀ መስቀሉ
እስመ ኃይለ እግዚአብሔር ላዕሌሃ/2/
ትርጉም=በስሙ የታነፀች በደሙ የቀደሳት በዕፀ መስቀሉ የተባረከች ቤተክርስቲያን የእግዚአብሔር ሀይል በላይዋ አለ።

  #©ከመትባርከነ
ከምትባርከነ በስቀልከ ክቡር/2/
ከመ ይኲን ቤዛ/2/ ለኩሉ አsaramareyama.890@gmail.com

እሑድ 9 ሴፕቴምበር 2018

እንኳን ለዐዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ! የዐውድ ዓመት መዝሙሮች

​​🌼#የእንቁጣጣሽ #መዝሙር🌼
                  🌼🌼♥♥♥♥♥♥

እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ዮሐንስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ

      ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
      ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን

አበባዮሽ 🌼 ለምለም   አበባዮሽ 🌼  ለምለም
እንቆቅልሽ   - -  ንግሥት   ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - -  ንግሥት   እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን -  ንግሥት   አጫወታቸው - -   ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼  ንግሥት  እያሳየችው - -    ንግሥት
መአዛው የሚሸት  - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - -  ለንጉሥ 

          ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
      🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ

እንቆቅልሹ -  -  የሳባ    ከበድም ቢለው -  -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ  ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - -  ሰለሞን   ቢለው ለሎሌው  - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ  - -  ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ  - -   መለሠ     ለተጠየቀው - -  በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - -   አለ     አልተሠወረው      🌼     በእውነት

 🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት   ምስጋና አቅርባ - -   ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት   ንግስተ ሣባ   🌼   ንግሥት
ጥበቡን አይታ - -  ንግሥት   አደነቀችው  - -    ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - -  ንግሥት  ዕንቁ ሰጠችው - -   ንግሥት

      ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
      የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼

የኢትዮጵያ ሠዎች  - -ለንግሥት   ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው     🌼   ለንግሥት   ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - -  ለንግሥት   ሀገር ስትገባ - -  ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - -  ለንግሥት   የፈካ አበባ    🌼ለንግሥት

      🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
      🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼

ኢየሩሳሌም - - ንግሥት   ደርሠሽ መጣሽ - -  ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት   ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት  ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - -  ንግሥት   ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት

      🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
      🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼

🌼የአባቶች ተስፋ - -   ለፃድቃን   የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - -     ለፀሎት   የአሮን በትር  - -   ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት    ይዘሸ የመጣሽ - -   ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ   ለሀገር መሠረት -    በእውነት🌼🌼

 🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
      🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼

በህገ ልቦና  - -   ህጉን     ፈጣሪን አውቀሽ - -  ህጉን
ህገ ነቢያትን - -  ከዓለም  ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን   🌼ለጌታ    መስዋዕት አቅርበሽ - -  ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን-  -በፊት    ይዘሽ ተገኘሽ    🌼    በፊት

      🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
      🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼

ካለፈው ሰህተት - -  ሁላችን    እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት  - -  ለሁሉም   መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው    ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - -  በጊዜው    ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ  - -  በጊዜው  🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት -  -  በጊዜው   ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ  - -  መጥምቁ      ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼

      🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼

ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ    🌼     አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ 🌼እያለች እማማ      አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ    አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ     አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)🌼

 🌼አበባ ለምለም 🌼 ቀጤማ ለምለም
    🌼ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)🌼

አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ🌼
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
🌼
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)

      ከበረው ይቆዩ ከብረው 🌼
       አመት አወደ አመት ደርሰው
      ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
      ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
      የፍቅር ሸማን ለብሰው🌼
      ንስሐ ገብተው ቆርበው
  🌼ከብረው ይቆዩ ከብረው
         
