ረቡዕ 31 ጃንዋሪ 2018

#በዮናስ #ስብከት ነነዌን ሊያቃጥል የወረደው እሳት(2) ተመልሶ አረገ(2) በኅዘን በጸሎት (2) ስለሆነ ከልብ የኀዘናቸው ምንጩ ነበር እንደ ራሔል(2)እንባን እየረጩ(2) ለነነዌ ሰዎች ደስታን ያበሰረ(2) ጋሻና ጦራቸው(2) ጾም ጸሎት ነበረ (2) እንኳን የሰው ልጆች እንስሳት ሳይቀሩ(2) በዮናስ ስብከት(2) ጾም ጸሎት ተማሩ(2) #ለሰብአ #ነነዌ ለሰብአ ነነዌ/፪/ አዉጻእኮሙ /እም ማዕከለ እሳት/፬/ ትርጉም:-የነነዌ ሰዎችን ከእሳት መካከል አወጣሃቸው።

https://youtu.be/uc8QTI48fD8



#በዮናስ #ስብከት


ነነዌን ሊያቃጥል የወረደው እሳት(2)
ተመልሶ አረገ(2) በኅዘን በጸሎት (2)
         
ስለሆነ ከልብ የኀዘናቸው ምንጩ
ነበር እንደ ራሔል(2)እንባን እየረጩ(2)

ለነነዌ ሰዎች ደስታን ያበሰረ(2)
ጋሻና ጦራቸው(2) ጾም ጸሎት ነበረ (2)

እንኳን የሰው ልጆች እንስሳት ሳይቀሩ(2)
በዮናስ ስብከት(2) ጾም ጸሎት ተማሩ(2)

#ለሰብአ #ነነዌ

ለሰብአ ነነዌ/፪/
አዉጻእኮሙ /እም ማዕከለ እሳት/፬/

ትርጉም:-የነነዌ ሰዎችን ከእሳት መካከል አወጣሃቸው።saramareyama.890.gmail.com

መንፈሳዊ የግጥም መድብል

እመቤቴ ማርያም የአምላክ እናት
እጅጉን ይደንቃል ያንችስ አሟሟት
በጥር 21 በክብር አርፈሽ
ስለ ኃጥዓን ስትይ ለመሞት ፈቀድሽ
አይሁድ በክፋት በአመጽ ተነስተው
እናቃጥላት አሉ ቅድስናሽን ስተው
ልጅሽ ይህን አይቶ መቼ ዝም አላቸው
መላእክትን ልኮ ተዓምር አሳያቸው
ክብርት ሥጋሽንም ነጠቁ ከእጃቸው
በክብር አኖርላሽ ከገነት አግብተው
የጌታ ቀን ደርሶ ትንሳኤሽን እስኪያዩ
ቅዱስን ሐዋርያትም በፆም ጸሎት ጸኑ
እግዚአብሔር ፈቅዶ እስክልሚደርስ ቀኑ
ያሟሟትሽን ነገር እጹብ እጹብ አሉ
እውነት ነው ይደንቃል የአምላክ እናት
እኛም እንድንድን ከሲዖል እሳት
እመ አምላክ አደራ ምልጃሽ አይለየን
እንደመናፍቃን እንደማያምኑ ሳይሆን
ሞትሽን በጥር ወር ነሐሴ መቃብር
ትንሳኤና እርገትሽን ሁሉን እናምናለን
ሐዋርያት አበውን አብነት አድርገን
እጹብ ድንቅ እያልን እናወድሳለን
እስከ ለዘለዓለም ብጽሒት እንላለን።

@ከ ወለተ ሥላሴ

♥♥♥♥♥♥♥♥

ጌታ ሆይ
አሁን በዚህ ስአት ፊትህ ተደፍቼ እንዲህ ምለምንህ ፣
አንድ ነገርን ነው ዛሬ ምጠይቅህ ፣
እንደ ትላንትናው እንዳለፈው ጊዚያት ፣
ለንዋይ አይደለም መምጣቴ ካንተ ፊት፣
ወይም ህይወት ግራ ሆና እጅግ  ከብዳኛለች ፣
ደስታ'ዬን ነጥቃ ሀዘን ሞልታኛለች ፣
በችግር በርሀብ ወዜ ተሟጠጠብርታቴን ተቀማው ፣
ያ ፀአዳ ፊቴን ማጣት አጠቆረው ፣
በማዲያት ተሞላ እንባዬ አሻከረው ፣
የተትረፈረፈው የሞላው ማጀቴ ፣
ዘይት ሆነ ዱቄት የለኝም ከቤቴ ፣
ሚቀመስ እንጀራ ጠፍቷል ከሌማቴ ፣
ምቀይረው የለም ከለበስኩት በቀር ፣
ማጥብበት እንኳን ጠፍቷል አንዳቺ ነገር ፣
ያው ተራቁቻለው ድህነት አጠቃኝ ፣
ምን ነው ዝም አልክ ታዲያ ምህረትህን ነፈከኝ ፣
ለሌላው ስትቸር ለእኔ ከለከልከኝ ፣
ይሄው የታደሉት እማ ....
4 አምስት ልጅ በቤታቸው ሞልቶደስታቸው ያስቀናል  ፣
የህፃናቱ ድምፅ ለመኖር ያጓጓል ፣
ልብን ተስፋ ሰጥቶ መንፈስን ያድሳል ፣
የእኔስ ወዴት አለ የማህፀኔ ክፋይ ዘሬን ምተካበት ፣
አይኔን በአይኔ አይቼ ምደሰትበት ፣
መውጣቴ መውረዴ ምክንያቴ ምልበት ፣
እኮወዴት አለዘሬን ምተካበት ?
አሁን ይሄን ሁሉ ልጠይቅ አይደለም ዛሬ መገኘቴ ፣
ያሁን ግን ይለያል ሌላ ነው ምኞቴ  ፣
በል ስማኝ ልንገርህ አድምጠኝ አባቴ፣
ስው ናፈቀኝ ብዬ ያነባውት እንባዛሬ ላይ ላልቅሰው ፣
በፀፀት ልታጠብ ሀጥያቴን ላስታውሰው፣
የዘላለም ቤቴ የሰጠኸኝን እርስት ገነትን ልናፍቀው ፣
መሪር እንባን ላውርድ ቃልህ ይመልሰኝ፣
የጴጥሮስን እንባ ለእኔም ዛሬ አድለኝ ፣
በደልሽን እመኚ ዶሮ ጮኃል በለኝ፣
ደግሞም አንዳንድ ጊዜ....
የስጋዬ አምሮት ጌደለብኝ ብዬ ምጉተመተመው ፣
በነጋ በጠባ እሮሮ እማሰማው ፣
እንዲያ ሲለኝ ደግሞ ...
እረሳኸኝ ብዬ ማነባውን እንባ ባክህ ዛሬ ስጠኝ ፣
ለበደሌ ይሁን በሀጥያት መኖር ይብቃኝ ፣
ይሄው.....
ዲያቆኑ በመቅደስ ተንስዑ እያለ ደውል ይደውላል ፣
በፀሎት እንድተጋ ወደ አንተ እንዳንጋጥጥ ቃሉን ይናገራል ፣
ስባኪውም ይላል ..?
ወደ ቤቱ ግቡ በንስሀ ውሀ በፍቅሩ ታጠቡ ፣
ስጋውንም ብሉ ክቡር ደሙን ጠጡ ፣
ከረከሰች ዓለም ቀጠሮ ሳትይዙ ዛሬውኑ ውጡ ፣
ሁሉም በእየፊናው መዳንን ይሰብካል ፣
መንግስትህን እንድወርስ ኑ ቅረቡ ይላል ፣
እባክህ አባቴ ሁሉም ነገር ቀርቶ ይህን አሳካልኝ ፣
የጴጥሮስን እንባ ለእኔ ልጅህ ስጠኝ ፣
አንተን ልፈልግህ አለም አድክሞኛል ፣
የጨበጥኩት ደስታ ወና ሆኖብኛል ፣
አለ ያልኩት ነገር የተማመንኩበት ባንድ ጊዜ ከድቶኛል፣
ደንዳናውን ልቤን በቃልህ ሰብረጀው ፣
ከአለም ምናምንቴ ቀራንዮን ልየው ፣
ጎልጎታን ልመልከት ፍቅርህን ላስበው ፣
አዎ መዳኒቴ

በህይወት ዘመኔ ያለቀስኩት ለቅሶ ፣
ለንስሀ ላንባው ይምጣ ተመልሶ።

@ከ ወለተ ብርሀንsaramareyama.890@gmail.com

እንቆቅልህ/ሽ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።

       *እንቆቅልሽ/ህ..?*

1, ጣፋጭ የሆነ እንደማር
የማያስርብ የሚያጠግብ
በስደትም ስንቅ ነው
አምኖ ለሚጠራው
.
//መልስ// የቅድስት ድንግል ማርያም ስም።

2.እግዚአብሔር ቢወደው
ጥፋትን አላሳየው
ሊቀጥፍ ሄዶ በለስን
አንቀላፍቶ ዘመናትን
የዳነ ከምርኮ ማነው?