               መዝሙር
      🌼በማህበረ ፊልጶስ🌼saramareyama.890@gmail.com

ሰኞ 27 ኦገስት 2018

የምዕራፍ ፭ የ41ኛ ዙር መንፈሳዊ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡አሜን!
`````````````
የምዕራፍ (፭) 41ኛ ዙር

በቤተክርስቲያን ታሪክ ላይ ለተዘጋጀው ጥያቄ እና መልስ መርሐ-ግብር ከአዘጋጁ አካል የማጠቃለያ መልሱ እንደሚከተለው ይቀርባል።
   ✝✝✝


1.የአዳም ሰባተኛ ትውልድ የትኛው ነው?
ሀ.አብርሃም
ለ.ሔኖክ
ሐ.ሙሴ
መ.ያዕቆብ

✔️ለ

2.ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት ዘመን እስራኤላውያን በተለያዪ ቡድኖች ተክፍለው ነበር።እነርሱም፡
ሀ.ሰማርያና ሴኬም
ለ.ሮማዊያን እና እስራኤላውያን
ሐ.ፈሪሳውያን፣ሰዱቃውያን እና ኤሲያውያን
መ.ሰሜን እና ደቡብ እስራኤል

✔️ሐ

3. የመጀመሪያዋ ሕንፃ ቤተ-ክርስቲያን የተሠራችው በየትኛዋ ከተማ ነበር?
ሀ.በፊሊጵስዩስ
ለ.በአንጾኪያ
ሐ.በደማስቆ
መ.መልሱ የለም

✔️ሀ

4.የሙሴን ሕግ በጥንቃቄ እንተረጉማለን ሚሉት የትኞቹ ናቸው?
ሀ.ፈሪሳውያን
ለ.ኤሲያውያን
ሐ.ሰዱቃውያን
መ.መልሱ አልተሰጠም

✔️ሀ

5.ሊቀ-ሐዋርያት ተብሎ ሚታወቀው ማን ነበር?
ሀ.ቅዱስ ቶማስ
ለ.ቅዱስ ዮሐንስ
ሐ.ቅዱስ ታዴዎስ
መ.መልሱ አልተሰጠም

✔️መ

6.ከቅዱሳት አንስት ወገን ያልሆኑት የትኞቹ ናቸው?
ሀ.ቅድስት ኤልሳቤጥ እና ቅድስት ሀና
ለ.ጤግላና ጲስ
ሐ.ጲላግያና መሪና
መ.መልሱ አልተሰጠም

✔️መ

7.ከምሥጢር ሐዋርያት መካከል ያልሆነ፡
ሀ.ዮሐንስ
ለ.ያዕቆብ-ወልደ ዘብዴዎስ
ሐ.ጴጥሮስ
መ.ያዕቆብ-ወልደ እልፍዮስ

✔️መ

8.«ይሁዳ»ማለት ምን ማለት ነው?
ሀ.ፍቁረ-እግዚእ
ለ.ዓለት
ሐ.በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው.
መ.ጸጋ የበዛለት ማለት ነው።

✔️ሀ

9.የኒቂያ ጉባኤ ሰብሳቢ ማን ነበር?
ሀ.ቄርሎስ
ለ.እለስክንድሮስ
ሐ.ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
መ.ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

✔️ለ

10.በቁስጥንጥንያው ጉባኤ ዋነኛው መናፍቅ ማን ነበር?
ሀ.ንስጥሮስ
ለ.መቅዶንዮስ
ሐ.አርዮስ
መ.አውጣቂ

✔️ለ

11.ከሚከተሉት የእስክንድርያ ሊቃነጳጳሳት መካከል«የቤተክርስቲያን ምሰሶ»ሚባለው ማን ነው?
ሀ.ቅዱስ እለስከንድሮስ
ለ.ቅዱስ ቄርሎስ ቀዳማዊ
ሐ.ቅዱስ አትናቴዎስ
መ.ቅዱስ ቄርሎስ 6ኛ

✔️ሐ

12.አቡነ ቄርርሎስ ቀዳማዊ ለእስክንድርያ ቤተ-ክርስቲያን በቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ ስንተኛው ፓትርያርክ ነው?
ሀ.12
ለ.23
ሐ.24
መ.32

✔️ሐ

13.በነገረ ሥጋዌ ላይ የ«እውነተኛ ተዋህዶ-Real Unification»ሚልን ቀመር ያዘጋጀ ማን ነበር?
ሀ.ቅዱስ ቄሮሎስ ቀዳማዊ
ለ.ቅዱስ አትናቴዎስ
ሐ.ጎርጎርዮስ ዘእንዚናንዙ
መ.መልሱ አልተሰጠም

✔️ሀ

14.የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አቡነ ባስልዮስ የምንኩስና(የቆብ) ስማቸው ማን ነበር?
ሀ.ንቡረእድ ገብረማርያም
ለ.እጨጌ ገብረጊዮርጊስ
ሐ.ፓትርያርክ ገብረእግዚአብሔር
መ.እጨጌ ተክለሃይማኖት

✔️ለ

15.ምንፍቅና የተጀመረው በማን ነበር?
ሀ.በሳጥናኤል
ለ.በይሁዳ
ሐ.በአርዮስ
መ.በዱዲያኖስ

✔️ሀ

16.በሐዋርያት ጊዜ የነበሩት የመጀመሪያዎቹ መናፍቃን እነማን ናቸው?
ሀ.ግኖስቲኮች
ለ.አርዮሳውያን
ሐ.ቢጽሐሳውያን
መ.ሁሉም ነበሩ

✔️ሐ

17.ፍልስፍና፣ጥንቆላ እና ምትሐታዊ ሕይወት የነበራቸው የትኞቹ ናቸው?
ሀ.ግሪኮች
ለ.ቢጽ ሐሳውያን
ሐ.ይሁዳውያን
መ.ግኖስቲኮች

✔️መ

18.የሶርያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርሲያን ቅጽል መጠሪያዋ ምንድን ነው?
ሀ.ጎርጎርዮሳዊት
ለ.ያዕቆባዊት
ሐ.እስጢፋኖሳዊት
መ.ማርቆሳዊት

✔️ለ

19.የመጀመሪያው የዓለም አብያተ-ክርስቲያናት ኅብረት ጉባኤ የተካሄደው የት ነበር?
ሀ.ኢቫንስተን-አሜሪካ
ለ.ናይሮቢ-ኪንያ
ሐ.ኤፕሳላ-ስዊድን
መ.አምስተርዳም-ሆላንድ

✔️መ

20.የመላው አፍሪካ አብያተ-ክርስቲያናት አንድነት ጽ/ቤቱ የት ይገኛል?
ሀ.አዲስአበባ-ኢትዮጵያ
ለ.ናይሮቢ-ኬንያ
ሐ.ፕሪቶሪያ-ደቡብ አፍሪካ
መ.አክራ-ጋና

✔️ለ

ማጠቃለያ መልሳችን ላይ ስህተት ካለ እርሙን።
saramareyama.890@gmail.com

ሐሙስ 16 ኦገስት 2018

ቡሔ ማለት ምን ማለት ነው,,??


Watch "እንኳን ለቡሔ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!" on YouTube
https://youtu.be/EmL0XMJP-d0
"ቡሄ ማለት ምን ማለት ነው"??
የኢትየጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዘጠኝ ዓበይት በዓላት አንዱ የደብረ ታቦር በዓል ነው። በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን የሚከበረው ይህ በዓል መሠረቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ደብረ ታቦር ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደ ፀሐይ የበራበት፣ ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት፣ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው።

ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ። እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ። ደቀ መዛሙርቱም ሰምተው በፊታቸው ወደቁ እጅግም ፈርተው ነበር።

ኢየሱስም ቀርቦ ዳሰሳቸውና፡ ተነሡ አትፍሩም አላቸው። ማቴ. ፲፯፡፩-፭ በቤተ ክርስቲያን ደብረታቦር ከቤተክርስቲያን ውጭ አከባበሩ ቡሄ እየተባለ የሚከበረው በዓል በሀገራችን በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን በታላቅ ድምቀት ይከበራል፡፡ ቡሄ ማለት ብራ፣ ብርሃን፣ ደማቅ ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፣ ወደ መፀው የሚዘለቅበት ወገግታ ፣ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚለወጥበት፣ የሚሸጋገርበት ወቅት በመሆኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡ በዚህ መሰረት የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት 'ቡሄ' የሚለውን ስያሜ አገኘ። ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡ ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት፣ ብረሃን የታየበት ድምጸ መለኮት የተሰማበት ስለሆነ፤ ችቦ ስለሚበራ የብርሃን በዓል በማለት የቡሄ በዓልም ይባላል፡፡

በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። መነሻ የሆናቸው ትውፊት ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡ እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል ፡፡ያንን ለማስታወስ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የሚከበረው ከዚህ በመነሣት ነው፡፡ የንጋት ወጋገን ሲፈናጠቅ ልጆች በከባድ ድምጽና በጅራፍ ጩኸት የሚታጀብ፣ በገደላገደል ስር እንዲያስተጋባ ተደርጎ ብዛት ባላቸው ህጻናት በከፍተኛ ድምጽ የሚዘመር ነው ቡሄ ። የጅራፉ ጩኸትም እግዚአብሔር አብ “የምወደው ልጄ ይህ ነው እርሱን ስሙት” ሲል ሐዋርያት ራሳቸውን ስተው የወደቁበትን የመለኮት ድምፅ ለማስታወስ ነው፡፡

ደብረታቦር ወይም ቡሄ በአብነት ተማሪዎች “ስለ ደብረ ታቦር" እያሉ እህል፣ ፣ ጌሾ ለምነው ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምዕመናን በመጋበዝ በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡ ይህ ትውፊት መምህረ ሐዋርያት የነበረው ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ተማሪዎቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ደብረ ታቦር ይዞ ሄዶ የተገለጠ ምስጢር ስለሆነ ከመምህራቸው ጋር በመሆን በዓለ ደብረ ታቦርን /ቡሄን ያከብራሉ፡፡ ስሙን ይጠራሉ፡፡
የበዓሉ እረዴት በረከት ይደርብን
አሜን
ወስብሀት እግዚአብሔር

ማክሰኞ 14 ኦገስት 2018

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
የምዕራፍ አራት(፬) የ40 ዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃልና የፁህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር

@ምንጭ በማኅበረ ቅዱሳን ተዘጋጅቶ ከቀረበው 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው  ከሚለው   መጽሐፍ የተወሰደ⤵

➡1⃣ ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ጳውሎስ በሰማዕትነት ያለፉባት ከተማ ማን ትባላለች???
ሀ/ አንጾኪያ
ለ/ ሰማርያ
ሐ/ሮም
መ/ መቄዶንያ

✅ሐ

➡2⃣ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ በነበረበት ወቅት ከሰይጣን የቀረበለት ፈተና ምን ነበር??

ሀ/ የትዕቢት
ለ/ የስስት
ሐ/ የፍቅረ ነዋይ
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

➡3⃣ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ቆሮንቶስ በላከው የመጀመርያ መልእክቱ ላይ በመጥፎ ምግባሩ ምክንያት አንድን ሰው ከመካከላቸው እንዲያስወግዱት ነግሮቸው ነበር። ሁለተኛ መልእክቱ ላይ ስለዚህ ሰው ምን አላቸው??

ሀ/ እስካሁ ባለማበረራቸው ተበሳጨ
ለ/ ይቅር እንዲሉት መከራቸው
ሐ/ ማንም ሰው እንዳያናግረው ፈረደበት
መ/ መልስ የለም

✅ለ. 1ኛ.ቆር,5፥4-5

➡4⃣ቅዱስ ጳውሎስ ከነዚህ እቃዎች መካከል ሰዎችን በምን መስሏቸዋል???

ሀ/ በሸክላ እቃ
ለ/ በጠርሙስ
ሐ/ በማንኪያ
መ/ በመጥረቢያ

✅ሀ

➡5⃣ቅዱስ ጳውሎስ ቅዱስ ጴጥሮስን በአንጾኪያ ከተማ ፊት ለፊት የተቀዋወመው ለምን ነበር??

ሀ/ የስህተት ትምህርት በማስተማሩ
ለ/ ራሱን ከቤተ ክርስቲያን አገልግሎት በመለየቱ
ሐ/አይሁድን ሲያይ ከአሐዛብ ጋር የነበረውን ግንኙነት በማቋረጡ
መ/መልስ የለም

✅ሐ..
➡6⃣ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ከተነሳ በኋላ መጀመርያ የታየው ለማን ነው??

ሀ/ ለሰሎሜ
ለ/ ለማርያም መግደላዊት
ሐ/ ለቅዱስ ጴጥሮስ
መ/ ለአርማትያሱ ዮሴፍ

✅ለ

➡7⃣በመጀመርያ ለአገልግሎት የተመረጡ ዲያቆናት ብዛት ስንት ነው?

ሀ/ 5
ለ/ 6
ሐ/ 7
መ/ 1

✅ሐ.

➡8⃣መልካም ዕድልን መረጠች ከእርሷም አይወሰድባትም ብሎ ክርስቶስ የተናገረላት ሴት ማን ናት???

ሀ/ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
ለ/ ኤልሳቤጥ
ሐ/ ማርያም የአላዛር እኅት
መ/ ማርያም መግደላዊት

✅ሐ.

➡9⃣ስለ ጽድቅ የሚራቡ ብፁዓን ናቸው??

ሀ/መጽናናት ያገኛሉና
ለ/ ምድርን ይወርሳሉና
ሐ/ ይጠግባሉና
መ/ መንግስተ ሰማያት የእነርሱ ናትና

✅ሐ.

➡1⃣0⃣በሌላ ስሙ "የቅዱስ ጴጥሮስ ወንጌል በመባል የሚታወቀው የወንጌል ክፍል የትኛው ነው?

ሀ/ የማቴዎስ ወንጌል
ለ/ የማርቆስ ወንጌል
ሐ/የሉቃስ ወንጌል
መ/ የዮሐንስ ወንጌል

✅ለ

➡1⃣1⃣የሕዝብ መምህር በመባል የሚታወቀው ሐዋርያ ማን ነው?

ሀ/ ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ/ ቅዱስ ጳውሎስ
ሐ/ ቅዱስ ታዴዎስ
መ/ ቅዱስ ጢሞቴዎስ

✅ለ

➡1⃣2⃣ከዐራቱ ወንጌላዊያን መካከል በንስር የሚመሰለው ማን ነው??

ሀ/ ቅዱስ ማቴዎስ
ለ/ ቅዱስ ማርቆስ
ሐ/ ቅዱስ ሉቃስ
መ/ ቅዱስ ዮሐንስ

✅መ.

➡1⃣3⃣ከሚከተሉት ቋንቋዎች መካከል መጽሐፍ ቅዱስ በመጀመርያ ያልተፃፈበት የትኛው ነው??

ሀ/ ፅርዕ/ግሪክ/
ለ/ ዕብራይስጥ
ሐ/ዐረብኛ
መ/ አረማይክ

✅ሐ

➡1⃣4⃣ከሚከተሉት ከተሞች መካከል ቅዱስ ጳውሎስ ያልጎበኘው የትኛው ነው??

ሀ/ አንጾኪያ
ለ/ አቴና
ሐ/ እስክንድርያ
መ/ ቤርያ

✅ሐ.

➡1⃣5⃣የጠፋው ልጅ ታሪክ በየትኛው የወንጌል ክፍል ይገኛል??

ሀ/ በማቴዎስ ወንጌል
ለ/በማርቆስ ወንጌል
ሐ/በሉቃስ ወንጌል
መ/ በዮሐንስ ወንጌል

✅ሐ.

➡1⃣6⃣የመቶ አለቃ ቆርኔሌዎስ የመንፈስ ቅዱስን ሀብት የተቀበለው በማን አማካኝነት ነው??

ሀ/ በቅዱስ ጴጥሮስ
ለ/ በቅዱስ ጳውሎስ
ሐ/ በቅዱስ ዮሐንስ
መ/በቅዱስ ጢሞቴዎስ

✅ሀ

➡1⃣7⃣ክርስቶስ ሊሰቀል ባለበት ሰዓት የሚያስጨንቅ ሕልም ያየችውና ባሏ እንዲጠነቀቅ የመከረችው የማን ሚስት ነበረች??

ሀ/ የሊቀ ካህናት ሐና
ለ/የጲላጦስ
ሐ/የሄሮድስ
መ/የአግሪጳ

✅ለ

➡1⃣8⃣እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ዮሴፍና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ከስደት መልስ የኖሩበት ከተማ__ነው??

ሀ/ ናዝሬት
ለ/ ቤተልሄም
ሐ/ቅፍርናሆም
መ/ኢያሪኮ

✅ሀ

➡1⃣9⃣"ለሁለት ጌቶች መገዛት የሚቻለው ማንም የለም" ብሎ ጌታችን  ስለነማን ነው የተናገርው??

ሀ/ ቤተ ክርስቲያንና ሰይጣን
ለ/የራሳችን ፍላጎትና የእግዚአብሔር ፍላጎት
ሐ/እግዚአብሔርና ገንዘብ
መ/መልስ የለም

✅ሐ

➡2⃣0⃣የቅዱስ ጴጥሮስ አማት በሽታዋ ምን ነበር??

ሀ/ለምጽ
ለ/ፍርሃት
ሐ/ንዳድ
መ/ደም መፍሰስ

✅ሐ
🌹🌹🌹🌹🌹
ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ከስተታችን አርሙን.?