//መልስ//አቤሜሌክ ነው።

3.ሰንሰለትን ለብሳ የተጋደለች
ለሃይማኖቷ ቆርጣ የታገለች
የሱስንዮስ ክኅደት ፍጹም ያላስፈራት
የእምነት አርበኛ ይህች ቅድስት እናት
በሉ እስኩ ንገሩኝ ማናት?

//መልስ// ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ናት።


4.ሳይገባኝ የማልችለውን ነክቼ
ተጣብቃ ቀረች እጄ ሰለሉ ጣቶቼ
የምሕረትን እናት በክፋት ነክቼ
ኃጢአቴ የበዛ ማነኝ ወገኖቼ?

//መልስ//ታውፋንያ ነው።

5.ለድንግል ማርያም በክብር የሸለማት
በሥጋ ወደሙ ባርኮ ያከበራት
የታቦተ ጽዮን የግዮን መገኛ
የታሪክ የሃይማኖት የእውቀት መመዘኛ
በቅዱስ መጽሐፍ ስሟ ተዘርዝሯል
ስለ ቅድስናዋ በስፋት ተጽፏል
..//መልስ//ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያ ናት።

6.የጌታን ትእዛዝ ትቶ
በባህር ሲሄድ ሸሽቶ
በአሳአንባሪ ተበልቶ
ከቀናት በኋላ የተፋው አውጥቶ
ማነው እስኪ ካወቃችሁት ንገሩኝ???

//መልስ// ነቢዩ ዮናስ
saramareyama.890@gmail .com

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

ዓርብ 26 ጃንዋሪ 2018

አፊያ ሁሴን ክፍል 12

አፊያ ሁሴን ክፍል #12saramareyame.890@gmail.com

አፊያ ሁሴን (ክፍል ፲፪)

የጀመርኩት አዲስ ሕይወት ከእርግዝናዬ ጋር ተደማምሮ ነው መሰለኝ የሚፈራረቁብኝ ስሜቶች ቅጥ የለሽ ሆኑብኝ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ያለ ምክንያት ቁጭ ብዬ ስነፈርቅ እውላለሁ፡፡ አንዳንዴ ደግሞ በስልክም ሆነ በአካል ለሚያናግሩኝ ሰዎች ቅን መልስ መስጠት ይቸግረኛል፡፡ ከመሬት ተነስቶ ውስጤ ብስጭትጭት ይልብኛል፡፡ አንዳንዴ ሙሉ ቀን ተኝቼ ሌላ ጊዜ ደግሞ ራሴን በሥራ ጠምጄ እውላለሁ፡፡ በመኝታም ሆነ በሥራ ተወጥሬ የምውለው በውስጤ ከሚጮህብኝ አንዳች ነገር ለማምለጥ የማደርገው እንደሆነ ቆይቶ ነበር የተረዳሁት፡፡ ለእርግዝና ክትትል የሚጎበኘኝን ሀኪም ስለሚሰማኝ ስሜት ነግሬው ነበር፡፡ እርሱ ግን "ከእርግዝና ጋር ተያይዞ በውስጥሽ በሚፈጠር የሆርሞን ለውጥ የስሜት መለዋወጦች ይከሰታሉ፡፡ ነገሩ ተፈጥሮአዊ በመሆኑ መጨነቅ የለብሽም" አለኝ፡፡ በሰርጌ ሰሞንና በአውሮፓ ጉብኝቴ አዕምሮዬ ከመደነቅ የሚተርፍ ሌላ ስሜትን የሚያስተናግድበት ጊዜም ቦታም አልነበረውም፡፡ አሁን ግን የጋብቻው ትኩስነት በመጠኑ መብረድ ሲጀምር፣ ዙሪያዬን የሚያጅበኝ ሰው ሁሉ ወደየመደበኛው ኑሮው ሲመለስ፣ ሁመይድም ሥራ እያለ የተለመደ ውክቢያውን ሲቀጥል የብቸኝነት ስሜት እየከበበኝ መጣ፡፡ በእርግጥ የሚያነጋግረኝ ሰው አላጣም፣ በስልክም ከተለያዩ ሰዎች ጋር ማውራት እችላለሁ፡፡ ችግር የሆነብኝ እርካታ የሚባል ነገር ማጣቴ ነው፡፡ ቤቴ ውስጥ እጅግ ውድ፣ ዘመናዊና ምቹ በሆኑ የቤት ውስጥ ቁሳቁሶች ተከብቤ ነው የምውለው፡፡ ግቢው መሐል ደግሞ እስካሁን ያልተነዱ ሁለት የራሴ የምላቸው መኪኖች አሉ፡፡ ቁስና ምቾትን እንደ ሕይወት ግብ ለሚቆጥሩ ሰዎች የእኔን እርካታ ማጣትን ከቅብጠት እንደሚቆጥሩት አያጠራጥርም፡፡ ማንም ምንም ተሰማው እኔ ግን በውስጣዊ እኔነቴ እርካታ፣ እረፍትና ሰላም አጥቻለሁ፡፡

ሁመይድ ከሀገር እየወጣ አሥራ አምስት ቀንም፣ ሦሥት ሳምንትም አንዳንድ ጊዜ ወር ያህልም እየቆየ ይመጣል፡፡ እርሱ ሀገር ውስጥ በማይኖርበት ጊዜ እህቴ ሰዓዳ ወይም ፋይሰል እየመጡ እኔ ጋር ያድራሉ፡፡ እናቴም ቀን ቀን አዘውትራ ትመጣለች፡፡ አባቴ ግን ከሁለት ቀን በላይ ብቅ አላለም፡፡ እማማ አፀደና ልጃቸው ሄለን፣ አስቻለውና ኤርምያስ የተወሰነ ጊዜ ጎብኝተውኛል፡፡ በተለይ ሄለን አዲሱ ቤት የገባሁ ሰሞን ለሳምንታት ሙሉ ቀን አብራኝ እየዋለች ጓደኝነቷንና አለኝታነቷን አሳይታኛለች፡፡ እርግዝናዬ እየገፋ ሄዶ ሆዴ ማስታወቅ ሲጀምር ቤት የምውልበት ሰዓት እየበዛ መጣ፡፡ ባሌ ሁመይድ ደግሞ ወራቴ እየጨመረ ሲመጣ የእርሱም ወደ ውጭ መመላለስ እየጠነከረ፣ በላይ በላዩም እየሆነ፣ ሄዶ የሚቆይበትም ጊዜ እየሰፋ መጣ፡፡ አንዳንድ ጊዜ "ገና ከማግባቴ ማርገዝ አልነበረብኝም" ስል አስባለሁ፡፡ በእርግጥ "ቸኮልሽ" የሚሉኝም ነበሩ፡፡ ሌሎች ደግሞ "ካገቡ በኋላማ የምን መቆየት ነው? የትዳር ማጥበቂያና የቤት ማድመቂያው ልጅ ነው"  ይላሉ፡፡ ያም ሆኖ እኔ ምኑንም ሳላስብ የልጅ እናት ለመሆን መንገድ ላይ ነኝ፡፡ ከወለድኩ በኋላ ስለሚሆነው ነገር ለማሰብ እሞክርና በፍርሃት "መጀመሪያ እስቲ በሰላም ልገላገል" እልና እተወዋለሁ፡፡ ሃሳቤ ግን እኔ ልተወው ብል እንኳ በዋዛ የሚለቀኝ አልነበረምና በሃሳብ ባህር እዋጣለሁ፡፡ በእርግጥ የሚያሳስቡ በርካታ ነገሮች አሉብኝ፡፡ ትምህርት የመቀጠል ብርቱ ፍላጎትና የከረመ ዕቅድ አለኝ፡፡ አባቴ ዶክሜንቴን ነጥቆ በተንኮልና በማን አለብኝነት እንዳልማር በማድረጉ የትምህርት ፍላጎቴ ይበልጥ ጨምሯል፡፡ ጋብቻዬን ተከትሎ ዶክሜንቶቼን ከመለሰልኝ ሰነባብቷል፡፡ እናም ከወለድኩ በኋላ ስለምማረው ትምህርት አስባለሁ፡፡ ልጄን ማንን እንደሚመስልና እንዴትስ ተንከባክቤ እንደማሳድገውም አሰላስላለሁ፡፡ በሰላም የመገላገሌ ነገርም እንዲሁ ያሳስበኛል፡፡ ከሁሉ ይልቅ የሚያብሰለስለኝ ጉዳይ ግን ሁመይድን ያገባሁበት ዋንኛ ምክንያት የሆነው የህሊና ነፃነቴና እርሱን ተጠቅሜ አደርገዋለሁ ብዬ ያቀድኩት ነገር ነው፡፡

ሁመይድን ለማግባት ስወስን በዋናነት የታየኝ ነገር ከአባቴ መገላገልን ነው፡፡ ሳገባ ይብዛም ይነስም የተሻለ የኢኮኖሚ ነፃነት እንደሚኖረኝ ገምቻለሁ፡፡ ስለዚህም ዋንኛ መደራደሪያ ያደረኩት የህሊና ነፃነትን ነበር፡፡ በዚያ ላይ ያገባች ሴት በዕድሜ የበሰለች፣ ከእርሷ አልፎ ቤተሰቧን የማስተዳደር ሃላፊነት የሚጣልባት ስለሆነች ከወላጆች የሚደርስባት ጫና ይቀንሳል፡፡ የኢኮኖሚ ነፃነቴን በመጠኑም ቢሆን ለማስከበር ሁመይድ የናጠጠ ቱጃር መሆኑና ኢትዮጵያዊ ዜግነት የሌለው መሆኑ ጠቅሞኛል፡፡ ለእርሱ ቀላል ከመሆኑ በተጨማሪ በእኔና በቤተሰቦቼ ዘንድ ሞገስ ለማግኘት ሲል የምንኖርበትን ቤትም ሆነ የሰጠኝን መኪና በእኔ ስም ነበር የገዛቸው፡፡ እኔ ሙሉ ውክልና የሰጠሁት ወንድሜ ፋይሰል ነው ተዋውሎ የገዛው፡፡ እነዚህን ምቹ ሁኔታዎች በመጠቀም በውስጤ ሲብላላ የኖረውን ክርስትና በወግ ልማረውና ልቀበለው አቅጃለሁ፡፡ ጌታ ከፈቀደ ምናልባት ለሁመይድም እተርፍ ይሆናል፡፡ ይህ የእኔ ሃሳብ ይሁን እንጂ እንዲህም ሆኖ ጠንካራ ተግዳሮቶች መኖራቸው አይቀርም፡፡ ከሥጋቶቼ አንዱ ያው አባቴ አንዱ ነው፡፡ እርሱ ካመነበት አስተሳሰብ እንዳልወጣ ምንም ነገር ከማድረግ አይመለስም፡፡ በዚህ መንገድ አቋሙንም ጭካኔውንም ባለፉት ጊዜያት አሳይቶኛል፡፡ በዚያ ላይ እጀ ረጅምና የተፅዕኖው አድማስ የሰፋ ነው፡፡ ምንም እንኳ እኔም ከመጣብኝ ለምንም ነገር ግንባሬን የማላጥፍ ጽኑ መሆኔ ባይጠፋውም እንቅፋቶች ከመፍጠር ወደ ኋላ እንደማይል ግልፅ ነው፡፡ ሌላው አሳሳቢ ነገር ራሱ ሁመይድ ነው፡፡ እርሱ ገጽታው ሲታይ የዋህ፣ ፎልፏላና ቅን ቢመስልም በደንብ አውቀዋለሁ ማለት ግን አልችልም፡፡ ሌላው ቀርቶ ለሥራ ጉዳይ ወደ ውጭ ሄድኩ ሲለኝ አምኜ ከመሸኘት፣ እዚያም ሳለ ሲደውል ከማውራትና ሲመጣ ከመቀበል የዘለለ ዝርዝር ነገር አላውቅም፡፡ በተለያዩ ሀገሮች ልዩ ልዩ ሥራዎች እንዳሉት የታመነ በመሆኑ ለመጠራጠር ዕድል አይሰጥም፡፡ ከዚህ ሁሉ ጋር ለእኔ ያለው ፍቅርን የእውነት የሚያስመስሉ በርካታ ሁኔታዎችም ይታዩበታል፡፡ ይሁን እንጂ ከጋብቻ በፊት ስላወራነው የሕሊናና የእምነት ነፃነት ላለፉት 6 ወራት አንስተን አናውቅም፡፡ ብዙውን ጊዜ ቤት የማሳልፍ ስለሆንኩ ይሁን ያልኩትን ነፃነት እያከበረልኝ ስለ እስላማዊ አለባበስ አንስቶብኝ አያውቅም፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ ግን በማላውቀው ምክንያት መጪውን ጊዜ አስመልክቶ ሁመይድን ጭምር በጥርጣሬ ቀለበት ውስጥ እንዳውለው የሚሰማኝ ስሜት አለ፡፡

ስለዚህ ነገሮችን ከተለያየ ማዕዘን ሳያቸው ከሁሉ በፊት ልጄን መውለድ እንደሚኖርብኝ አመንኩ፡፡ ያን ሁሉ መሥዋዕትነት የከፈልኩበትን ነገር ያላግባብ እንደገፋሁትና እንዳዘገየሁት የሚወቅስ መንፈስ በውስጤ እየተመላለሰ እያወከኝ ቢሆንም በቅድሚያ መውለድ ይኖርብኛል እያልኩ ደጋግሜ ለራሴ ነገርኩት፡፡ እንዲህ ያለው ውሳኔ ፈተና ምናልባትም መከራ ሊከተለው ስለሚችል በጽናት ለመጋፈጥና  በአገባብ ለመጋደል የአካልና የአዕምሮ ጤንነት ላይ መሆን እንደሚያስፈልግ ተሰምቶኛል፡፡ ሆኖም አልፎ አልፎ በራሴ ማስተዋልና ብልሃት ለመመራት እየሞከርኩ እንዳለሁ በማሰብ እጨነቃለሁ፡፡ መልሼ ደግሞ ከየት ያገኘሁት ትምህርት እንደሆነ ባላውቅም "እግዚአብሔር ያለልክ ቸር በመሆኑ በራሱ ጊዜም በእኛ የጊዜ ሰሌዳም ገብቶ ለማዳን የሚሰራ አምላክ ነው" በማለት ራሴን አፅናናዋለሁ፡፡ እንዲህ ባለው የሕሊና ሙግት፣ በዚህ ዓይነት ውጫዊ ሁኔታ ተከብቤ ቀሪዎቹ ወራት ነጎዱና የመውለጃዬ ጊዜ ደረሰ፡፡ ከአሁን አሁን ምጥ ያጣድፈኛል እያልኩ በምጠባበቅበት ሰዓት ሚዜዬና ጓደኛዬ የሆነችው ሄለን ደወለችና "ሁመይድ ተመልሷል እንዴ?" ስትል ጠየቀችኝ፡፡ ግርም አለችኝና "ምን ሆነሻል? በሦሥት ቀኑ ነው እንዴ የሚመጣው? ናዝሬት የሄደ አስመሰልሽው እኮ፡፡ ይልቅ ለምን በፍጥነት አትመጪም?" አልኳት፡፡ በእኔ ቤት የጅል ጥያቄ መጠየቋ አናዶኛል፡፡ ለመውለድ በመቃረቤ እንደ ሚዜነቷና አብሮ አደግነቷ ሰሞኑን ሁሉ አጠገቤ ነበረች፡፡ ዛሬ ግን ብቅ ሳትል ከሰዓቱ ተጋመሰ፡፡ ሄለን አጠገቤ ስትሆን በጣም ደስ ይለኛል፡፡ የሆነ ሁነኛ ሰው ከጎኔ እንዳለ ይሰማኛል፡፡ ስለዚህም ዛሬ በመዘግየቷ ተነጫነጭኩባት፡፡ እህቴ ሰዓዳ ከእኔ ጋር ብትሆንም እንደ ልጅ ስለማያት ለጨዋታ እንጂ ለጭንቅ የምትሆን አይመስለኝም፡፡ ውስጤ መረጋጋት ሲያቅተው "እንደውም ለምን ብዬ ምጥ እስከሚጀምረኝ እዚህ እቆያለሁ?" አልኩና ክትትል ሳደርግበት የነበረ አንድ ልዩ የማዋለጃ ክሊኒክ ሄድኩ፡፡ እዚያም ምንም እንኳ ምጥ ባይጀምረኝም ጊዜዬ መድረሱን አይተው አልጋ ሰጡኝና ተኛሁ፡፡