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
✝ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ለወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር አሜንsaramareyama.890Gmail.com

ሐሙስ 9 ኦገስት 2018

የምዕራፍ (፬)የ39ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝#በስመ #አብ #ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፫
የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄና መልሶች⤵
የምዕራፍ አራት(፬)/የ39ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃልና የጹህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር⤵
ምንጭ ማሕበረ ቅዱሳን 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ⤵
➡️ማጠቃለያ መልስ
_1⃣ቅዱስ እስጢፋኖስ በአይሁድ እጅ ተይዞ በሐሰት ተከሷል ክሱ ምን ነበር ❓_
_ሀ// ዓመጽ አነሳስቷል_
_ለ// ሰንበትን ሽሯል_
_ሐ// ሙሴን እና እግዚአብሔርን ተሳድቧል_
_መ// ፊቱ እንደ መልአክ አብርቷል_
✅ሐ. ሐዋ 6፥11
_2⃣የህግ ሁሉ ፍጻሜ ምንድን ነው ❓_
_ሀ// ጽድቅ_
_ለ// አስርቱ ትእዛዛት_
_ሐ// መሥዋዕት_
_መ// ፍቅር_
✅.መ. ፍቅር
_3⃣ሐዋርያት በበዓለ ጰንጠቆስጤ የተሰባሰቡባት ቤት የማን ቤት ናት❓_
_ሀ// የማርቆስ እናት_
_ለ// የማርያም ባውፍልያ_
_ሐ// የበርናባስ ወንድም ሚስት_
_መ// ሁሉም መልስ ይሆናሉ_
✅ሀ.የማርቆስ እናት ቤት
_4⃣በአስቆሮቱ ይሁዳ ምትክ ለሐዋርያነት ከማትያስ ጋር ሐዋርያት ያቆሙት ማንን ነበር❓_
_ሀ// ኢዮስጦስ_
_ለ// ዮሴፍ_
_ሐ// በርስያን_
_መ// ሁሉም መልስ ይሆናል_
✅መ.ሐዋ.1፥23
_5⃣በሐዋርያት ሥራ <<ሐዋርያትንም ወደ እነርሱ ጠርተው ገረፉአቸው ፣በኢየሱስም ስም እንዳይናገሩ አዝዘው ፈቱአቸው።>> ተብሎ እንደተጻፈው አይሁድ በገረፉአቸው ግዜ ሐዋርያት ምን አደረጉ❓_
_ሀ// ለግዜው ዝም እንበል ብለው ቃሉን ከመስበክ ተከለከሉ_
_ለ// ወደ ሌላ አገር ተበታተኑ_
_ሐ// ወደ ቀድሞ ሥራቸው ተመለሱ_
_መ// እንዲያውም ዕለት ዕለት በመቅደስ እና በቤታቸው ስለ ጌታችን ያስተምሩ እና ይሰብኩ ነበር_
✅መ.
_6⃣ሳኦል ክርስቲያኖችን ያሳድድ ዘንድ ወደ ደማስቆ በቀረበ ግዜ <<ድንገት በእርሱ ዙሪያ ከሰማይ ብርሃን አንጸባረቀ>> ሳኦል ከጌታችን ምን ማድረግ እንደሚገባው ትእዛዝ ከተቀበለ በኋላ ያልቻለው ምንድን ነው❓_
_ሀ// መራመድ_
_ለ// ማየት_
_ሐ// መናገር_
_መ// መስማት_
✅ለ.
_7⃣በአይሁድ ሸንጎ ፊት በቀረበ ወቅት መጽሐፍ ቅዱስን ከብሉይ እስከ ሀዲስ ኪዳን ያስተማረው ሰማዕት ማነው❓_
_ሀ// ቅዱስ ጴጥሮስ_
_ለ// ቅዱስ ቶማስ_
_ሐ// ቅዱስ ጳውሎስ_
_መ// ቅዱስ እስጢፋኖስ_
✅መ
_8⃣በግሪክ ቋንቋ "አቡቀለምሲስ"የሚባለው መጽሐፍ የትኛው ነው❓_
_ሀ// ትንቢተ ዳንኤል_
_ለ// ኦሪት ዘዳግም_
_ሐ// መዝሙረ ዳዊት_
_መ// የዮሐንስ ራእይ_
✅መ.
_9⃣ሐሙስ ማታ በጌታችን የመጨረሻዋ ሰዓት ጌቴሴማኒ የተገኙት .......❓_
_ሀ// ቅዱስ እንድርያስ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እና ቅዱስ ዮሐንስ_
_ለ// ቅዱስ ጴጥሮስ ፣ቅዱስ ዮሐንስ እና ቅዱስ ያዕቆብ_
_ሐ// ቅዱስ ጴጥሮስ፣ ቅዱስ ዮሐንስ እና ቅዱስ እንድርያስ _
_መ// ቅዱስ ማቴዎስ ቅዱስ ዮሐንስ እና ቅዱስ ጳውሎስ_
✅ለ.
_ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ሁለት ግዜ መልዕክት የጻፈላቸው የትኞቹ ናቸው❓_
_ሀ// የፊልጵስዩስ ሰዎች_
_ለ// የቆላስይስ ሰዎች_
_ሐ// የተሰሎንቄ ሰዎች_
_መ// የኤፌሶን ሰዎች_
✅ሐ
_1⃣1⃣ከአራቱ ወንጌላውያን በሰው የሚመሰለው ማነው❓_
_ሀ// ቅዱስ ዮሐንስ_
_ለ// ቅዱስ ሉቃስ_
_ሐ// ቅዱስ ማርቆስ_
_መ// ቅዱስ ማቴዎስ_
✅መ.
_1⃣2⃣የቅዱስ ጳውሎስ መምህር የነበረው ማን ነው ❓_
_ሀ// ኒቆዲሞስ_
_ለ// ታዴዎስ_
_ሐ// ፊልክስ_
_መ// ገማልያል_
✅መ
_1⃣3⃣ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እርገት  አስቀድሞ በትንቢት የተናገረው ማን ነው❓_
_ሀ// ቅዱስ ሙሴ_
_ለ// ንጉሥ ዳዊት_
_ሐ// ነብዩ ኢሳያስ_
_መ// ነብዩ ዳንኤል_
✅ለ
_1⃣4⃣ከሚከተሉት መካከል መርዘኛ እባብ ነድፎት ያልተጎዳው ማን ነው ❓_
_ሀ// ቅዱስ በርናባስ_
_ለ// ቅዱስ ጴጥሮስ_
_ሐ// ዮሐንስ መጥመቀ መለኮት_
_መ// ቅዱስ ጳውሎስ_
✅መ.
_1⃣5⃣ቅዱስ ጳውሎስ በደማስቆ ሊገድሉት ከነበሩት አይሁድ አምልጧል ።_
_በምን አይነት ሁኔታ ነበር ያመለጠው❓_
_ሀ// ፊቱን በመሸፋፈንና ሌላ ሰው በመምሰል_
_ለ// በቅርጫት ውስጥ ከከተማው ግንብ በመሻገር_
_ሐ// ተአምር በመስራት_
_መ// እዛው ከተማ ውስጥ በመደበቅ_
_ሠ// መልሱ አልተሰጠም_
✅ለ.
_1⃣6⃣ቅዱስ ጴጥሮስ ከሞት ያስነሳት ጣቢታ የምትባል ደገኛ ሴት ነበረች በግሪክ ቋንቋ የስሟ ትርጓሜ ምን ነበር❓_
_ሀ// ጵርስቅላ_
_ለ// አሌክሳንድራ_
_ሐ// ፌበን_
_መ// ዶርቃ_
✅መ.
1⃣7⃣ከሐዋርያት መካከል ሰማዕትነትን ለመቀበል የመጀመሪያ የሆነው ማን ነው
_ሀ// ቅዱስ እስጢፋኖስ_
_ለ// ቅዱስ ያዕቆብ_
_ሐ// ቅዱስ ቶማስ_
_መ// ቅዱስ ጴጥሮስ_
✅ለ.
_1⃣8⃣ክርስቶስ አልዓዛርን ከሙት ያስነሳበት ታሪክ በየትኛው ወንጌል ላይ ይገኛል❓_
_ሀ// የማቴዎስ ወንጌል_
_ለ// የማርቆስ ወንጌል_
_ሐ// የሉቃስ ወንጌል_
_መ// የዮሐንስ ወንጌል_
✅መ.
_1⃣9⃣ቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ እስኪለያዩ ድረስ ያልተስማሙበት  ሀሳብ ምን ነበር❓_
_ሀ// ቅዱስ በርናባስ ወደ ቆጵሮስ ለመሄድ ስለፈለገ እና ቅዱስ ጳውሎስ ሮምን ስለመረጠ_
_ለ// ቅዱስ ማርቆስ አብሯቸው እንዲሆን በርናባስ በመፈለጉ ምክንያት_
_ሐ// በነገረ መለኮት ትምህርት ባላመስማማታቸው_
_መ// ቅዱስ በርናባስ_
✅ለ.
_2⃣0⃣ከሚከተሉት ውስጥ በአራቱም ወንጌላውያን ተፅፎ የሚገኘው  የትኛው ነው❓_
ሀ//የዘሩው ምሳሌ
ለ// የጠፋው ልጅ ምሳሌ
ሐ/የክርስቶስ ስቅለት
መ/የበለስ መርገም

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ቅዳሜ 4 ኦገስት 2018

የምዕራፍ አራት(፬)የ38ኛዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የቃልና የፁህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፫

↪የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄና መልስ↩

➡ማጠቃለያ መልስ⤵

የምዕራፍ አራት(፬)/የ38ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት  መንፈሳዊ የቃልና የፁህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር

@ምንጭ በማኅበረ ቅዱሳን ተዘጋጅቶ ከቀረበው 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ⤵

➡1⃣ከሚከተሉት ውስጥ ከሐዋርያው  ቅዱስ ጳውሎ ጋር በጉዞ የተሳተፈው ማን ነው??
ሀ/ቲቶ
ለ/ ሉቃስ
ሐ/ጢሞቴዎስ
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ

➡2⃣የመጥምቀ ቅዱስ ዮሐንስ አንገት እንድትቆረጥ ያደረገው ማን ነው??

ሀ/ጢባርዮስ ቄሳር
ለ/ፊልክስ
ሐ/ ሄሮድስ
መ/ፈርዖን

✅ሐ.

➡3⃣ከመጠራቱ አስቀድሞ ከሰዱቃውያን ወገን የሆነው ሐዋርያ ማን ነው??

ሀ/ ሉቃስ
ለ/ ሰምዖን
ሐ/ቶማስ
መ/ታዴዎስ

✅ሐ

➡4⃣ጴጥሮስ ለስምዖን፣ ማቴዎስ ለሌዌ፣ ቶማስ ፣ ታዴዎስ ለ___ ነው?

ሀ/ሳውል
ለ/ልብድዮስ
ሐ/ናትናኤል
መ/ለዲዲሞስመ/ስምዖን ቀነናዊ

✅ለ.

➡5⃣"ጌታችን የኢያአሮስን ልጅ ከሙታን በአስነሳ ጊዜ አብረውት የነበሩት ደቀ መዛሙት እነማን ነበሩ??

ሀ/ 12ቱ የሐዋርያት
ለ/ጴጥሮስ፣ እንድርያስ
ሐ/ ዮሐንስ፣ያዕቆብና ጴጥሮስ
መ/ያእቆብ፣ፊልጶስ፣እንድርያስ ያዕቆብ

✅ሐ.

➡6⃣"አብን አሳየንና ይበቃናል። ያለው ሐዋርያ ማን ነው??

ሀ/እንድሪያስ
ለ/ዮሐንስ
ሐ/ፊልጶስ
መ/ጴጥሮስ

✅ሐ.

➡7⃣ለአብ መርዓቱ ለወልድ ወላዲቱ፣ ወለመንፈስ ቅዱስ ___

ሀ/ታቦት
ለ/ ጽርሐ ቤቱ
ሐ/እናቱ
መ/ መልስ የለም

✅ለ.

➡8⃣ከዐራቱ ወንጌላውያን መካከል ሐኪምም ሠዓሊም የነበረው ማን ነው??

ሀ/ቅዱስ ማቴዎስ
ለ/ቅዱስ ማርቆስ
ሐ/ቅዱስ ሉቃስ
መ/ቅዱስ ዮሐንስ

✅ሐ.

➡9⃣ጌታችን ደጋግሞ እኔ ነኝ በማለት ያስተማረው ትምህርት በየትኛው የወንጌል ክፍል ላይ ይገኛል?

ሀ/በማቴዎስ ወንጌል
ለ/ በማርቆስ ወንጌል
ሐ/በሉቃስ ወንጌል
መ/ በዮሐንስ ወንጌል

✅መ.

➡🔟ጌታችን በአዛኙ ሳምራዊ ምሳሌ የመሰለው ምን በመጠየቁ ነው??

ሀ/ወንድሜ ቢበድለኝ ስንት ጊዜ ይቅር ልበለው
ለ/የዘላለምን ሕይወት እንድወርስ ምን ላድርግ
ሐ/ ባልንጀራዬ ማን ነው?
መ/ለሌሎች እንዴት  መልካም እናድርግ

✅ሐ.

➡1⃣1⃣ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ስንት መልእክታትን ጽፏል??

ሀ/12
ለ/14
ሐ/15
መ/7

✅ለ.

➡1⃣2⃣ ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ያጠመቀው ማን ነው?

ሀ/ ቅዱስ እስጢፋኖስ
ለ/ ቅዱስ ፊሊጶስ
ሐ/ ቅዱስ ጢሞቴዎስ
መ/ ቅዱስ ቲቶ

✅ለ.

➡1⃣3⃣ክርስቶስ ሊሰቀል ወደ ጎለጎታ በሚሄድበት ወቅት መስቀሉን ይሸከም ዘንድ ግድ ያሉት ሰው ማን ነው?

ሀ/አሌክሳንድሮስ
ለ/ሩፎስ
ሐ/ የአርማትያሱ ዮሴፍ
መ/የቀሬናው ስምዖን

✅መ.

➡1⃣4⃣የቁም ተዝካሩን/ሀብቱን በመጽውቶ/በማውጣት ጌታን የተከተለው ወንጌላዊ ማን ነው??

ሀ/ቅዱስ ማቴዎስ
ለ/ቅዱስ ማርቆስ
ሐ/ቅዱስ ሉቃስ
መ/ቅዱስ ዮሐንስ

✅ሀ.

➡1⃣5⃣ትንሳዔ ሙታን የለም ይሉ የነበሩት እነማን ነበሩ??

ሀ/ፈሪሳውያን
ለ/ሰዱቃሰዱቃውያን
ሐ/ኤሴያውያን
መ/መለካውያን

✅ለ

➡1⃣6⃣ከሚከተሉት ውስጥ አንዱ የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ደቀ መዝሙር አይደለም?

ሀ/ ጢምቲዎስ
ለ/ቲቶ
ሐ/ሉቃስ
መ/አፍሮዲ
ሠ/ሲላስ
ረ/እስጢፋኖስ

✅ረ

➡1⃣7⃣ጌታችን በተሰቀለ ጊዜ የአይሁድ ንጉሥ፣ የናዝሪቱ ኢየሱስ የሚለው ጽሑፍ በሦስት ቋንቋዎች ተጽፏል።ከሚከተሉት ውስጥ ያልተፃፈበት ቋንቋ የትኛው ነው??

ሀ/ሮማይስጥ
ለ/ሱርስት
ሐ/ግሪክ
መ/ዕብራይስጥ

✅ለ

➡1⃣8⃣መጽሐፍ ቅዱስ 66 ብቻ ሳይሆን 81 እንደሆነ ለማጠየቅ ከመጽሐፈ ሄኖክ የጠቀሰ ሐዋርያ ማን ነው??

ሀ/ቅዱስ ያዕቆብ
ለ/ቅዱስ ቶማስ
ሐ/ቅዱስ በርተሎሜዎስ
መ/ቅዱስ ይሁዳ

✅.መ.

➡1⃣9⃣ከሚከተሉት ውስጥ የዘጠኝ ሰዓት ጸሎት እንደሚያደርግ የተጻፈለት ማን ነው??

ሀ/ቅዱስ ጴጥሮስ
ለ/ቅዱስ ዮሐንስ
ሐ/ቆርኔሌዎስ
መ/ሁሉም መልስ ይሆናል

✅መ.

➡2⃣0⃣ሐናንያና ሰጲራ መሬት ሽጠው ወደ ሐዋርያቱ እግር ሥር አምጥተው ነበር። ነገር ግን ሁለቱም በሞት ተቀስፈዋል፣ በምን ምክንያት.?

ሀ/ የሰው መሬት በመሸጣቸው
ለ/ከመሬቱ ሽያጭ አስቀርተው እኩሌተውን በመስጠታቸው
ሐ/በሐዋርያቱ ላይ በማጉረምረማቸው
መ/መልስ የለም

✅ለ.

🖊ማጠቃለያ መልስ ይህ ይመስላል ስተት ከአለ አርሙን.?

✝ወስብሀት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር አሜንsaramareyama@gmail.com

ሰኞ 23 ጁላይ 2018

የምዕራፍ አራት(፬)/የ37ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የቃል ጥያቄና መልስ ውድድር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

✍የምዕራፍ ፬የ37ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልሶች


1⃣➡ስለ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ የተነበየ ነቢይ ማን ነው??

ሀ/ኢሳይያስ
ለ/ኤርምያስ
ሐ/ሕዝቅኤል
መ/ዘካርያስ

✅ሀ.

2⃣➡የነጎድጓድ ልጆች በመባል የሚታወቁት እነማን ናቸው??

ሀ/ዮሐንስና ጴጥሮስ
ለ/ ያዕቆብና ጤሞቴዎስ
ሐ/ ዮሐንስና ያዕቆብ
መ/ ማቴዎስና ስምፆን

✅ሐ.

3⃣➡የተራራው ስብከት በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል  ይገኛል??
ሀ/ በማቴዎስ ወንጌል
ለ/ በሉቃስ ወንጌል
ሐ/ በሐዋርያት ሥራ
መ/በመጽሐፈ ነገስት

✅ሀ.ማቴ 5፥1

4⃣➡ለስም አጠራሩ ክብር ይሁንና ጌታችን መዳህኒታችን እየሱስ ክርስቶስ "ቀበሮ" የሚል ቅፅል ስም የሰጠው ንጉሥ ማን ነው??
ሀ/አውግስጦስ ቄሳር
ለ/ሄሮድስ
ሐ/ ጴላጦስ
መ/አርኬላዎስ

✅ለ.

5⃣➡ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን አስቀድሞ የላከው ወደ የትኞቹ ነበር??

ሀ/ ወደ አሐዛብ
ለ/ ወደ ሰማርያ
ሐ/ወደ ጠፉት የእስራኤል ልጆች
መ/ ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅ሐ. ማቴ 28፥19

6⃣➡ከሚከተሉት ውስጥ የቅዱስ ጴጥሮስ ወንድም ማን ነው??
ሀ/ፊልጶስ
ለ/ስምዖን
ሐ/እንድሪያስ
መ/በርተሎሜዎስ

✅ሐ.ዮሐ.1፥41

7⃣➡"እውነት ምንድን ነው?? ብሎ ጌታችንን  የጠየቀው ማን ነው??

ሀ/ ቀያፋ
ለ/ጲላጦስ
ሐ/ሄሮድስ
መ/ኒቆዲሞ

✅ለ.ዮሐ.18፥38

8⃣➡በሐዋርያት ሥራ እንደተዘገበው የመጀመርያው የኢየሩሳሌም  ጳጳስ ማን ነው??

ሀ/ ቅዱስ ቶማስ
ለ/ቅዱስ ጳውሎስ
ሐ/ቅዱስ ታዴዎስ
መ/ቅዱስ ያዕቆብ

✅መ.

9⃣➡ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለራሱ  ለሐዋርያት በሚናገርበት ሰዓት ቅዱስ ጴጥሮስ "ይህስ አይሁንብህ; ሲለው ጌታችን ምን ብሎ መለሰለት?

ሀ/ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ
ለ/እኔም እልሀለሁ አንተ ጴጥሮስ ነህ