እግዚአብሔር ይመስገን የበኩር ልጄን ምጥ ብዙም ሳይጠናብኝ በሰላም ተገላገልሁ፡፡ ዙሪያዬ በበርካታ ሰው ተሞልቶ በማየቴ እጅጉን ደስ አለኝ፡፡ መኝታዬ በአበባና በመልካም ምኞት መግለጫ ተሞልቷል፡፡ የሌለው ሰው ቢኖር የልጄ አባት ሁመይድ ብቻ ነው፡፡ አባቴ ሳይቀር አጠገቤ ነበር፡፡ ከአባቴ የሚወለዱት ወንድሞቼና እህቶቼ፣ ዘመዶቻችን፣ የሰፈራችን ሰዎች እየተመላለሱ ሲጠይቁኝ የሆነ የኩራት፣ ብቻዬን ያለመሆን ስሜትና ለማህበራዊ መስተጋብር ገዘፍ ያለ ዋጋ የመስጠት ሃሳብ ውስጤን ይሞላዋል፡፡ አንድ ተለቅ ያለ ጉድለት የሚታየው የሁመይድ አለመኖር ነው፡፡ የመጀመሪያ ልጁ ሲወለድ ባለማየቱ፣ አጠገቤ ባለመሆኑ፣ በጠያቂዎች ሊቀርብለት የሚገባን የ"እንኳን ደስ አለህ" ምርቃት አደግድጎ ያለመቀበሉ አሳዘነኝ፡፡ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ ነገሩ ያበሳጨኝ ጀመር፡፡ በተለይ ሰዎች "አባቱ የታለ? እንኳን ደስ አለህ እንበለው" ሲሉ ብሽቀቴ ይጨምራል፡፡ ሆኖም ይህን ነገሬን የተረዱ የቅርብ ሰዎቼ እንዲህ ያለው መገጣጠም የተለመደ እንደሆነና ብዙም ቦታ ልሰጠው እንደማይገባ ደጋግመው ስለወተወቱኝ ነገሩን ቀለል አድርጌ ለማየት ሞከርኩ፡፡ በወለድኩኝ በአራተኛ ቀኔ ሁመይድ ደወለና በተለመደ ጩኸቱና ሳቁ ታጅቦ ደስታውን ገለፀልኝ፡፡ አሁን ዱባይ እንዳለና ከጥቂት ቀን በኋላ በዚያው ወደ እንግሊዝ አቅንቶ እንደሚመለስ ነገረኝ፡፡ አጠገቤ የተኛውንና ከእርሱ የተወለደውን ጨቅላ ሕጻን ዝም ብዬ ሳስተውለው የፈጣሪ ሥራ ይደንቀኛል፡፡ እኔ ለዘጠኝ ወራት ያህል በሆዴ የተሸከምኩትን ይህን ሕጻን እንዲህ አሟልቶና ውብ አድርጎ መሥራት ምን ዓይነት ጥበብ ነው ብዬ እገረማለሁ፡፡ ክንዴ ስር ተወሽቆ በጸጥታ ሲተኛ፣ ጡት ፍለጋ ደረቴ ላይ ሲርመሰመስ፣ ጡቴን በአፉ ጎርሶ በዓይኖቹ ዓይን ዓይኔን ሲመለከት እንዴት አንጀቴን እንደሚያንሰፈስፈው ልነግርሽ አልችልም፡፡ በቃ ተፈጥሮ የራሷ እጅግ የረቀቀ የእናትና ልጅ መስተጋብር አላት፡፡ ወልደው ካላዩት በቀር በፍፁም ለመረዳት ይከብዳል፡፡ በቃ...ገና ከወልድኩ በጥቂት ቀናት ውስጥ "ወይ እናቴ ለካ እንዲህ በስስት ነው ያሳደግሽኝ" እያልኩ መደመም ጀምሬያለሁ፡፡

በአራስነት ጊዜዬ ቤቴ እንደደመቀ ሰነበተ፡፡ እናቴና ሰዓዳ ሙሉ በሙሉ እኔ ጋር ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ ሄለንም አዳሯ እኔ ጋር ነው፡፡ ብዙ ጠያቂዎች ስለሚመላለሱ ቀኑ ሳይታወቀኝ ነጎደ፡፡ ሁመይድ እንደተለመደው በሦሥት ትላልቅ ሻንጣዎች ለእኔና ለሕጻኑ የልብስ መዓት አጭቆ መጣ፡፡ ገና ምኑንም ለማያውቀው ጨቅላ በየዓይነቱ አሻንጉሊትና መጫወቻ በመግዛት ቤቱን ሞላው፡፡ የፈጠረው ድባብ የሆነ ዓይነት ደስታ ፈጠረብኝ፡፡ ውጭ ሀገር እንደሚያየው ዓይነት እዚሁ እኛ ጋር የሚኖሩ የሕጻኑን ጤና የምትከታተል ነርስና የምትንከባከብ ሞግዚት ካልቀጠርኩ ብሎ ከእኔ ጋር ሙግት ገጠመ፡፡ እኔ ከአራስ ቤት እስክወጣ እናቴ አጠገቤ መኖሯንና ከዚያም በኋላ ቢሆን ልጄን ራሴ መንከባከብ እንደምፈልግ ለዚህም እንደማላንስ በመናገር ተከራከርኩ፡፡ ይሁን እንጂ ሸምጋዮች ልጁን የምትንከባከብ ሞግዚት እንድትቀጠር የነርሷ አስፈላጊነት ግን ብዙም እንዳልሆነ በማስረዳት ዳኙን፡፡ ለእኔም "ሕጻኑ ከፍ ሲል አንቺም ወጣ ወጣ ማለት ስትጀምሪ የግድ ጠባቂ ያስፈልገዋል፡፡ ስለዚህ ካሁኑ ቢለምዳት የተሻለ ነው" አሉኝ፡፡ አያይዘውም "አይዞሽ...እናትነቱን እንደው አትቀማሽም፣ በጠረንሽ ነው የሚለይሽ" እያሉም ቀለዱብኝ፡፡ በዚህ የግርግር ወቅት አዲስ አበባ ያልነበረችው ሌላዋ ሚዜዬ ልዕልና ልትጠይቀኝ መጣች፡፡ ስንጫወት ቆይተን አመሻሽ ላይ ሁመይድ መጣ፡፡ ከልዕልና ጋር ረዥም ጊዜ ባለመገናኘታቸው ሞቅ ያለ ሰላምታ ተለዋወጡ፡፡ "ኤፊን ለመጠየቅ ትንሽ አርፍጃለሁ፣ አንተም እንኳን ደስ አለህ" ስትለው ትንሽ ራቅ ብዬ ካለሁበት እያስተዋልኳቸው ነበር፡፡ እርሱም "እንኳን አብሮ ደስ አለን..! ለማርፈዱ ግን ችግር የለም፡፡ እኔ ባልየው እንኳን አሁን በቅርብ ነው የመጣሁት" አለ፡፡ "እንዴ..!? ስትወልድም እዚህ አልነበርክም እንዴ?" አለች ልዕልና፡፡ ከሌላኛው ጥግ ያለችው ሄለን ልዕልናን በዓይኗ ስትገስፃት ተመለከትኳት፡፡ "ሄለንና ልዕልና ባሌ ላይ ሙድ እየያዙበት ነው እንዴ?" ስል አሰብኩና ይበልጥ ጆሮዬን እነርሱ ላይ ለማድረግ ሞከርኩ፡፡ ነገር ግን አጠገቤ ያሉት ሰዎች ሲያዋሩኝ ቀሪው የባሌና የጓደኞቼ የቃላት ልውውጥ አመለጠኝ፡፡

ሜሪዬ.. መቼም የልጄን ስም አወጣጥ በተመለከተ የነበረውን ውዝግብ ሳልነግርሽ ባልፍ ደግ አይሆንም፡፡ እኔ የልጄ ስም እስላማዊና አረባዊ ዘይቤ ያለው እንዲሆን አልፈለኩም፡፡ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ስም መስጠትም መሰረታዊው ነገር ሳይነካ በዘርፍ ጉዳዮች ፀብ ማስነሳት መስሎ ታየኝ፡፡ ከዚህ ሁሉ በተጨማሪ እየተመናመኑ ባሉ ኢትዮጵያዊ ስሞች የሚቆጭ አንድ ጽሑፍ አንብቤ ስለነበር የልጄ ስም ኢትዮጵያዊ ይዘት እንዲኖረው ወስኜ ነበር፡፡ ስለሆነም ለክትባት ክሊኒክ በሄድኩ ጊዜ የልጄን ስም "በረከት" ብዬ አስመዘገብኩ፡፡ ይህን ያልሰሙት ቤተሰቦቼ ስም በመምረጥ ተጠመዱ፡፡ ብዙዎቹ መሐመድ ይሁን አሉ፡፡ የቀሩት ሙስጠፋ፣ ሌሎች ደግሞ ካሊድ እንዲባል ተመኙ፡፡ ነስረዲን፣ ጀማል፣ ሀሰን፣ አብደላህ... መዓት ስም በአማራጭ ቀረበ፡፡ እኔን እንድመርጥ ሲጠይቁኝ ስም እንዳወጣሁለትና ክሊኒክ እንደተመዘገበ፣ የልደት ካርዱንም በአዲሱ ስም እንዲያዘጋጁት እንደላክሁ ነገርኳቸው፡፡ ማን ብዬ እንዳወጣሁለት ሲጠይቁኝ እጄ ላይ ሆኖ የሚቁለጨለጨውን ልጄን በጨዋታ መልክ ወደ ላይ እያነሳሁት "በረከት ብዬዋለሁ...በረከት ሁመይድ" አልኳቸው፡፡ ከተሰበሰቡት ብዙዎቹ ኩምሽሽ ሲሉ ያስታውቅባቸዋል፡፡ አባቴ ግን በእኔና በስም አውጭዎቹ መካከል የማቀራረብ ሥራ ለመስራት እየጣረ "ጥሩ ነው ይሄም ጥሩ ነው..ግን ሙባረክ ቢባል የበለጠ ውብ ይሆናል" አለ ወደ ሰዎቹም ወደ እኔም እያፈራረቀ ተመለከተ፡፡ አባቴን በሰዎች ፊት ለማክበር ስል ገልመጥ አድርጌ አይቼው ዝም አልኩ፡፡ አስተያየቴና ዝምታዬ አንዳች መልዕክት አስተላለፈለት መሰለኝ ጥቂት ግርግር ፈጥሮ ሹልክ አለ፡፡ ከአባቴ የቅርብ ሰዎች አንዱ እንደ ምክርም እንደ ልመናም በሚመስል ቃና "አፊያ ሐጂ ልክ ናቸው፣ ሙባረክ የአንቺንም የሁሉንሜ ፍላጎት ያሟላል" አለኝ፡፡ እኔም "ምነው..በረከት መጥፎ ስም ነው?" ስል ጠየኩት፡፡ "አይ...መጥፎ አይደለም፣ ይበልጥ ውብ ለማድረግ ብዬ ነው፡፡ እስላማዊ ይዘት ቢኖረው ደስ ይላል" አለኝ፡፡ ፈገግ አልኩና "ቀኑን ሙሉ 'ወበረካቱ' ስትሉ አይደል እንዴ የምትውሉት? ምኑ ነው ከእስላማዊ ይዘት የወጣው?" አልኩ፡፡ እርሱ ግን በዋዛ የሚተወኝ አልሆነም፡፡ ቀጠለና "ቁራን በወረደበት፣ ነቢያችን ጥሪ ባደረጉበት ቋንቋ ስም ሲወጣ ጥሩ ነው" አለ፡፡ እኔም "ተው ባክህ አታድክመኝ፣ እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ፡፡ በአፍ መፍቻ ቋንቋዬ የተዋበ ትርጉም ያለው ስም አውጥቻለሁ፡፡ ስነ ልቡናዬ በአረቦች ቅኝ ግዛት እንዲገዛ አልፈቅድም" ብዬው ዞሬ ከሌላ ሰው ጋር ማውራት ቀጠልኩ፡፡ በሁመይድ በኩል ጫና ፈጥረው ስሙን ሊያስቀይሩ ቢሞክሩም ሳይሳካላቸው ቀረ፡፡

ልጄ ስድስት ወር ከሞላው በኋላ አንድ ቀን ከሁመይድ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በኃይለኛው ተጨቃጨቅን፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የተለመደው እስላማዊ አለባበስ ነው፡፡ አንድ ምሽት ቤታችን ውስጥ አንድ ተለቅ ያለ ግብዣ ማድረግ እንደሚፈልግ ነገረኝ፡፡ እኔም በድግሱ ምንም ቅሬታ እንደሌለኝ ነግሬው የግብዣው ምክንያት ግን ምን እንደሆነ ጠየኩት፡፡ እርሱም "እውነት ለመናገር ምንም የተለየ ምክንያት የለኝም፡፡ ነገር ግን ከሰርጋችን ወዲህ በተለይ ደግሞ ቤታችን ውስጥ ግብዣ አዘጋጅተን አናውቅም፡፡ ዘመዶቻችን፣ ጓደኞቻችን፣ ሌሎችም እንግዶች የሚገኙበት ፕሮግራም ቢኖረን መልካም ነው፡፡ እንደ አባወራነቴ ቤቴ ውስጥ ወዳጆቼን ብጋብዝና ቆመን ብናስተናግድ በጣም ደስ ይለኛል" አለኝ፡፡ ሃሳቡ እኔንም ደስ አሰኘኝ፡፡ እንደ ቤተሰብ ሃላፊ ማሰቡንም መናገሩንም ወድጄለታለሁ፡፡ ወዲያው ግን የተሰማኝን በጎ ስሜት ሁሉ የገለበጠ ነገር ተከተለ፡፡ እጄን እየያዘና በዓይኑ እየተለማመጠኝ "ኤፊ ቆንጆ የእኔ ውድ..አንድ ነገር ልለምንሽ...እባክሽ እምቢ እንዳትዪኝ?" ብሎ ሁለቱንም እጆቼን በየተራ ይስም ጀመር፡፡ በጥርጣሬ እየተመለከትኩት "ምንድነው..?" አልኩት፡፡ አጥፍቶ በሚቀጣው አባቱ ፊት እንደቆመ ታዳጊ ልጅ መሬት መሬት እያየ ሲቅለሰለስ ቆየና "የዚያን ቀን ማለቴ የግብዣው ቀን በእስላማዊ ልብስ ተውበሽ ብትታዪ በጣም ደስ ይለኝ ነበር" አለኝ፡፡ ጠላትሽ ክው ይበልና ሜሪዬ እንዴት እንዳስደነገጠኝ አትጠይቂኝ፡፡ በድንጋጤ ከደረቅሁበት ሁኔታ ስወጣ ንዴት ከአጥንቴ ሥር እንደ አዲስ ምንጭ ሲፈልቅ ይሰማኝ ነበር፡፡ ነገሩን ሳስበው ድግስ ደግሶ እኔን በሂጃብና አባያ ቁጥጥር ሥር እንዳደረገኝ ለማሳየት የፈለገ መሰለኝ፡፡ ቀድሞውኑ ዋናው ነገር እኔን በእስላማዊ ልብስ ማሳየት እንጂ ድግሱ አልነበረም፡፡ ግብዣው ማጀቢያ ፕሮግራም ብቻ ነበር፡፡ ቀጥሎ ደግሞ ይህ ሃሳብ ፈፅሞ የእርሱ እንዳልሆነ፣ የአባቴና የግብር አበሮቹ ዕቅድ ሊሆን እንደሚችል ማሰላሰል ያዝኩ፡፡ በውስጤ እንደ እሳት የሚነደውን ብሽቀት አምቄ ልመረምረው ፈለግሁ፡፡