ሐ/ "ሒድ አንተ ሰይጣን
መ/ "ሰይፍ የሚያነሱ በሰይፍ ይጠፋሉ

✅ሐ..ማቴ 16፥23

1⃣0⃣➡"በነጋታው ሲፈረድበት፣ በእስር ላይ ሳለ የሰላም እንቅልፍ የተኛው ማን ነው??

ሀ/ ቅዱስ ጳውሎስ
ለ/ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐ/ቅዱስ ሲላስ
መ/ቅዱስ ያዕቆብ

✅ለ.ሐዋ 12፥1-10

1⃣1⃣➡እመቤታችን ለዳዊት ልጅ ለሰሎሞን የታተመች ምንጭ፣ ለሕዝቅኤል የተዘጋጅ መቅደስ፣ ለኤልያስ_____ናት??

ሀ/ሠረገላ
ለ/ደመና
ሐ/ሽቶ
መ/ዮርዳኖስ

✅ለ.

1⃣2⃣➡በፊልጲሲዩስ ከተማ ለመጀመርያ ጊዜ ክርስቲያን የሆነው ማን ነው??

ሀ/ልድያ
ለ/የወኅኒው ጠባቂ
ሐ/ድሜጥሮስ
መ/ባርናባስ

✅ሀ.የሐዋርያት ሥራ 16፥11

1⃣3⃣➡ከሚከተሉት ውስጥ የአርማትያሱ ዮሴፍን የሚገልጸው የትኛው ነው??
ሀ/ ክርስቶስ በተሰቀለ ጊዜ በመስቀል ሥር ተገኝቷል
ለ/በስውር የክርስቶስ ደቀ መዝሙር ነበር
ሐ/ክርስቶስን በአይሁድ ልማድ ገንዞታል
መ/ለ እና ሐ መልስ ይሆናሉ

✅መ.ዮሐ 19፥38-40

1⃣4⃣➡ከሚከተሉት ውስጥ ተዋህዶን በተሻለ ሁኔታ የሚገልጸው የትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ነው ??

ሀ/1ኛ.ቆሮ 11፥1
ለ/ዮሐ.1፥16
ሐ/ሉቃ.23፥34
መ/ማር. 5፥34

✅ለ.ዮሐ.1፥16

1⃣5⃣➡የጌታችን ደቀ መዛሙርት በሰንበት ቀን ተርበው እሸት በቀጠፉ ጊዜ ፈሪሳውያን በጌታ ፊት ከሰዋቸው ነበር። ክርስቶስ ግን ከብሉይ ኪዳን ቅዱሳን አንድ ሰው በመጥቀስ ከካህናት በቀር በማንም መብላት የሌለበትን የመሥዋዕቱን ኅብስት መብላቱን ጠቅሶ ገሥጿቸዋል። ይህ የብሉይ ኪዳን ሰው ማን ነው??

ሀ/ ነቢዩ ኤልያስ
ለ/አብርሃም
ሐ/ቅዱስ ዳዊት
መ/ጠቢቡ ሰሎሞን

✅ሐ.ማቴ ም 12፥3

1⃣6⃣➡"እንግዲህ ከክርስቶስ ኢየሱስ ላሉት አሁን ኩነኔ የለባቸውም" ያለው ሐዋርያ ማን ነው??

ሀ/ቅዱስ ጳውሎስ
ለ/ ቅዱስ ጴጥሮስ
ሐ/ ቅዱስ ጢሞቴዎስ
መ/ቅዱስ ዮሐንስ

✅ሀ.

1⃣7⃣➡ከሚከተሉት ትዛዛት ውስጥ ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ሐዋርያትን የአዘዛቸው የትኛው ነው??
 ሀ/ ሂዱና አሐዛብን ሁሉ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው
ለ/ህጌን አስተምሯአቸው
ሐ/ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው
መ/ በየኢየሱስ ስም አጥምቋቸው

✅ሀ.ማቴ 12፥3

1⃣8⃣➡"አምላኬ፣ አምላኬ ለምን ተውከኝ,? የሚለው ቃል ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ የተናገረው ነው። ከብሉይ ኪዳን አባቶች መካከል ይህን ቃል በትንቢት የተናገረው ማን ነው??

ሀ/ ነቢዩ ኢሳይያስ
ለ/ነቢዩ ኤልያስ
ሐ/ነቢዩ ዕንባቆም
መ/ ንጉሥ ዳዊት

✅መ.

1⃣9⃣➡ክርስቶስ ሊሰቀል በአለበት ወቅት በመካከላቸው የነበረውን ጥል ትተው የታረቁ ሁለት ሐገረ ገዥዎች እነማን ነበሩ??

ሀ/ ሐናና ቀያፋ
ለ/ሄሮድስና ጲላጦስ
ሐ/አናሲሞስና ዲዲሞስ
መ/ጢባርዮስና አውግስጦስ

✅ለ.

2⃣0⃣➡ቴዎፍሎስ ለተባለው የግሪክ ባለ ሥልጣን የተጻፈው ወንጌል የትኛው ነው??

ሀ/የማቴዎስ ወንጌል
ለ/ የማርቆስ ወንጌል
ሐ/የሉቃስ ወንጌል
መ/የዮሐንስ ወንጌል

✅ሐ.
ማጠቃለያ መልስ ይህን ይመስላል ስተት ስለሚኖር አርሙን⤴
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለ መስቀሉ ክቡር አሜን

ረቡዕ 18 ጁላይ 2018

የምዕራፍ አራት(፬)/የ36ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የቃል ጥያቄና መልስ ውድድር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

✝የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄ እና መልስ✝

🖊የምዕፍ(፬)የ36ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ የቃልና የፁህፍ ጥያቄና መልስ ውድድር
👏🏻👏🏻👏🏻👏🏻👏🏻👏🏻👏🏻

ማጠቃለያ መልስ እነሆ⤵️
1⃣ሐዋርያት ማለት ምን ማለት ነው??
ሀ.መምህርት
ለ. ተማሪ
ሐ.ተጓዥ
መ. ነቢይ

መልስ✅ሐ.

2⃣ጌታችን ርግብ ሻጮችንና ለዋጮችን ከቤተ መቅደስ በኃይል  ወቅት አይሁድ ተሰብስበው "ይህን ስለምታደርግ ምን ምልክት ታሳየኛለህ;? በአስወጣበትብለው በጠየቁት ጊዜ ጌታችን ምን ብሎ መለሰላቸው??
ሀ. የቤትህ ቅናት ይበላኛል
ለ.ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሰዋለሁ
ሐ. አንተ የማታምን ጠማማ ትውልድ
መ.ምንም አልመለሰላቸውም

መልስ✅ለ.

3⃣ሠላሳ ስምንት ዓመት በሽተኛ የነበረው ሰው የተፈወሰባት መጠመቂያ ቦታ ማን ትባላለች??
ሀ. እየሩሳሌም
ለ.የበጎች በር
ሐ.ቤተ ሳይዳ
መ.መልስ የለም

መልስ✅ሐ.

4⃣"እርሱ ሙሉ ሰው ነው እርሱ ስለራሱ ይናገራል" ያሉ እነማን ናቸው??
ሀ.አይሁድ ክርስቶስን በጲላጦስ ፊት በከሰሱት ጊዜ
ለ. አይሁድ ቅዱስ ጳውሎስን በከሰሱት ጊዜ
ሐ. ከሕፃንነቱ እውር ሆኖ የተወለደውንና ክርስቶስ የፈወሰውን ሰው ወላጆች አይሁድ ስለሁኔታው በጠየቋቸው ወቅት
መ. መልስ የለም

መልስ✅ሐ.

5⃣ከሚከተሉት ውስጥ ክርስቶስ በተሰቀለ ወቅት ታልተደረገ ተአምር የትኛው ነው???
ሀ.ዐለቶች ተሰነጣጠቁ
ለ.ሙታን ተነሱ
ሐ.ፀሐይ ጨለመች
መ.መልሱ አልተሰጠም

መልስ✅መ.

6⃣"አይሁድ ጌታችንን ብዙ ጥያቄ ጠይቀውታል፤አንዳንድ ጊዜም እርሱ ጥያቄአቸውን በጥያቄ ይመልስ ነበር። በአንድ ወቅት "የዮሐንስ ጥምቀት ከሰው ነው ወይስ ከእግዚአብሔር ብሎ ለጠየቃቸው ጥያቄ ምን ብለው መለሱለት.?
ሀ.አናውቅም
ለ.ከእግዚአብሔር ነው
ሐ.ከሰው ነውል
መ.መልሱ አልተሰጠም

መልስ✅ሀ.

7⃣ጌታችን የወይን አትክልት ስለነበረው ሰው በተናገረበት አንቀጹ ላይ የወይኑ ባአለቤት ለንግድ ወደ ሌላ ቦታ እንደሄደና እርሻው የሚያፈራበት ወቅት ሲደርስ ባሮቹን እና ልጁን እንደ ላከ ነገር ግን ገበሬዎቹ ግማሹን እንደ ደበደቧቸው ልጁን ደግሞ እንደገደሉት ተናግሯል። አይሁድ ይህን ሲሰሙ ሊይዙት ፈልገው ነበር። ነገር ግን አልያዙትም ለምን??
ሀ. በመካከላቸድ አልፎ በመሔዱ
ለ.ሰንበት ስለነበረ
ሐ. ሕዝቡን በመፍራት
መ.ቢይዙት ምሳሌው ለእነርሱ እንደተናገረ መቀበል ስለሚያስመስልባቸው

መልስ✅ሐ. ሉቃ 20፥9-21

8⃣ክርስቶስ ከመስቀሉ በፊት በነበሩ ቀናት፣ ቀን ቀን በቤተመቅደስ እያስተማረ ይውል ነበር። ሌሊቱን የት ነበር የሚያሳልፈው??
ሀ. በቤቱ
ለ. በደብረ ዘይት ተራራ
ሐ.ከኒቆዲሞስ ጋር
መ. በባህረ ጌንሳሬጥ

መልስ✅ለ.

9⃣የርኅሩኁ ሳምራዊ ታሪክ በየትኛው ወንጌል ላይ ይገኛል???
ሀ. በማቴዎስ ወንጌል
ለ. በማርቆስ ወንጌል
ሐ. በሉቃስ ወንጌል
መ. በዮሐንስ ወንጌል

መልስ✅ሐ.

1⃣0⃣ከቅዱስ ጳውሎስ ጋር በመሆኑ ለስብከተ ወንጌል ይፋጠን የነበረው በርናባስ የየትኛው ወንጌላዊ አጎት ነው።?
ሀ. የቅዱስ ማቴዎስ
ለ.የቅዱስ ማርቅቆስ
ሐ. የቅዱስ ሉቃስ
መ. የቅዱስ ዮሐንስ

✅ለ.

1⃣1⃣ጎለጎታ ማለት ምን ማለት ነው..?