"በጣም ይገርማል...ከመጋባታችን በፊት በዚህ ጉዳይ ተነጋግረን አልነበረ እንዴ? የገባኸውን ቃል ማጠፍህ ነው?" አልኩት የተሰማኝን ንዴት ለመደበቅ እየታገልኩ፡፡ "አይ አይ አይ...እንደዚያ አይደለም ኤፊ፣ እየለመንኩሽ ነው፡፡ ውሳኔው የአንቺ ነው፣ እኔ ልመና ነው ያቀረብኩት" አለ ሁለቱን መዳፎቹን በመዘርጋት የልመና ምልክት ለማሳየት እየሞከረ፡፡ በአንድ በኩል የሌሎች ሰዎች ምክርና ግፊት መሆኑን ሳስብ በሌላ በኩል ደግሞ "በእስላማዊ ልብስ ተውበሽ" የሚለው ንግግሩ እየታወሰኝ 'የራሱ ድብቅ አጀንዳ ይሆን እንዴ?' ስል ራሴን እጠይቃለሁ፡፡ ይህን ነገር ማውጣጣት አለብኝ ብዬ ምርመራዬን ቀጠልኩ፡፡ "ይህን ሃሳብህን ባልቀበለውስ ድግሱና ግብዣው ይቀራል?" ስል ጠየኩ፡፡ ቀና ብሎ አይቶኝ ዝም አለኝ፡፡ እኔም "መልስልኝ እንጂ እየጠየኩህ እኮ ነው?" ብዬ ኮስተር አልኩ፡፡ እንደማመንታት አረገውና "አይ...ለምን ይቀራል?" አለ፡፡ በጣም እንደተከፋ ያስታውቃል፡፡ ከመጋባታችን በፊትም ሆነ በኋላ እንዲህ ዓይነት ቅሬታ አይቼበት አላውቅም፡፡ "ሁመይድ" ስል ጠራሁት፣ ከአንገቱ ቀና ብሎ አየኝ፡፡ አስተያየቱ "አቤት" ከማለት በላይ ነበር፡፡ "በዚህ ጉዳይ መነጋገር ይኖርብናል፣ እየጠየከኝ ያለኸው ከሕይወት መመሪያዬ ውጪ የሆነ ነገር ነው፡፡ በዚያ ላይ በሕሊና ነፃነቴ ላይ ላትገባ የገባኸው ቃል አለ፡፡ ለምንድነው ታዲያ እንዲህ ቅር የሚልህ?" ስል ጠየኩት፡፡ እርሱም በተለመደ የንግግር ዘዬው "ኤፊ..እኔ እያስገደድኩሽ ወይም እየተጫንኩሽ አይደለም፡፡ ቃሌንም እያጠፍኩ አይደለም፡፡ ልመና ነው ያቀረብኩት፡፡ እኔ ባልሽ ነኝ፣ የልጅሽ አባት ነኝ፡፡ አንቺ ባልሽውና በፈለግሽው መንገድ ነው የተጋባነው፡፡ እስካሁንም አንቺ የፈለግሽው ብቻ ነው እየሆነ ያለው፡፡ አንድ ትንሽ ነገር ብጠይቅሽ ይሄን ያህል..." ብሎ ጭንቅላቱን በትዝብት መልክ ነቀነቀ፡፡ ለምን እንደሆነ ባላውቅም አሳዘነኝ፡፡ ይህ ሰው ባሌ ነው ስል አሰብኩ፣ ከወላጅ አባቴ መሸሻ ይሆነኝ ዘንድ አምኜ የተጠጋሁት ሰው ነው፡፡ እውነት ለመናገር እስካሁንም አስቀይሞኝ አያውቅም፡፡ ምናልባት ግፊት እየተደረገበት ይሆን? በእኔስ ለመኩራት ወይም ለማፈር መንታ መንገድ ላይ እንዲቆም ሥልታዊ በሆነ ዘዴ እየተገደደ ይሆን? ይህን መሳዩን ነገር ሳወጣና ሳወርድ ቆየሁና ብድግ ብዬ እርሱ ያለበት ሶፋ ላይ በጎን እየተቀመጥኩና እጁን እየያዝኩ "እውነቱን ንገረኝ ሁመይድ..ይህ የአንተ ሃሳብ ነው? ንገረኝ፣ እያየኸኝ እውነቱን ንገረኝ?" አልኩት፡፡ ቀና ብሎ አይቶኝና ፈገግ ብሎ "የራሴ ሃሳብ ነው ኤፊ፡፡ ምነው ተልኮ ነው ብለሽ ተጠራጠርሽ እንዴ?" አለኝ፡፡ ለጥቂት ሰከንዶች አስተዋልኩትና "መልካም፡፡ አስቤ ውሳኔዬን አሳውቅሀለው" ብዬ የለቅሶ ድምፁን የሰማሁት ልጄ ጋር ተነስቼ ሄድኩ፡፡

ሁመይድ ባነሳው ሃሳብ ላይ ምን ዓይነት ውሳኔ ላይ እንደምደርስ ችግር ሆነብኝ፡፡ ነገሩን ከሁለቱም አቅጣጫ ለማጤን ሞከርኩ፡፡ ሂጃብና አባያ ላይ በማመፅ ከአባቴ ጋር ብዙ ነገር ተዳርሰናል፡፡ ቤተሰቤን ለበርካታ ጊዜያት ሰላም ነስቻለሁ፡፡ እኔም አባቴም በየፊናችን ለወራት ለከባድ ሕመም ተዳርገናል፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ በአቋሜ እንደፀናሁ ዘልቄያለሁ፡፡ ባደረኩት ተጋድሎና ባሳየሁት ጽናት በብዙዎች ዘንድ ሞገስን ሳተርፍ የሚሰድቡኝና የሚረግሙኝም ነበሩ፡፡ ስለዚህም ይህን ጽናቴን መተውና ለሽንገላ መሸነፍ ትልቅ ክህደት መስሎ ታየኝ፡፡ በአንፃሩ ደግሞ እኔ ያን ሁሉ ፈተና የተቀበልኩት ልቤን ላሳረፈው እምነትና ቃል እንጂ ለሂጃብና አባያ ብቻ አይደለም፡፡ እምነት አጠቃላይ ነገር ነው፣ ልብስ ደግሞ አንድና አነስተኛ መገለጫ ብቻ ነው፡፡ ምነው መካከለኛው ምስራቅ ያሉ ክርስቲያን እህቶች ሂጃብና አባያ ለብሰው ይውሉ የለ፣ የልብ እምነትና የሰውነት ጨርቅ የሚገጥሙበትም የማይገጥሙበትም ጊዜ ይኖራል ስል አሰብኩ፡፡ በዚያ ላይ ምንም ነገር ጠይቆኝ የማያውቀው ሁመይድን ማስቀየም ከባድና ለትዝብት የሚጥል መስሎ ተሰማኝ፡፡ እንዲህ ያለው ፈተና ውስጥ የከተተኝ ለምን እንደሆነ ወደፊት በደንብ ይጠየቃል አልኩና ሃሳቡን ለመቀበል ከጀለኝ፡፡ በሂጃብና አባያ የሚያዩኝ አባቴና አጋሮቹ ምን እንደሚሉ፣ እንዴትስ እንደሚፈነድቁ ታሰበኝ፡፡ በእነርሱ ሁኔታ ከመናደድ ይልቅ ፈገግ አልኩ፡፡ በውስጤ 'ሌላኛውንም መንገድ ማየት ደግ ነው' ብዬ ከመኝታዬ ተነሳሁ፡፡ ከቁርስ በኋላ ለመውጣት የሚዘገጃጀውን ሁመይድ "ሃሳብህን ተቀብያለሁ፣ ለዚያን ቀን በምትፈልገው አለባበስ እታይልሃለው፣ የግብዣውን ቀን በፍጥነት አሳውቀኝ" አልኩት፡፡ ያልጠበቀውን ነገር እንደሰማ የተደነቀው ሁመይድ ጥቂት ከተደናገረ በኋላ "አመሰግናለሁ ኤፊ" ብሎ ግንባሬን ስሞኝ ወጣ፡፡

                        (ይቀጥላል)

    -------- ማርያማዊት ገብረመድኅን --------

የሰርግ መዝሙሮች

///////////////////////////7

ሰናይ በዜና ሰናይ በዜና/4/
ሰናይ በዜና    ፍፁም ደስታ ነው
ሰናይ በዜና     ከጌታ የሆነ
ሰናይ በዜና     እንዲህ ይሞሸራል
ሰናይ በዜና     ማን አፍሮ ያመነ
ሙሺሬት         አበባ
ስርአቷ            አበባ
ያበራል            አበባ
ህይወቷ          አበባ
ሰናይ በዜና ሰናይ በዜና/2/
ሰናይ በዜና       እንዲ ነው ጋብቻ
ሰናይ በዜና       እንዲ ነው መዳር
ሰናይ በዜና       በቤተ ክርሥቲያን
ሰናይ በዜና       በስራት በክብር
እልልልልልልልልልልልልልልልልsaramareyama.890@gmail.com

ዓርብ 19 ጃንዋሪ 2018

የምዕራፍ ሦስት/የ22ኛ/ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ ጥያቄና መልስ ውድድር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን

ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እንደምን ሰነበታችሁ?? ሰላማችሁ ይብዛልኝ እያልኩ፦ እነሆ የምዕራፍ ሦስትን/ የ22ኛ/ ዙር የጠቅላላ እውቀት መንፈሳዊ  ጥያቄና መልስ እንዲህ ተጀመረ።
//////////////////////////

✍ ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣አምስቱ እህት አብያተ ክርስቲያናት/Oriental Churches/ የሚባሉት ማን ማን ናቸው???

//መልስ//፦ ኢትዮጵያ፣ግብፅ፣ ህንድ፣ ሶርያ እና አርመን ናቸው።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅2⃣በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን የመጀመሪያዋ  ገዳምና ቤተ-ክርስቲያን የትኛዋ ነች??

//መልስ//፦  አክሱም ጽዮን ናት።

✍ ጥ.ተራ.ቁ.✅3⃣ከዘጠኙ ቅዱሳን መካከል አንዱ የሆኑት ባታችን አቡነ አረጋዊ ያረፉበት ገዳም ምን በመባል ይታወቃል?.

//መልስ//፦ትግራይ ውስጥ ደብረ ዳሞ ይባላል።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅4⃣ወንጌል ማለት የስሙ ትርጉም ምን ማለት ነው??

//መልስ//፦ ዜና ሠናይ/ መልካም ዜና/ የምስራች ማለት ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅5⃣ነቢይ ማለት ምን ማለት ነው??

//መልስ//ነብይ ማለት፦ኃላፍያን አልፎ የተሰወረውን ሚስጢር ገና ለወደፊት የሚሆነውን የሚያውቁ/ሀብተ ትንቢት  የተሰጣቸው ቅዱሳን አባቶች ቅዱሳት እናቶቻችን  ነብይ ተብለው ይጠራሉ።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅6⃣12ቱ ደቂቀ ነቢያት ከሚባሉት መካከል ቢያንስ 5ቱን ጥቀስ???

//መልስ//፦ደቂቀ ነብያት የሚባሉት
1ኛ ቅዱስ ሆሴዕ
2ኛ አሞፅ
3ኛ ሚክያስ
4ኛ ዮናስ
5ኛ. ናሆም
6ኛ አብድዩ
7ኛ ሶፎንያስ
8ኛ ሐጌ
9ኛ ኢዩኤል
10ኛ ዕንባቆም
11ኛ ዘካርያስ
12ኛ ሚልክያስ እነዚህ ናቸው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅7⃣ጌታችን የተጸነሰበትንና የተወለደበትን ወርና ቀን ጥቀስ??

//መልስ//መጋቢት 29 ተጸነሰ ታህሳስ 29 ተወለደ።


✍ጥ.ተራ.ቁ✅8⃣ አንድ ክርስቲያን ሥጋና ደሙን ከመቀበሉ  አስቀድሞ ስንት ሰዓት መፆም አለበት??

//መልስ//፦ ለ18 ሰዓት መፆም አለበት።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅9⃣ የቤተክርስቲያን የልደት ቀን በመባል የምትታወቀዋ ድንቅ ቀን የቷ ነች?

//መልስ//መንፈስ ቅዱስ የወረደባት እለት/ቀን ነች። በሐዋርያት ሥራ ላይ ተጽፎ እናገኘዋለን።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅1⃣0⃣ጥምቀት ማለት ምን ማለት ነው???

//መልስ//፦ ጥምቀት ማለት በውኃ መነከር መዘፈቅ ብቅ ጥልቅ ማለት ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣1⃣ጥምቀትን አጥማቂው   ማን ተምማቂውስ ማን ነው???

//መልስ//፦አጥማቂዎች በሁለት የክህነት ደረጃዎች ብቻ ይፈጸማል። ይኸውም፦
በኤጲስ ቆጶስ በሚባለው ጳጳስ" እና በቄስ ብቻ ነው።
ተጠማቄዎች በክርስቶስ ያመኑ ሁሉ
ዮሐ (8፥36)

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣2⃣ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ወደ መጥምቁ ዮሐንስ ወርዶ {ሄዶ)ለምን ተጠመቀ??

//መልስ//፦አንድም ለትህትና፤ ለፍቅር፤ ስርዓትን፣ ለማስተማር፤ ጌታችን ቅዱስ ዮሐንስን መጥተህ አጥምቀኝ ቢለው ኑሮ የዛሬ ምህመን መጥታችሁ አጥምቁን ባሉ ነበር ካህናትን ባስቸገሩ
ነበር።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅1⃣3⃣ጌታችን ሲጠመቅ ባህር ሸሽች የመሸሹ ምሳሌ ምንድን ነው???

//መልስ// መሸሹ የኃጢአት ምሳሌ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅1⃣4⃣በዮርዳኖስ ወንዝ የሥላሴ ሚስጥር እንዴት ተገለጸ???

//መልስ//፦መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ተገለፀ
↪አብ የምወደው ልጄ ይህ ነው ሲል በቃል ተገለፀ
↪ወልድ ስጋ ለብሶ በዮርዳኖስ መሀል ቁሞ ተገልፀዋል።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣5⃣ዮርዳኖስ አንድ ወንዝ ሲሆን ዝቅ ብሎ ለስንት ተከፈለ ጌታችንስ ምኑ ላይ ነው የተጠመቀው???

//መልስ//፦ዮርዳኖስ አንድ ወንዝ መሆኑ አዳም አንድ ሁኖ መፈጠሩ ምሳሌ ነው ዝቅ ብሎ በ2 በዮር" እና በዳኖስ" ተከፍሎል ሁለቱም ዝቅ ብለው ተገናኝተዋል ከመገናኛው ላይም ጌታችን ተጠምቆል።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣6⃣ጌታችን ለምን "በዮርዳኖስ" ወንዝ ተጠመቀ???

//መልስ//፦አንድም እዮብና ንእማን በዮርዳኖስ ተጠምቀው ከደዌ ሥጋ ድነዋል።
 ሚስጥሩ ግን አዳምና ሔዋን ከገነት ከወጡ በኋላ ዲያቢሎስ መከራ አፀናባቸው አዳም የዲያቢሎስ ወንድ አገልጋይ ሔዋን የሴት አገልጋይ ነን ብላችሁ ስማችሁን ጽፍችሁ ስጡኝ ብሎ ዲያቢሎስ አታሏቸው ነበርና ይሁንብን ይደረግብን ብለው አዳምና ሔዋን ቃል ሰተው ነበር። ያንን ቃላቸውን/የእዳ ደብዳቤ አድርጎ በ2 እምነ በረድ ቀርፆ አንዱን "በዮርዳኖስ" አንዱን "በሲዖል" ጥሎት ነበርና በዮርዳኖስ ያኖረውን የእዳ ደብዳቤ 'ጌታችን' በጥምቀቱ ጊዜ በዮርዳኖስ የተጣለውን እንደ ሰውነቱ እረግጦ እንደ አምላክነቱ አቅልጦ ደምስሶልናል።

✍ጥ.ተራ.ቁ✅1⃣7⃣.በሀገራችን በኢትዮጵያ ጥምቀት ታቦት ወጥቶ መከበር የተጀመረው መቼ ነው???

//መልስ///፦ በ5ኛው ክ/ን በአፄ ገብረ መስቀል ዘመን ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣8⃣ባህር ሸሽች አንተ ዮርዳኖስስ ወደኋላ የተመለስከው ምን ሁነህ ነው። ይህን ቅዱስ  ቃል በየትኛው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል እናገኘዋለን ምዕራፍና ቁጥሩስ??

//መልስ//፦ መዝ (113፥3-5) ላይ እናገኘዋለን።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅1⃣9⃣የእግዚአብሔርን መኖር የምናውቅባቸው መንገዶች /ማስረጃዎቻችን/ የትኞቹ ናቸው??