ሀ. ቀራንዮ
ለ.የመስቀያ ቦታ
ሐ. ራስ ቅል
መ.የወንበዴ መቅጫ

መልስ✅ሐ.

1⃣2⃣በሰሞነ ሕማማት የማይደረግ የቤተ ክርስቲያን ስርዓት የትኛው ነው..??
ሀ. ጸሎት
ለ.ስግደት
ሐ.ፍትሐት
መ.ምንባብ

መልስ✅ሐ.

1⃣3⃣ከሚከተሉት አንዱ ቅዱስ ጴጥሮስ በበዓለ ኃምሳ ከተናገራቸው ነጥቦች መካከል አይደለም??
ሀ.ክርስቶስ ያደረጋቸው ተአምራት ከእግዚአብሔር ዘንድ ለእኛ የተገለጠ መሆኑ
ለ.የክርስቶስ ልደት በመላእክት የተበሠረ መሆኑን
ሐ.ስለ ክርስቶስ ትንሳኤ አስቀድሞ ነቢዩ ዳዊት እንደ ተነበየው
መ. አይሁድ በአመፀኞች እጅ ሰቅለው እንደገደሉት

መልስ✅ለ.

1⃣4⃣መልካም በተባለች ቦታ ተቀምጦ ሲለምን የነበረው ሰው ለዘጠኝ ሰዓት ጸሎት ወደ ቤተ መቅደስ ሲመጡ የፈወሱት እነ ማን ነበሩ??
ሀ. አሥራ አንዱ ሐዋርያት
ለ.ቅዱስ ጴጥሮስና ቅዱስ ዮሐንስ
ሐ.ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ
መ. አዲስ የተጠመቁ ክርስቲያኖች

መልስ✅ለ.

1⃣5⃣ደቀ መዛሙርቱ ለመጀመርያ ጊዜ ክርስቲያን የተባሉት በየት ከተማ ነው??
ሀ.በቁስጥንጥንያ
ለ.እስክንድርያ
ሐ.በአንጾኪያ
መ.በፊልጵስዩስ

መልስ✅ሐ.

1⃣6⃣ከሚከተሉት አንዱ ከሰባቱ ዲያቆናት መካከል አይደለም..?
ሀ. እስጢፋኖስ
ለ.ፊልጶስ
ሐ.አርኬላዎስ
መ.ኒቆላዎስ

መልስ✅ሐ.

1⃣7⃣የካህኑ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ጎረቤቶች፤ የዘካርያስ ልጅ ስም ማን እንዲባል ፈለጉ.?
ሀ.ዘካርያስ
ለ.ዮሐንስ
ሐ.ኤልያስ
መ.መጥምቁ

መልስ✅ሀ.

1⃣8⃣ከሚከተሉት አንዱ በዮሐንስ ራእይ ከተገለጹት ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ አንዱ አይደልም??.
ሀ. ኤፌሶን
ለ.ጴርጋሞን
ሐ.ሎዶቅያ
መ.ሮም

መልስ✅መ.

1⃣9⃣የመንፈስ ቅዱስን ሀብት ከሐዋርያት በገንዘብ ለመግዛት የፈለገው ማነው??
ሀ. ይሁዳ
ለ.ሲሞን
ሐ. አናንያ
መ.ሰጴራ

መልስ✅ለ.

2⃣0⃣ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በገሊላ ያደረገው ሁለተኛው ተአምር ምንድን ነው??
ሀ. ውኃውን ወደ ወይነ ጠጅ ለወጠ
ለ.ለ5000 ሰው መመገብ
ሐ.የንጉሱን ሹም ልጅ መፈወሱ
መ.ለምፃሞችን ማንፃቱ

መልስ✅ሐ.ዮሐ 4፥46-

ማጠቃለያ መልስ ይህንን ይመስላል
ወስብሐት ለእግዚአብሔርsaramareyam.890@gmail.com

ሰኞ 9 ጁላይ 2018

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄና መልሶች የምዕራፍ ፬የ35ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ ውድድር

✝የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄ እና መልስ✝@Teyakaenamels
@Teyakaenamelsወመንፈስ

በስመ አብ ወወልድ  ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

#የምዕራፍ ፬/የ35 ዙር የጠቅላላ እውቀት የቃልና የጹህፍ የጥያቄና መልስ ውድድር

የዚህ ጥያቄና መልስ ምንጭ፦ በማኅበረ ቅዱሳን ተዘጋጅቶ ከቀረበው 420 ጥያቄዎች እስከ መልሶቻቸው ከሚለው መጽሐፍ ነው👇
===×××===
1⃣ዐማኑኤል ማለት ምን ማለት ነው?
     ሀ.እግዚአብሔር ብርሃን ነው
     ለ.እግዚአብሔር ፍቅር ነው
     ሐ.እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው
     መ.እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው

✅= ሐ

2⃣የነብያት ትንቢት ፍጻሜ የሆነውን ጌታችንን ሳያይ ሞትን እንደማይቀምስ በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ የነበረ ሰው ማን ነው?
  ሀ.ቀነናዊው ስምዖን
  ለ.ስምዖን ጴጥሮስ
  ሐ.አረጋዊው ስምዖን
  መ.ሲሞን መሥርይ(መሠርይ)

✅=ሐ

3⃣የሰውነት መብራት የሚባለው የአካል ክፍል የትኛው ነው?
  ሀ.ልብ
  ለ.ልቦና
  ሐ.ዓይን
  መ.አዕምሮ

✅= ሐ

4⃣ከሚከተሉት አባባሎች መካከል በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተነገረው የትኛው ነው?
  ሀ.«ሄደህ ራስህን ለካህን አሳይ»
  ለ.«ስለ እኔና ስለወንጌል ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን ያድናታል»
  ሐ.«የማይቃወመን እርሱ ከእኛ ጋር ነውና»
  መ.ሁሉም መልስ ይሆናሉ

✅=መ

5⃣«ይህ መጥምቁ ዮሐንስ ነው እርሱ ከሙታን ተነሥቷል፡ስለዚህም ኃይል በእርሱ ይደረጋል»ያለው ማን ነው?
  ሀ.ፊሊጶስ
  ለ.ጲላጦስ
  ሐ.ሄሮድስ
  መ.አርኬላዎስ

✅=ሐ ማቴ 14፥1

6⃣«የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም»ያለው ማን ነው?
  ሀ.ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
  ለ.ቅዱስ ጴጥሮስ
  ሐ.ልጇ የታመመችባት ከነናዊት ሴት
  መ.ይሁዳ

✅=ሀ

7⃣ልጆቿ በክርስቶስ ቀኝ እና ግራ እንዲቀመጡላት የለመነችው ማን ናት?
  ሀ.የያዕቆብ እና ዮሳዕ እናት
  ለ.የጴጥሮስ እና እንድርያስ እናት
  ሐ.የያዕቆብ እና የዮሐንስ እናት
  መ.የማርታ እና የማርያም እናት

✅=ሐ

8⃣የጌታችን ደቀመዛሙርት ምን በማድረጋቸው ነው ፈሪሳውያኑ ቀርበው«ደቀመዛሙርትህ እንደ ሽማግሎች ወግ ስለምን አይሄዱም»ያሉት?
  ሀ.ስላልጾሙ
  ለ.ሰንበትን ስላላከበሩ
  ሐ.እጆቻቸውን ሳይታጠቡ ስለበሉ
  መ.ብሉይ ኪዳን አያስፈልግም ስላሉ

✅= ሐ

9⃣ወደ ኤማሁስ በሚሄዱበት ጊዜ ሁለት ሐዋርያት ስለምን እየተነጋገሩ ነበር?
  ሀ.ስለ ኢየሰስ ክርስቶስ ማንነት
  ለ.ክርስቶስ በምሳ ስላስተማረው ትምህርት
  ሐ.ከመካከላቸው ማን እንደሚበልጥ እየተመካከሩ
  መ.መልስ የለም
✅= መ

🔟በይሁዳ ምትክ ከዐሥራ አንዱ ጋር የተቆጠረው ሐዋርያ ማን ነው?
  ሀ.ማቴዎስ
  ለ.ሉቃስ
  ሐ.ማትያስ
  መ.ቀለዮጳ

✅=ሐ

1⃣1⃣ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረታቦር ተራራ አምላክነቱን በገለጠ ጊዜ የነበሩት ሦስት ደቀመዛሙርት እነማን ነበሩ?
  ሀ.ቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅዱስ ዮሐንስ እና ቅዱስ እንድርያስ
  ለ.ቅዱስ ፊሊጶስ፣ቅዱስ በርተሎሚዎስ እና ቅዱስ ታዴዎስ
  ሐ.ቅዱስ ጴጥሮስ፣ቅዱስ ያዕቆብ እና ቅዱስ ዮሐንስ
  መ.ቅዱስ ናትናኤል፣ቅዱስ ስምዖን እና ቅዱስ ማርቆስ

✅=ሐ

1⃣2⃣በቤተክርስቲያን ታሪክ የመጀመሪያው የሐዲስ ኪዳን ሰማዕት ማን ነው?
  ሀ.ቅዱስ እስጢፋኖስ
  ለ.ቅዱስ ያዕቆብ
  ሐ.ቅዱስ ለንጊኖስ
  መ.ቅዱስ ጴጥሮስ

✅= ሀ

1⃣3⃣ክርስቶስ በተሰቀለበት ዘመን ሊቀ ካህናት የነበረው ማን ነው?
  ሀ.ሐና
  ለ.ቀያፋ
  ሐ.ሰጲራ
  መ.ሐናንያ
✅=ሀ

1⃣4⃣ከሚከተሉት የቅዱስ ጳውሎስ መልዕካታት ውስት ስለ ካህናት አጠቃላይ ሁኔታ የሚገልፀው የትኛው ነው?
  ሀ.ለቲቶ የተላከው