 ሀ) በሥነ ፍጥረት መኖር

 ለ)የኅሊናችን ምስክርነት

 ሐ) የመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት

መ) ሁሉም መልስ ነው

//መልስ//መ/ ሁሉም መልስ ነው።

✍ጥ.ተራ.ቁ.✅2⃣0⃣የጌታችን በዮርዳኖስ ወንዝ መጠመቅ ምክንያት፡-

  ሀ) ትንቢቱ ይፈጸም ዘንድ

 ለ) የአዳምና የሔዋን የዕዳ ደብዳቤ በዚያ ተቀብሮ ስለነበረ

 ሐ)በብሉይ ኪዳን ለሥጋ ደዌ በዮርዳኖስ ይጠመቁ ስለነበረ ለነፍስ ድኅነት ይሆን ዘንድ።

 መ) ሁሉም መልስ ነው።

//መልስ//መ/ ሁሉም መልስ ነው።

የ22ኛ ዙር የጥያቄና መልስ ውድድር ይህን ይመስላል ከስተቴ አርሙኝ 👉ስል በትህትና እጠይቃለሁ።saramareyama.890@gmail.com

ሰኞ 15 ጃንዋሪ 2018

የጠፋው ልጄ ተገኘ መንፈሳዊ መነባንብ

*"*   *የጠፋው*  *ልጄ*   *ተገኘ*  *"*

🙎🏽‍♂ አባቴ ልንገርክ ኧኽ ብለክ ስማኝ
ንብረቴን እሻለሁ ለኔ የሚደርሰኝን አካፍልና ስጠኝ
ከህል ከከብት ከገንዘብም ቢሆን ሁሉን አስረክበኝ
ሆኖም አደራክን ዛሬ ነገ እንዳትል አሁኑኑ ይሰጠኝ
ሽማግሌዎች ጥራ ጉልማዬን ልወቅ ሸንሽነው ያካፍሉኝ
ድርሻዬን ለይተክ እንድታስረክበኝ እፈልጋለሁኝ

👴🏽 *በወላዲትዋ*!
ምንድነው የምትል የሆንከው አለ እንዴ?
እንዲህ ተበሳጭተክ የምታናግረኝ ምን ነክቶክ ነው ውዴ?
ማነው የስቀየመክ ክፉ የተናገረክ ወይስ ምን በደልኩክ
ገንዘብስ ለምንክ ምን ሊጠቅምህ ገና ልጅ አይደለክ?
ችግርም እንዳለ ንገረኝ አትፍራ አንተ በምን አቅምክ ትቋቋመዋለክ
እኔ እስካለሁ ድረስ አደራ እንዳይኖር ከቶ  የሚያስጨንቅክ

🙎🏽‍♂ እንደዚህ ስላልኩክ አይክፋክ አትናደድብኝ
ነገር ግን አሁን ደግሜ ዕልካለሁ ድርሻዬን አካፍለኝ
ያለኝን ስጥና ለኔ የሚደርሰኝ መርቅና ሸኘኝ
ተትረፍርፎ ሳለ አውድማ ጎተራው ለምን አሰሰተክ?
ብታካፍለኝም በእጥፍ ይገባል በወሰድኩት ምትክ
ይልቅ አባዬ ሳታመነታታ አሁኑኑ ስጠኝ ነው ደግሜ ምልክ


👴🏽 እሺ በቃ ልጄ እጅግ ከባሰብክ
እሰጥሀለሁኝ አትናደድ አሁን ውሰድ እሄው ድርሻክ
ሳልል ወደኋላ አስረክቤካለሁ ሁሉም ያልፋልና አትከፋ አይዞክ
ባገር ሽማግሌ ከንብረቴም ሁሉ አካፍዬካለሁ
ሰርተክ ጨምርበት አምላክ ይባርክልክ ብዬ መርቄሀለሁ

🙎🏽‍♂አመሰግናለሁ ደህና ሰንብቱልኝ
እንደዚህ ይሻላል በማያቁት ሀገር ዝና እላለሁኝ
መኖር እንዲህ እንጂ ቀብረር ፀዳ ብሎ
የት ነበርኩ እስካሁን እሄንን ለማየት ያልነቃሁት ቶሎ
በይ ነፍሴ ተደሰች ያሻሽን አድርጊ
ገንዘብ እንደው አለኝ በአንዳች አትስጊ
ብይ ጠጪ በቃ ሀሴት አድርጊ
ለስጋሽ እርካታ ለአይንሽም ደስታ ከቶም አትንፈጊ

💗 ከአባትህ ኮብልለህ ከፈሩ ወተሃል
አክብር የሚለውን ህጌንም ጥሰሃል
የልብህን ምኞት ስትፈፅም ኖረሃል
አላፊ ጠፊውን አለሙን መርጠሃል
መሰረት የሌለው ህወት ገንብተሀል
በዘፈን ጭፈራ በሱስይሁንህ ደንዝዘካል
ለሰራህው ስራ ደመወዝ ልክፈልህ
ተዘጋጅቻለው መማርያ

🙎🏽‍♂  ወይኔ ጉዴ ፈላ  ተራብኩኝ ተጠማው
ገንዘብ አለኝ እያልኩ ያኔ እንዳላቅራራው
 አለቀ ገንዘቤ  እሄው እጄ ባዶ ነው
የአባቴን ንብረት
ተድላን  የለመደው የቀድሞ ሕይውቴ
ጭራሽ ይባስ ብሎ ድንገት ተጎሳቁሎ ጠፋ ማንነቴ
ኪሴ ተራገፈ እጄ ባዶ ቀረ እኔም ሆንኩ ዋተቴ
ደስታ ሰላም ጠፋ  እራቀ  ከፊቴ
እርሀብ ፀናብኝ እጂግ ተንገላታሁ እስኪዝል ጉልበቴቤቴ
ከማር ከወተቱ የበላው  አንጀቴ
ትዝ ይለኝ  ጀመረ ፍቅሩ የአባቴ

ጥፋቴ ከባድ ነሁ አውቃለሁ ጠንቅቄ
ወደ አባቴ ልሂድ ልኑር በግ ጠብቄ
ይቅርታ ልጠይቅ እግሩ ላይ ወድቄ

💗 መመለስ አለብህ መልካም አስበሃል
ስህተት መስራትክ አሁን አስታውሰሃል
አባትክን ይቅርታ መጠየቅ ይገባሃል ስላንተ ያስባል ሁሌም ይወድሀል
ልጁን የሚጠላ አባት የት አይተሀል ?
ከልብህ ሁንና ጠይቀው ይቅርታ
ዳግም ለመበደል ልብህ አያመንታ

👴🏽 ገና ከሩቅ ሳይክ ሀሴት አገኘሁኝ
የጠፋውን ልጄን ጌታ ምልሶልኝ
ለብዙ ጊዜያት ደስታ ከኔ ርቆኝ
ሀዘን ሰፍኖ ቤቴ  ሰላምም  ሳላገኝ
ዛሬ መጣህልኝ ፍሪዳ ጣሉለት ጥሩ ዘመድአዝማድን
እጅግ ደስ ብሎና የጠፋው ልጃችን ስለተገኘልን
ለግሩ ጫማ አምጡ  ለዕጆቹም አንባር
ከጠፋበት ቦታ ስለተመለሰ አምላክ ተመስገን

🙍🏿‍♂ ምንድነው ይህ ሁሉ ትላንት ንቆን አይደል?
ዛሬ ተመልሶ ድርሻውን ሲጨርስ
ዳግም ደሞ መጣ ሌላውን ሊያፈርስ
እንዳሻው ሲቦርቅ ሲፈነጥዝ
ከርሞ የትም ሲልከሰከስ
ሲቸግረው መጣ የኛንም ሊካፈል ሳናስበው ድንገት
እንዴት ለዚህ ብኩን ለሆነብክ ሽፍታ
ንብረቱን አጥፍቶ ለመጣ ከርታታ
እንዴት ተቅበልከው በፍቅር በደስታ
 ለኔም አላሳየህኝ እሄንን ፈገግታ?
አገልጋይህ  ለሆንከህ ጠዋትና ማታ

👴🏽 ልጄ ተው እባክህ የስጋዬ ክፋይ
ላንተም  እንደዛው ነኝ ለያይቼም አላይ
የኔ ያልኩት ሁሉ ነው ግድ የለም ያንተ
ሳትለያዩበኝ አንድላይ ኑሩ እንጂ በፍቅር በሰላም
ወንድምክም አንተ
 ተገኘልን ከሞት ከጥፋት
ዛሬ
 ፀልይለት አንተም
ጥፋቱን እንዳይደግም
እናም እናመስግን ጌታን በዝማሬ


🙎🏽‍♂ ወይ አቤቴ ደጉ የቀዶሞ ስራዬን በደሌን ሳይቆጥር
ይልቁንም አባብሎ እሄው ተቀበለኝ በሰላም በፍቅር
ዕውነት ለውለታው ለታላቅ ምህረቱ ምን እከፍለዋለሁ
ስለቸርነቱ
 ስለዕርሕራሄው በሒወቴ ሁሉ አመሰግናለው
ዳግም ላልባድለው ገፍቼውም ላሌድ ቃል ገባለታለሁ።

   አሜን ወስበሀት ለእግዚአብሔር
ተፃፈ በእህተ ጊዮርጊስ
saramareyama.890gmail.com

የምዕራፍ አምስት(፭)የ46 የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ

✝በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡ አሜን! ↪️የምዕራፍ አምስት(፭) 46ኛ ዙር የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልስ⤵️ 1⃣ ቅዱስ ያሬድ ከመላዕክት የተማራቸው ሦስቱ የዜማ ዓይነቶች ምን ምን ናቸው?ሞገር...