  ለ.ለጢሞቴዎስ መጀመሪያ የላከው
  ሐ.ወደ ኤፌሶን ሰዎች የላከው
  መ.ወደ ገላቲያ ሰዎች የላከው

✅=ለ

1⃣5⃣ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተወለደባት ከተማ ማን ናት?
  ሀ.ገሊላ
  ለ.ቤተልሔም
  ሐ.ናዝሬት
  መ.ቃና

✅=ለ

1⃣6⃣በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው---
  ሀ.መንግስተ-ሰማያት የእነርሱ ናትና
  ለ.መጽናናትን ያገኛሉና
  ሐ.ምድርን ይወርሳሉና
  መ.እግዚአብሔርን ያዩታልና

✅=ሀ

1⃣7⃣ነባቤ መለኮት በመባል ሚታወቀው ወንጌላዊ ማን ነው?
  ሀ.ቅዱስ ማቴዎስ
  ለ.ቅዱስ ማርቆስ
  ሐ.ቅዱስ ሉቃስ
  መ.ቅዱስ ዮሐንስ

✅= መ

1⃣8⃣እግዚአብሔር የኃይልና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጂ ------------- መንፈስ አልሰጠንምና
  ሀ.የፍርሃት
  ለ.የግብዝነት
  ሐ.የሐሰት
  መ.የጥላቻ

✅=ሀ

1⃣9⃣አገልጋዩ አናሲሞስን ምሕረት አድርጎ እንዲቀበለው ቅዱስ ጳውሎስ ደብዳቤ የላከለት ሰው ማን ነው?
  ሀ.በርናባስ
  ለ.ጢሞቴዎስ
  ሐ.ፊሊሞና
  መ.ቲቶ
✅=ሐ

2⃣0⃣ከሚከተሉት ውስጥ ምሳሌያዊነት የሌለው ታሪክ የትኛው ነው?
  ሀ.የጠፋው ልጅ
  ለ.የቀራጩና የፈሪሳዊው
 ሐ.የጠፋው በግ
  መ.የሰማርያዊቷ ሴት


✅=መ

✅✅✅
ማጠቃለያመልስ ይህንን ይመስላል ስተት ካለ አርሙን....saramareyama.890@gmail.com

ረቡዕ 4 ጁላይ 2018

ቅኔ ሰምና ወርቁን ለዩ

saramareyama.890@gmail.com
#ቅኔ
ሰሙን ወርቁን በማውጣት ይሞክሩ፡፡

#ቅኔ
፩. ከዚያ ታች ያለችው ድውይ፤
ከቶ ምን ቀመሽ አልሻት ወይ
ኋላ ፀፀቱ ባንቺ ይሆናል
ተይ ሥጋ ብላሽ ይሆናል፡፡

#ቅኔ
፪.የቀድሞ ዘመን ስህተት
የፆም ቀን አሳ መብላት
የአሁን ዘመን ሰው አያውቅ መላ
በጦም ሽሮ ነው የሚበላ፡፡

✝ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንዴት ዋላችሁ እንዴትስ ቆያችሁ???

ለተሳተፋችሁ ሁሉ ቃለ ሕይወትን ያሰማልን ተስፋ ዕርሰተ መንግስተ ሰማያትን ያውርስልን አሜን፫


☞ የቅኔ ፩ መልስ

ሕብረ ቃሉ => ተይ ሥጋ ብላሽ
ሰሙ => #ሥጋው #ብላሽ (#የተበላሸ) ሊሆን ስለሚችል እንዳይፀፅትሽ ምንም አትበያት። ወይም ቅመሽው አትበያት ነው።
ወርቁ => 1ኛው ፍቺ #ሥጋ(የሰው ደካማው ሥጋ) ብላሽ መሆኑ አይቀርም። አፈር መግባቱ ወይም መበላሸቱ አይቀርም።

2ኛው የወርቁ ፍቺ ደግሞ => ነብስሽ ለሥጋሽ "ተይ ሥጋ" ብላሽ(ተናግራሽ)ይሆናልና፣ ይህን እያለችሽ(እንፁም )እያለችሽ) እንብላ(እንቅመስ) አትበያት። ኋላ እንዳይፀፅትሽ። ማለት ነው።


☞ የቅኔ ፪ መልስ

ሕብረ ቃሉ => በጦም ሽሮ
ሰሙ => የጦም ቀን ሽሮ የሚባል ወጥ ነው የሚበላው። ወይም የጦም ምግብ ነው የሚበላው።
ወርቁ => #ጦምን #ሽሮ ወይም #አፍርሶ ነው የሚበላው። የቀድሞዎቹ #በስህተት(#ባለማወቅ) ነበር የሚበሉት፣ የአሁኖቹ ግን #እያወቁ #ጦምን #ሽረው(#አፍርሰው) ነው አሳ የሚበሉት ማለት ነው።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር አሜን፫

ማክሰኞ 3 ጁላይ 2018

መንፈሳዊ የጥበብ ውጤቶች: መንፈሳዊ የእንቆቅልሽ/ህ መረሀ ግብር

መንፈሳዊ የጥበብ ውጤቶች: መንፈሳዊ የእንቆቅልሽ/ህ መረሀ ግብር: ✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፫ �������� እንቆቅልሽ �������� ��ምናውቅልሽ ፩///የሰራዊት ጌታን ከፊት አስቀድሞ መሳሪያ ሳይኖርው እንዲሁ በባዶ ኃያልነኝ ያለውን በራስ ተ...

መንፈሳዊ የእንቆቅልሽ/ህ መረሀ ግብር

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን፫
🌹🌹🌹🌹
እንቆቅልሽ
🌹🌹🌹🌹
👉ምናውቅልሽ

፩///የሰራዊት ጌታን ከፊት አስቀድሞ
መሳሪያ ሳይኖርው እንዲሁ በባዶ
ኃያልነኝ ያለውን በራስ ተመክቶ
ያሸነፈው ማነው  በጠጠር ወርውሮ❓
       
✅ የህዝቡን መርበሽ የንጉሱን ጩኽት
ሲሰማና ሲያይ ሳለ በእረኝነት
የአባቶቹን አምላክ በጸሎት ለምኖ
እደሚያሸንፍም በእግዚአብሔር ተማምኖ
ለሐገር ያስቸገረን ጎልያድን የጣለው
ያትንሽ ብላቴና ቅዱስ ዳዊት ነው።

፪// የተመርጡትን ቅዱሳን ሲያሳድድ
አምላክን ሳይፈራ ድሀን ሲጨፈጭፍ
የበደሉ ብዛት ጽዋው ሞልቶ ሲፈስ
ጌታም ሊመልሰው አመጣበት መቅሰፍት
በደማርቆስ ተራራ አታሰደኝ ብሎ ጌታ የገሰጸው ማነንነው❓

✅ የጌታ ምርጥ እቃ ተብሎ የተጠራው
አምላኩን በጽናት ሁኖ የተከተለው
ተዘቅዝቆ ተሰቅሎ መሰእዋት የሆነው
ከአይሁድ ወገን የሆነ  ጳውሎስ ነው።

///፩ ስልጣን አለኝ ብለህ በራስህ አትኩራ
ብሎ የገሰጸው ንጉሱን ሳይፈራ
ፈጣሪን እሚያሳዝን ስራን እዳሰራ
የወንድምህን ሚስት በፍጹም አታግባ
ጌታ ይጠራሀል እባክህ ቃሌን ስማ
ያለው ቅዱስ ሐዋርያ ማነው❓


   ✅ ገና ከናቱ ማህጸን የተመርጠ
በዮወርዳኖስ ባህር ጌታን ያጠመቀ
ለፍጥርቱ ሁሉ ወንጌል የሰበከ
እራሱ ክርስቶስ የመሰከርለት
ቅዱስ ሐዋርያ መጥምቀ መለኮት
ቅዱስ ዮሐንስ ነው።

፬//መስዋዕት ከፍዬ ለፍቅሬ
ሰባት አመት  ፍየሎች ጠብቄ
ነው የተገኘች ሄዋን አጋሬ

እኔ ማነኝ
✅ ለእስራኤል አባት የሆንኩ ድንቅ ታሪካቸው
በመፃፍ ተከትቤ እስከዛሬ ያለው
እኔ ነኝ ያእቆብ የራሄል ባለቤት
የ አስራሁለቱ ነገድ የዮሴፍ አባት

፭//በብልሃቴ ተጠቅሜ
አምኖንን ከፉ ምክር በመምከሬ
እህቱን እዲያሰነውራት ያደረግኩ
እርሱንም ለሞት የዳረኩ
እኔ ማነኝ

✅አቢናዳብ 2ኛ ሳሙ 13:1-34


፮//የሰባ ሰገልን ስጦታ
በግብጽ የስደት ቦታ፤
አብረን ሳለን ካንዱ ጓዴ
የቀማሁኝ  ወንበዴ፤
ወርቁን ጫማ በመውሰዴ
ተጸጽቼ ባብቶ ሆዴ፤
 መለስኩኝ በፈቃዴ።

እኔ ማነኝ
✅ ይህንን ውለታ ጌታዬ አስቦ
በትንሽ ትልቁ እንደሰው አድጎ
በመስቀል ላይ በዋለ ጊዜ ዓለማውን ፈፅሞ
በዚያ በቀራንዮም ጎልጎታ
አስበኝ አልኩት ለፅድቅ ቦታ
እደበደሌ ሳያይ ለመንግቱ የጠጠራኝ
የቀድሞው ወንበዴ የዛሬው ፊያታዊዘይማ ነኝ

፯// ስንጓዝ ያኔ በግብፅ በረሃ
አውርዶ የመገበን የሰማዩን መና
ከአለት አመንጭቶ ያጠጣን ውሃ
እዳያቃጥለን ፀሃይ ሀሩሩ
የጋረደን በክንፋ የተዋጋልን በሰይፉ
መኑ ከማከ የተባለው ብረሃናዊው መለአክ ማነው
✅ የአፎማያ እረዳት የባህራን ታዳጊ
በክንፎቹ ጥላ ወዳጁን ጠባቂ
ከእያሱ ጋር አብሮ ህዝቡን የመራ
እርሱ ነው ሚካኤል ሁሌ አብሮን የሚኖረው ሁሌ ከኛ ጋራ

፰/ ልዩ ስትሆን ከአለም
ከምድር ማር ከሰማይ ያም
ወስደው ሁለቱን ደምረው
ለስሟ ትርጓሜ የሰጧት
ይቺ ቅድስት ማናት

✅የጣፈጠች ከሁሉ በላይ
ብረሃኗ የሚልቅ ከጨረቃ ከፀሃይ
የወለደች አምላክ አዶናይ
ማርያም ናት።
@Teyakaenamels
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለ ወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር
saramareyama.890@Gmail.Com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...